ልብ-ወለድ

Rate this item
(11 votes)
የቁም ቅዠት ውድቅት ላይ ነው፡፡ ጧ ያለ እንቅልፍ ላይ ነኝ፡፡ ግን እረፍት የለሽ ነፍሴ ትቃትታለች፡፡ይመስለኛል !... የአያቴ ቤት ነው፡፡ ፊት ለፊቱ ለጥ ባለ ሜዳ ላይ የሚገማሸር ወንዝ አለ፡፡ ህፃናት ጠርዙን ይዘው ተኮልኩለዋል:: በእጃቸውና በእግራቸው እንደ ልብ ያንቦጫርቃሉ፡፡ በደስታ ማዕበል ይከንፋሉ::…
Saturday, 01 August 2020 13:19

ያልታረመው…

Written by
Rate this item
(0 votes)
መበማለዳ ደመና የተጎነጎነው የጀምበሯ ሹሩባ ያምራል፡፡ ተራራው በጤዛ እርሶ ደረቱን ለሙቀት አጋልጦ ሰጥቷል፡፡ ነፋስ ሁሉን በፍቅር ለመዳበስ ይመስል ለስለስ ባለ የዋሽንት ስልት ይርመሰመሳል፤ የባህሩ ውሃ እናቱ ደረት ላይ ጡት እንደሚዳብስ ህጻን ፈገግታው ልከኛ ነው፣ እስክስታም ለመውረድ ተዘጋጅቷል፡፡ ማለዳው እንደ ዛሬ…
Saturday, 18 July 2020 16:20

አዲስ ዐመል

Written by
Rate this item
(7 votes)
ፍቅሯ ውስጤ እየገፋ ሲመጣ ይታወቀኛል፡፡ ነጋ መሸ እንደ ዳንስ ውስጤ የሚላወስ፤ ነፍሴን እንደ ጡጦ የሚጠባ ምትሃት፤ አጠገቤ ተቀምጣ እንድትናፍቀኝ የሚያደርግ ምትሃት እንደሆነ ይታወቀኛል፡፡ አሁን አራት ወራት አልፈናል ብዬ ሳሰላው፣ ነገሩ ይደንቀኛል፡፡ የናፍቆት የሰቀቀን ጊዜ ይሆንብኛል፡፡ ነገሩ ሁሉ እንደተገናኘን ሰሞን አይደለም፤…
Saturday, 11 July 2020 00:00

ኧረ በህግ

Written by
Rate this item
(5 votes)
ይሔ የቀዬው የአውጫጭኝ ሥርዓት ነው፡፡ ማህበረሰቡ በእምነቱና በሥርዓቱ መሠረት ይዳኝበታል፡፡ ይካሳልም ይቀጣልም፡፡ የልብ ፍርድ ሚዛን ሲደፋ ማህበረሰቡ የእውነት ዳኛ ይሆናል፡፡ የቀዬው፣ ሽማግሌዎች ብቻም ሣይሆኑ የተሰበሰቡበት ግዙፍ ዋርካም ሳይቀር ይወደዳል (ለዚህ ይመስለኛል እንኳን ሰው ግንድ ያስጥላል) የሚባለው፡፡ እዚህ መንደር ዛሬ ለየት…
Saturday, 04 July 2020 00:00

የዋህ

Written by
Rate this item
(6 votes)
 ከእንቅልፉ እንደነቃ እንደነገሩ አጣጥፎ ወንበር ላይ ያስቀመጣቸውን ልብሶቹን ለበሰና ማሠሪያቸውን ሳይፈታ ያወለቃቸው ጫማዎቹን በትግል ተጫምቶ፤ ያደረ ፊቱን ውሃ እንኳን ሳያስነካ የቤቱን በር ቆልፎ ወጣ:: ለደቂቃዎች ተጉዞ ቴዎድሮስ አደባባይ ሲደርስ፤ አስፋልቱን ተሻግሮ፤ ቁልቁል ወረደና ቴሌው ፊት ለፊት ባለችው ቀጭን፣ ቁልቁለት መንገድ…
Rate this item
(2 votes)
 አለን አውስተን በችኮላ አረማመድ፣ ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ እያለ፣ ያሮጌውን ፎቅ ደረጃ በዳበሳ ከወጣ በኋላ መተላለፊያው ላይ ቆሞ በደብዛዛ ብርሃን በየክፍሉ በር ላይ የተጻፈውን ለማንበብ ሞከረ፡፡ ነገር ግን የሚፈልገውን በር ጽሑፍ ለይቶ እስኪያገኝ ድረስ ብዙ ደቂቃዎችን አባከነ:: ትንሽ ቆይቶ እንደምንም ብሎ…