ኪነ-ጥበባዊ ዜና

Rate this item
(0 votes)
የቀድሞው የፓርላማ አባልና የአሁኑ ዲፕሎማት የአቶ አማኑኤል አብርሃም ሁለተኛ ስራ የሆነው “ወላይታ በዘመናዊቷ ኢትዮጵያ“ የተሰኘ መፅሃፍ ለንባብ በቃ፡፡ መፅሀፉ በዋናነት ወላይታ ከጥንት እስከ አሁን የተጓዘበትን ታሪክ፣ባህል፣ሀይማኖትና ስብዕና በዝርዝር የሚያስቃኝ ሲሆን ከሽፋን ስዕሉ ትርጉም ገለፃ ጀምሮ በርካታ ጉዳዮች በውስጡ መያዙን የመፅሀፉ…
Rate this item
(0 votes)
ዋልያ መጻሕፍት በየሳምንቱ የሚያዘጋጀው የመጻህፍት ውይይት መርሓግብር፣ በዛሬው ዕለት የዶ/ር በድሉ ዋቅጅራን “የ፭ ግጥም እድሜ” መጽሐፍ ለውይይት ያቀርባል፡፡ በዚህ መርሃግብር ታዳሚያን ከገጣሚው ጋር ከሚያደርጉት የፊት ለፊት ውይይት በተጨማሪ መጽሐፍ የማስፈረም ሥነሥርዓት እንደሚኖር ታውቋል፡፡መርሐግብሩን ዛጎል የመጻሕፍት ባንክና ዋልያ መጻሕፍት በትብብር የሚያሰናዱት…
Rate this item
(0 votes)
ገቢው በ2 ቢ. ብር ለሚገነባው የኩላሊት ህክምና ሆስፒታል ማስጀመሪያ ይውላል ድርሰትና ዝግጅቱ የአርቲስት ሰለሞን ቦጋለ የሆነው “የራስ መንገድ”የተሰኘው ፊልም የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ በስካይ ላይት ሆቴል ይመረቃል፡፡የምረቃ ሥነሥርዓቱ የመግቢያ ዋጋው 2ሺ ብር ሲሆን እራትን ይጨምራል ተብሏል፡፡በዕለቱ የሚሰበሰበው ገቢም…
Rate this item
(2 votes)
 የደራሲና ጋዜጠኛ ዘነበ ወላ “አይ ፐሲዜ እና ሌሎች ወጎች” የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ከሰሞኑ ለንባብ በቅቷል፡፡ ደራሲው፤”የተከበራችሁ አንባቢያን” በሚል ርዕስ ባሰፈረው ማስታወሻው፤ “እዚህ ጥራዝ ውስጥ የምታገኟቸው ወጎች አዳዲሶችም ከዓመታት በፊት የጻፍኳቸውም ናቸው።” ብሏል።ከአንጋፋ ደራሲያን ጋር ያደረገውንም ቃለ-ምልልስ በዚህ መድበል ውስጥ ማካተቱን…
Rate this item
(0 votes)
በኮቪድ-19 ወረርሽኝ መከሰት ሳቢያ ላለፉት ሁለት ዓመታት ተቋርጦ የቆየው “ንባብ ለህይወት” የመጻህፍትና የምርምር ተቋማት አውደ ርዕይ፣ ከትላንት በስቲያ ሐሙስ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል የተከፈተ ሲሆን ለአምስት ቀናት እንደሚቆይ ታውቋል፡፡በዚህ 5ኛው “ንባብ ለህይወት” አውደ ርዕይ ላይ ደራሲያን፣ የመጻህፍት አሳታሚዎችና አከፋፋዮች እንዲሁም…
Rate this item
(1 Vote)
 ሁለተኛው ዙር “ዱቡሻ” የኪነጥበብ ምሽት ዛሬ አመሻሹ ላይ በሶዶ ከተማ በጉተራ አዳራሽ በተለያዩ የኪነጥበብ መሰናዶዎች ይካሄዳል። በምሽቱ ግጥም፣ ወግ በወላይትኛ፣ ሙዚቃ፣ የታዋቂ ሰዎች ልምድና ተሞክሮና ሌሎችም ዝግጅቶች ይቀርባሉ ተብሏል፡፡ በኪነጥበብ ምሽቱ ላይ ገጣሚያኑ መንበረማሪያም ሃይሉ፣ አስታውሰኝ ረጋሳ፣ ድምፃዊ ዘውዱ በቀለ፣…