የግጥም ጥግ
እስከዚህም ፍቅርሽከሰንደል ጭስ በላይደምቆ የማይገዝፈውምንሽን ልፃፈው?እስከዚህም ፍቅርሽበጧት የረገፈውከዕድሜ እሬሳ ውጭዋኝታ ምኑን ታውጣውነብሴ ከባለፈው?እስከዚህም ፍቅርሽዘመን ያሳረጠውምኑን አስታውሼሣጌን እየማኩኝእንባዬን ልዋጠው?እስከዚህም ፍቅርሽሲነድፍ ያለሰንኮፍመታሁ ቢልም ለኮፍእንኳንና ሰምበርስምሽስ ማን ነበር?
Read 3001 times
Published in
የግጥም ጥግ
ኧረ ጉድ ባየህ ወዳጄ ኧረ ጉድ ባየህ ጓዴ!ጓዴ ባለህበት ፅና! ስምንት አመት ሆነው ዝክርህ፤ ይህንን ጉድ ከማየት ያለህበት ነው እሚሻልህ!ገበያው ተደበላልቋል፤ ተገዢው ጊዜውን ይቃኛል ገዢው ግና ተሰናብቷል ስምንት ዓመት ሆነህ ጓዴ፣ ካለፍክ ከዚህ ሀገር እክል ተበዳይ አርፎም ቢተኛ፣ በዳይ ዘራፍ…
Read 3225 times
Published in
የግጥም ጥግ
አበባው አብቦ ንቡ ገብቶልህእንግዲህ ጉብሌ ማር ካላበላህ...“እንኳንስ ማርና...አላየሁም ሠፈፍ...”እያልህ በመራራ፣ ዜማ ከመንሠፍሠፍ...ያ!... የቀፎው አውራ፣ ማሩን የደበቀውንብ ሆኖ ሲመጣ...ጭስ ሆነህ ጠብቀው!
Read 2802 times
Published in
የግጥም ጥግ
የተነሳብህ ለትየዛፍ ባላንጋራከምትተናነቅከመቶ ቅርንጫፍከሺህ ቅጠል ጋራእንደ ጡንቻ ሁሉስልት በማፈርጠምወርደህ ከግንዱ ጋርአንድ ለአንድ ግጠም!...
Read 2922 times
Published in
የግጥም ጥግ
ሲከፋው፤ከተማም እንደ ሰው ልጅ መልክየታመቀ ህመም ግርዶሽበበሩ ድባብ ይጥላልየተነከረ ከል ሸማየጠቆረ ማቅ ይለብሳልፅልመት ፀሐዩን ያደምቃልሲቃጠል ብርሃን አይሰጥምሲጋይ መቀት አይወልድምእንደ በረዶ ክምርአጥንት ያቀዘቅዛልየደም ዝውውር አግዶየስትንፋስ ሂደት ይዘጋል አንድ ባንድ የተካበው ካብ በቅፅበት ግፊት ተንዶ በበቀል ክብሪት ይጫራል፡፡ያልተቀመረ ብሶት ጎርፍአይኑን ጨፍኖ ይነዳልየጊዜን…
Read 2842 times
Published in
የግጥም ጥግ
ሞት ማስደንገጥ ሲያቅተውሞት ማስደንገጥ ሲያቅተውያን ጊዜ ነውምን መሆኔን የማላውቀው፡፡ ነፍስ ነስጋ ስትለይ ተመልሳ ላትከተት የእንቁላል ዘመኑን አልፎ ሰብሮ እንደወጣ ነፍሳት እንኳን በግፍ ተሰርቃ እንደሷ ሕይወት ባዘለ በመሰሏ እጅ ተነጥቃ በእንቅልፍ ዓለም እንኳን ጀንበር ሲጠባ ባታይ ለወትሮው የቋሚው የውስጥ ለቅሶ የኗሪው…
Read 2642 times
Published in
የግጥም ጥግ