ልብ-ወለድ

Rate this item
(6 votes)
ዐይኖችሽ ውስጥ የሚነዱት ጧፎች ልቤን ከሩቁ ያቀልጡትና በአጥንቴ ስሮች ልቆም ያቅተኛል፣ እንገዳገዳለሁ፤ የቀለጠው ልቤ እንደ ሎጥ ሚስት የጨው ዐምድ የሆነ ይመስለኛል፡፡ ፍቅሬ ልብሽ አበባ ነው፡፡ ንቡ ልቤ ቀለምሽን ሲያደንቅ፣ መዐዛሽን እንደ ጡጦ ሲጠባ ይቆያል፡፡ ድንኳኔ በሳቅ ፣ ዐይኔ በተስፋ እንዲሞላ፣…
Saturday, 09 May 2020 13:21

የጥበብ ጓሎች

Written by
Rate this item
(3 votes)
 ጆሮ ግንዱ ጋለ፤ ቀጥታ እንደገባ ጥናታዊ ጽሑፉን ሊያሰናዳ አንደ ፍሬ ቴምር ቀመሰና ወደ መጻሕፍት መደርደሪያው ሄደ:: ለብቻ የሚያስቀምጣቸው መጻሕፍት በቦታቸው የሉም፡፡መቸም ቢሆን እንደ ስዕለት ልጆች የሚያያቸው መጻሕፍት ከሌሉ የርሱ ሕይወት እንዳለ አይቆጥረውም፡፡ በድንጋጤ ውስጥ ሆኖ ወደ ኋላ አሰበ፡፡ በተለየ ሁኔታ…
Saturday, 25 April 2020 13:36

የመስቀሉ ድንበር!

Written by
Rate this item
(4 votes)
ፍልቅልቅ ብለው እንደሳት የሚነድዱ ዐይኖች፣ እንባ የገረፋቸው ጉንጮች፣ ሰቀቀን ያረገባቸው ተስፋዎች ጋራው ላይ ተቀይጠዋል፡፡ ቆነጃጅት፣ ፈርጣማ ወጣቶች፣ እንደ አበባ የፈኩ ልምጭ የመሰሉ እመቤቶች፣ የገረጡ ፊቶች፣ የነደዱ ቀለሞች፣ ሁሉም በያይነቱ ፊታቸው ተዘርግቷል፡፡ሶስቱ ሰዎች ከሁሉም ከፍ ብለው ሰማዩን የደገፉ ምሰሶ የሆኑ ይመስል…
Rate this item
(10 votes)
ሳምንት ያህል ከቤት ሳልወጣ ቆየሁ:: ተጋድሜ እውላለሁ፤ ፊልም አያለሁ፣ መፅሃፍ አነባለሁ … እተኛለሁ፡፡ ይሰለቻል:: ነገርየው እየከፋ እንደሄደ ተረድቻለሁ፤ ግን ደግሞ ሳልወጣ ከዚህ የበለጠ መቆየት እንደማልችል ስረዳ ልብሴን ቀያይሬ ተነሳሁ:: ቢያንስ ቢያንስ ለጥቂት ቀናት የሚሆን አስቤዛ እንዲሁም አልኮል ነገር ባገኝ እገዛለሁ፡፡…
Rate this item
(10 votes)
የቤቴ መዝጊያ ሲንኳኳ ግር ብሎኝ በዝምታ ጆሮዬን ቀሰርኩ፤በደጉ ቀን የማይንኳኳው ቤቴ በዚህ በምጥ ቀን መንኳኳቱ ግር አለኝ፡፡ አሁንም ተንኳኳ:: ማንም ሰው በሬን አያንኳኳውም፡፡ ወይ ቀበሌ፣ አንዳንዴ ደግሞ ቅባት፣ የቤት ማጽጃ እንዲሸጡ የተፈቀደላቸው ነጋዴዎች ይመጣሉ፤ እርሱም አልፎ አልፎ ነው:: ጎረቤቶቼ በአውዳመት…
Saturday, 04 April 2020 12:03

ደራሽ

Written by
Rate this item
(6 votes)
እየጮህኩ ነበር የነቃሁት፡፡ “ሃሎ ሃሎ!..” ጩኸቷ ነቅቼ እንኳን ይሰማኛል፤ “ለምንድን ነው ለእኔ ያልደወልሽልኝ? ወንድሜን አፍነሽ ልትገይው ነው?” አባባሏ ከነቃሁ በኋላም እንኳን ይሰማኛል፡፡ ቁጣዋ የሚያስበረግግ ነው፡፡ “ለምን? ለምን….?” የመረረ ጥያቄዋ ያስጨንቃል፡፡ እንዴት ግን? ቢቸግረኝ እራሴን ጠየቅሁ፡፡“የፈጣሪ ያለህ! ደወልኩላት እንዴ?” በድንጋጤ ወንድሜን…