ኪነ-ጥበባዊ ዜና
የኮሜዲያን ደረጀ ኃይሌ እና አሁን በህይወት የሌለው ባልደረባው ሀብቴ ምትኩ ሥራዎች የተካተቱበት “ወርቃማው ጊዜ” የኮሜዲ ቪሲዲ ከትናንት በስቲያ ወጣ፡፡ ቁጥር 1 በሚል በቀረበው የኮሜዲ ቪሲዲ ላይ 20 የኮሜዲ ሥራዎች የተካተቱ ሲሆን፤ ቪሲዲውን እያሰራጨ ያለው “ፒያሳ ዘ አራዳ ኢንተርቴይመንት” ነው፡፡
Read 1140 times
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
ከአውሮፓ የስፔን እና የፖርቱጋል፣ ከአሜሪካ ደግሞ የብራዚል፣ ኩባ፣ ቬኔዚዋላ፣ ሜክሲኮ እና አርጀንቲና ፊልሞች የሚታዩበት ስምንተኛው “የኢብሮ-አሜሪካ” ፊልም ፌስቲቫል ከትናንት በስቲያ ምሽት በጣልያን የባህል ተቋም ተጀመረ። ሐሙስ ምሽት፣ “ኤርማኖ” የተሰኘው የቬኔዙዋላ ፊልም ሲታይ፤ ትናንት “ኖሶድሮስ ሎስ ኖብልስ” የተሰኘው የሜክሲኮ ፊልም ታይቷል፡፡…
Read 1180 times
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
ዛሌፍ የሥነ ጥበብ እና ፋሽን ዲዛይን ተቋም፣ በታዋቂ ዲዛይነሮች የተሰሩ አልባሳት የተካተቱበት የፋሽን ትርዒት ዛሬ ከቀኑ 10 ሰዓት በኢንተርኮንቲነንታል ሆቴል እንደሚያቀርብ አስታወቀ፡፡ ከተቋሙ የሥራ ውጤቶች መካከል በ2003 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሂልተን የቀረበው በኮንዶም የተሰሩ አልባሳት ዐውደርዕይ ይገኝበታል።
Read 1267 times
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
በኮንስታብል ጌታቸው ዳምጠው የተፃፈው “የብልህ ፖሊስ ቁልፍ ምስጢር” የተሰኘ አነስተኛ መፅሐፍ ባለፈው እሁድ ካዛንቺስ በሚገኘው ወረዳ 8 አዳራሽ ተመረቀ፡፡ ፖሊሶች ሊገነዘቧቸው በሚገቡ አምስት መልእክቶች ላይ ያተኮረው መፅሐፍ 50 ገፆች ያሉት ሲሆን ዋጋው 25 ብር ነው፡፡
Read 999 times
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
ኢትዮጵያውያን እና እንግሊዛውያን ሠዓሊዎች የሚሳተፉበት የሥዕል አውደርእይ ሰኞ ከምሽቱ 12፡30 ቦሌ አውሮፓ ሕብረት መ/ቤት አካባቢ በሚገኘው ሲዳማ ሎጅ ይከፈታል፡፡ አውደርእዩ ለአንድ ሳምንት ለሕዝብ ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡
Read 1148 times
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን “መጽሐፈ ቅዳሴ” ወደ ኦሮምኛ ቋንቋ ተተረጎመ፡፡ ለብዙ ዘመናት “መጽሐፈ ቅዳሴ”ን በግእዝ እና በአማርኛ ስትጠቀምበት የቆየችው ቤተክርስትያኗ፤መፅሃፉን በኦሮምኛ ማስተርጎም የጀመረችው በ1999 ዓ.ም እንደሆነ ታውቋል፡፡ የመጽሐፉ መተርጎም በኦሮሚያ ክልል ላሉ አብያተ ክርስትያናት በኦሮምኛ ለመቀደስ ያስችላቸዋል ተብሏል፡፡ የቤተክርስትያኒቱ ቅዱስ…
Read 6836 times
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና