የግጥም ጥግ
ወንዜም ሞላ ቦይምንጬም አትጉደይከስሬ ስትፈልቂራሴን እንዳይምስሌ ይፍሰስብሽፀድተሸ ብታጠሪኝወንዜ ፍሰሽልኝ፡፡ፍሰሽልኝ ወንዜ፤ተቀላቅሎ ይኑርወዝሽና ወዜ፡፡ጥያቄ ነንጥያቄ ነንለራሳችንመልስ የሌለን፡፡በሴኮንዶች ተጀምረንበአመታት የምናድግበግዜ ጎርፍየምንጓዝ የምንከንፍመነሻ እንጂመድረሻ የለሽ ፍጡራንሄደን ሄደን…ሄደንጀማሪዎች የምንሆንአውቀን አውቀንመሃይማን፤አድገን አድገን-ህፃናት ነን!ጥያቄ ነን!
Read 861 times
Published in
የግጥም ጥግ
ክፉ ፍርሃት ጨለማ እኮ…! በድቅድቁ - ምሽቱ ላይ ጥቁር ሌሊት መቀለሙጽልመቱ ውስጥ - ተስፋ አርግዞ - ሊነጋ ነው መጨለሙ፡፡ብርሃን ግን… ካድማሱ ጥግ ‘ብቅ‘ ብሎ - ፀሐይ ክንፉን ሚዘረጋው፣የመከነ ተስፋ ይዞ - ሊጨልም ነው የሚነጋው፡፡***የሚሊኒየሙ አናፂአብዮት ፈንድቶ - ጥርስ ቀን ወጣለት፣…
Read 1217 times
Published in
የግጥም ጥግ
አፈቅርሻለሁ ነፍሴ፤እንደ እራሴእንደ አበቦቹ ሽታ፤ እንደ ቢራቢሮ እስክስታ፤እንደ ጥርኝ ጭቃ፤ልክ እንደ ስጦታ ዕቃ፤እወድሻለሁ እኔ፤ እወድሻለሁኝ፡፡እንደ ፍልስፍና ሃሳብ፤ሊጠግብ እንዳለ ረሃብ፤እንደ ህፃን ልጅ ሳቅ፤እንደ ዘላለማዊ ሃቅ፤እወድሻለሁ እኔ፤ እወድሻለሁኝ፡፡እንደ ሎጂክ፤እንደ ተፈጥሮ ህግ፤እንደ ቋንቋ፤ልክ እንደ ሙሉ ጨረቃ፤እወድሻለሁ እኔ፤ እወድሻለሁኝ፡፡እንደ ሙዚቃ ቅንጣት፤እንደ አልጋ ውስጥ ትኩሳት፤ልክ…
Read 1162 times
Published in
የግጥም ጥግ
“አገር ውዝግብ ውስጥ ስትወድቅ የማይናድ የሚመስለው ይናዳል። ከድጡ ወደ ማጡ ይሄዳል። “ወጣ ወጣና እንደ ሸንበቆ፣ ተንከባለለ እንደ ሙቀጫ” ያሰኛል። ህዝብ መሪዎች ላይ እምነት ያጣል። ሰላም ሰላም-የሚለው ሁሉ ትርምስና ሁከት ይሰማዋል።“
Read 858 times
Published in
የግጥም ጥግ
(በድሉ ዋቅጅራ) (በድሉ ዋቅጅራ)ወንድምን ከወንድሙ ቢለዩት፣ አልቦ ስጋ - ደም፣ ነፍስም አልቦ፤ጮጮ ላይሞላ፣ ታልቦ ታልቦ፤ልምሻ ሊጥለው፣ አቅም ሰልቦ፡፡ወልነት ያጣው፣ የኛም ቃል፤ሲዘረጋ ይጠቀለላል፤ሲያወፍሩት፣ ደርዙ ይሰላል፡፡የሰው ልጅ ንፉግ ህይወቱን፣ ለነገ ቸርነት ሲያጨው፤ያልተጨበጠ ድንግዝ ምኞቱን፣ በዛሬ ብርሀን እያየው፤ተስፋ አለና ሰየመው፡፡ችግሩ ከተስፋችን ስር፣ ያቆጠቆጠው…
Read 960 times
Published in
የግጥም ጥግ
ተኖረና – ተሞተ“ሳለ – ለሌለ”እየታለ . . . እየተሌለበመሸ – ነጋ – መሸእንደነበረ . . . እንዳለእንዳደረ . . . እንደ – ዋለእንዲሁ . . . እንደ – ዋተተ“መኖር”ን እንደ – ሞገተ“ኗሪ” ሳይኖር . . .ኖረ . . . ኖረና…
Read 849 times
Published in
የግጥም ጥግ