Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Print this page
Saturday, 10 September 2011 13:57

..ሙዚቃውም አድማጩም ያደገበት ዓመት ነው..

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ያለፈውን 2003 ዓ.ም ከሙዚቃ ኢንዱስትሪው አንፃር እንዴት እንዳለፈ ስገመግመው፤ አድማጩ ጥራት ያለውን ሥራ የሚመርጥበት ጊዜ በመሆኑ የሙዚቃ ሞያውም አድማጩም ያደገበት ነው፡፡ ነገር ግን የቅጂ መብት ጥሰት በየቦታው በመንሠራፋቱ እና በሌሎች የተለያዩ ምክንያቶች አጠቃላይ ኢንዱስትሪው ማደግ በሚገባው መጠን ሊያድግ አልቻለም፡፡ ከሞያው አንፃር እያበረከትኩ ያለሁትን አስተዋጽኦ በሚመለከት ከተጠየኩ ለ2004 ዓ.ም መግቢያ አዲስ የሙዚቃ አልበም አበረክታለሁ ብዬ ነበር፡፡ ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች እና ከቅጂ መብት ጥሰት ጋር በተያያዘ አዲስ ዓመትን ተሻግረዋል፡፡ ከዓመቱ በአንዱ ወር ግን እነዚህ አዳዲስ ሥራዎቼን ለሕዝብ ጆሮ አደርሳለሁ የሚል እምነት አለኝ፡፡  በሌላ በኩል ክለብ ውስጥም በሙዚቃው ዘርፍ በርካታ ጥሩ ነገሮችን ለመሥራት እየጣርኩ ነው፡፡  በ2003 ዓ.ም ቀን በቀን ጤነኛ ሆኜ ማሳለፌ አስደሳች ትውስታዬ ነው፡፡ ቴሌቭዥን በከፈትኩ ቁጥር የምሠማው የዓለም አለመረጋጋትና ችግር እንዲሁም በኢትዮጵያ የተከሰተው የኑሮ ውድነት 2003ን በአስቸጋሪነቱ የሚያስታውሱኝ ክስተቶች ናቸው፡፡ 2004 ዓ.ም እርስ በእርስ መዋደድ ያለባት፤ ሰላም የበዛባት፣ የበለፀገች ኢትዮጵያን ለማየት እመኛለሁ፡፡ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መልካም አዲስ ዓመት፡፡
ሸዋንዳኝ ኃይሉ
ድምፃዊ

Read 4695 times

Latest from