Administrator

Administrator


*በኤክስፖው ከ30ሺ በላይ ለሚሆኑ ጎብኚዎች  ነጻ የህክምና  ምርመራ ይሰጣል

አፍሮ-ኤዥያ ዓለማቀፍ የጤና ኤክስፖ፣ እዚህ አዲስ አበባ በኤግዚቢሽን ማዕከል፣ ከግንቦት 9-11 ቀን 2016 ዓ.ም ለሦስት ቀናት  ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ፡፡

በኤክስፖው ላይ ከ400 በላይ የአገር ውስጥና የውጭ ድርጅቶች፣ ከ30ሺ በላይ ጎብኚዎችና  ከ2ሺ በላይ የጤና አጠባበቅ ባለሙያዎች  ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡

የጤና ኤክስፖውን አስመልክቶ አዘጋጆቹና አጋር ተቋማት  ዛሬ ከሰዓት በኋላ 8 ሰዓት ላይ በራማዳ  ሆቴል የሚዲያ ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት  ሰፊ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡



በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንደተመለከተው፣ በጤና ኤክስፖው  ላይ የፓናል ውይይቶች፣ ዎርክሾፖችና ኤግዚቢሽኖችን ጨምሮ በርካታ ኹነቶች ይቀርባሉ፡፡ የጤና ባለሙያዎች የልምድ ልውውጥ የሚያደርጉበትና የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግር የሚካሄድበት እንዲሁም የትስስርና የትብብር ዕድሎች የሚፈጠርበት  መድረክ እንደሚኖርም ተጠቁሟል፡፡

ኤክስፖው በጤና አጠባበቅ ኢንዱስትሪ ውስጥ የህዝብ ጤናን፣ ፋርማሲዩቲካልስን፣ የህክምና ቴክኖሎጂንና ሌሎች በርካታ ርዕሰ ጉዳዮችንና ዘርፎችን እንደሚሸፍን የተገለጸ ሲሆን፤ ይህ ሁሉን አቀፍ አቀራረብም ተሳታፊ ድርጅቶችና ጎብኚዎች በተለያዩ መስኮች ከአዳዲስ ዕድገቶችና ፈጠራዎች ጋር እንዲተዋወቁ ዕድል ይፈጥራል ተብሏል፡፡

“ድልድዮችን እንገንባ፣ ህይወትን እናድን” በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው በዚህ ዓለማቀፍ የጤና ኤክስፖ፤ ከ30ሺ በላይ ለሚሆኑ ጎብኚዎች ነጻ የጤና ምርመራ የሚከናወን ሲሆን፤ ለጤና አጠባበቅ  ባለሙያዎችም ነጻ ሥልጠና እንደሚሰጥ ታውቋል፡፡

ለሦስት ቀናት በሚቆየው የአፍሮ- ኤዥያ ዓለማቀፍ የጤና ኤክስፖ ላይ ከህንድ፣ ዱባይ፣ ታይላንድ፣ ቱርክ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ማላይዥያና ሌሎችም አገራት የተውጣጡ በጤና ላይ የሚሰሩ ተቋማትና ባለሙያዎች እንደሚሳተፉበት ተጠቁሟል፡፡

ኤክስፖው ከወትሮው በተለየ በቢዝነስ ላይ ብቻ የሚያተኩር ሳይሆን፣ ተቋማት ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን ለመወጣት ልዩ ዕድል የሚያገኙበት እንደሆነም ተነግሯል፡፡

ይህን ዓለማቀፍ የጤና ኤክስፖ ኤፍዚ ማርኬቲንግና ኮምዩኒኬሽን ኃ.የተ.የግ. ማህበር ከሰላም ኸልዝ ኮንሰልታንሲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ሲሆን፤ ሳልማር ኮንሰልታንሲ፣ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር፣ የኢፌዲሪ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ባለሥልጣን፣ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብና መድሃኒት ባለሥልጣን እንዲሁም የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት በአጋርነት እንደሚሳተፉበት ታውቋል፡፡

For more than 3,000 years, the Jewish people have reenacted their journey to freedom during the Passover festival, as they joyously celebrate the Children of Israel's exodus from slavery in Egypt to a life of liberty and independence in the Land of Israel.

This holiday’s message can resonate with people of diverse backgrounds and beliefs, as it emphasizes the universal yearning for personal and collective freedom. Always coming just before the Ethiopian and other Eastern Christians’ celebrations of Fasika/Easter, the Passover holiday is one part of a larger holiday season which touches us all, Israelis and Ethiopians alike.

This year, however, our joy is tinged with sadness. As Israeli families gather for the traditional Seder meal, the Passover dinner will be accompanied by sorrow for our fallen soldiers and civilians, prayers for the recovery of the wounded, and expressions of solidarity with the tens of thousands of displaced Israelis who cannot return to their homes. Many families will set an empty place at their Passover table to symbolize our longing for the release of the 133 men, women and children still being held hostage in Gaza in the most horrific conditions imaginable.

Since October 7th, Israel has been confronted with brutal attacks and existential threats emanating from the Iranian regime and its many proxies, from Hamas in Gaza to Hezbollah in Lebanon, through the Houthis in Yemen to other militias and terrorists in Syria and Iraq. These self-declared enemies of the Jewish state openly threaten Israel with complete annihilation. More ominously, they have not hesitated to try and turn their malevolent aspirations into reality, as recently demonstrated by Iran's massive missile and drone attack and Hamas' massacre of 1,200 Israelis on 7 October.

Despite the resounding success in repelling Iran's attack on 14 April, realized with the extraordinary cooperation of the US and Israel’s allies in Europe and the region, as well as the exemplary military accomplishments made in the fight against Hamas in the Gaza Strip, the war is not yet over. Much remains to be done, including the restoration of deterrence against the Ayatollahs' regime and its proxies. This step is essential to preventing additional direct attacks on Israel, and also to stopping the spread of the Islamic revolution worldwide, Iran's efforts to become a nuclear power, and its ballistic missiles program.

A key element is the designation as a terrorist organization of the Iranian Revolutionary Guard Corps (IRGC) - which is a primary pillar of support of the regime and the spearhead of its repressive policies in Iran and aggressive actions abroad.
This war is not only about Israel. It is a combat waged with our allies to protect our shared values and the freedoms we hold so dear.

Jewish history is the story of prevailing, of a people that overcomes obstacles and challenges against all odds. The age-old longing to return to the Jewish homeland, as expressed every Passover with the words “Next year in Jerusalem," inspired generation after generation with the dream of becoming again a free people in the Land of Israel.
Alongside freedom, Passover bears a powerful message of resilience and optimism. This year too, despite the present situation, we will be strengthened by our heritage and will look forward towards the future with faith and hope.

Israel must fight to protect its citizens and their liberty against murderous aggressors. However, we will not abandon the struggle to live in peace and coexistence with other peoples of goodwill in our region.

May the festivals of Passover and Fasika bring Israel and Ethiopia – our countries and peoples – many blessings of health, peace and prosperity.

በባሮክ ኢቨንት ኦርጋናይዘር አ.ማ የተዘጋጀው የፋሲካ ባዛርና ኤክስፖ ቅዳሜ ሚያዝያ 12 ቀን 2016 ዓ.ም ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ባለሃብቶችና ታዋቂ ግለሰቦች በተገኙበት በሚሊኒየም አዳራሽ በይፋ ተከፈተ፡፡

የፋሲካ ባዛርና ኤክስፖው እስከ ሚያዝያ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ለጎብኚዎች ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ ታውቋል፡፡

በዚህ ባዛርና ኤክስፖ ሸማቹ የህብረተሰብ ክፍል በዓልን ምክንያት አድርጎ ከሚገጥመው የዋጋ ንረት በተመጣጣኝና በቅናሽ ዋጋ ከራሱ ከአምራችና አስመጪው የሚገበያይበት ሲሆን፤ አምራችና ሸማቹም ከፍተኛ የገበያ ሽያጭ በማግኘት ተጠቃሚ የሚሆንበት ነው ተብሏል፡፡

ከተከፈተ 17ኛ ዓመቱን ያስቆጠረውና እስካሁን ከ3ሺ800 በላይ የፋሽን ዲዛይነሮችን አሰልጥኖ ያስመረቀው ኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ ፤ አዲሱን የማስተር ክላስ ሥልጠናውን ቅዳሜ ምሽት ሚያዝያ 12 ቀን 2016 ዓ.ም ቦሌ ዩጎ ሰርች አጠገብ በሚገኘው ሪያሊቲ ፕላዛ ህንጻ ላይ በይፋ መጀመሩን አስታወቀ፡፡

የፋሽን ማስተር ክላስ ከሚሰጣቸው ሥልጠናዎች መካከል፡- ስፔሻል ፓተርን ዲዛይን፣ አርት ድሮዊንግ፣ ፋብሪክ ፔይንቲንግ፣ ፋሽን ስታይሊንግ፣ 3ዲ ዲዛይን፣ ፋሽን ማኔጅመንትና ሌሎችም ይገኙበታል ተብሏል፡፡

የኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ መሥራችና ባለቤት ወ/ሮ ሣራ መሃመድ በምሽቱ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ “ማስተሪንግ ክላስ ሰዎች እንደ መክሊታቸው (ተሰጥኦዋቸው) ሥልጠና የሚያገኙበት ፕሮግራም ነው” ብለዋል፡፡



በምሽቱ በኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ ተመራቂዎች የተዘጋጀ ለየት ያለ የፋሽን ትርኢት ለታዳሚዎች ቀርቧል፡፡

ኮሌጁ ከዓለማቀፍ ተመሳሳይ የማሰልጠኛ ተቋማት ጋር በፈጠረው መልካም የሥራ ግንኙነት 42 ዲዛይነሮች በህንድ አገር ሙሉ የነጻ ትምህርት እንዲያገኙ በማድረግ ሥልጠናቸውን ተከታትለው በመመለስ ለኢንዱስትሪውና ለአገራቸው ትልቅ አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡

ኮሌጁ ባለፉት ዓመታት  ከሥልጠናው ጎን ለጎን የተለያዩ የፋሽን ትርኢቶችን ከአገር ውስጥ ባሻገር በኒውዮርክ፣ ፈረንሳይ፣ ጣልያን፣ ጀርመን፣ ስዊዘርላንድ፣ ኡጋንዳና ሌሎች አገራትም ማቅረቡ ታውቋል፡፡
ኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ የማስተር ክላስ ስልጠናውን በይፋ ጀመረ

ከተከፈተ 17ኛ ዓመቱን ያስቆጠረውና እስካሁን ከ3ሺ800 በላይ የፋሽን ዲዛይነሮችን አሰልጥኖ ያስመረቀው ኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ ፤ አዲሱን የማስተር ክላስ ሥልጠናውን ቅዳሜ ምሽት ሚያዝያ 12 ቀን 2016 ዓ.ም ቦሌ ዩጎ ሰርች አጠገብ በሚገኘው ሪያሊቲ ፕላዛ ህንጻ ላይ በይፋ መጀመሩን አስታወቀ፡፡

የፋሽን ማስተር ክላስ ከሚሰጣቸው ሥልጠናዎች መካከል፡- ስፔሻል ፓተርን ዲዛይን፣ አርት ድሮዊንግ፣ ፋብሪክ ፔይንቲንግ፣ ፋሽን ስታይሊንግ፣ 3ዲ ዲዛይን፣ ፋሽን ማኔጅመንትና ሌሎችም ይገኙበታል ተብሏል፡፡

የኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ መሥራችና ባለቤት ወ/ሮ ሣራ መሃመድ በምሽቱ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ “ማስተሪንግ ክላስ ሰዎች እንደ መክሊታቸው (ተሰጥኦዋቸው) ሥልጠና የሚያገኙበት ፕሮግራም ነው” ብለዋል፡፡

በምሽቱ በኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ ተመራቂዎች የተዘጋጀ ለየት ያለ የፋሽን ትርኢት ለታዳሚዎች ቀርቧል፡፡

ኮሌጁ ከዓለማቀፍ ተመሳሳይ የማሰልጠኛ ተቋማት ጋር በፈጠረው መልካም የሥራ ግንኙነት 42 ዲዛይነሮች በህንድ አገር ሙሉ የነጻ ትምህርት እንዲያገኙ በማድረግ ሥልጠናቸውን ተከታትለው በመመለስ ለኢንዱስትሪውና ለአገራቸው ትልቅ አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡

ኮሌጁ ባለፉት ዓመታት  ከሥልጠናው ጎን ለጎን የተለያዩ የፋሽን ትርኢቶችን ከአገር ውስጥ ባሻገር በኒውዮርክ፣ ፈረንሳይ፣ ጣልያን፣ ጀርመን፣ ስዊዘርላንድ፣ ኡጋንዳና ሌሎች አገራትም ማቅረቡ ታውቋል፡፡

አሜሪካ በእርስ በርስ ጦርነቱ ወቅት ያጣችው የሰው ሕይወትና ሀብት የትየለሌ ነው። በዘመኑ የነበረው አብረሃም ሊንከን፣ ለአሜሪካ ዳግም ሀገር መሆን የከፈለው ዋጋና የፈሰሰው የዜጎች ደም ቀላል አይደለም።

የኋላ ኋላ ጦርነቱ አብቅቶ፣ችግር በሰማዩ ላይ ካረበበ በኋላም የመከራው ገፈት ቀማሽ ሕዝቡ ነው። ሠራተኛ ከሥራ ሲቀነስ፣ወታደር ወደቤተሰቡ ሲመለስ፣ብዙ ቤተሰብ ወላጅና ልጆቹን ሲያጣ፣የጨለማው ድባብ፣የሐዘኑ

ምሬት ሀገሪቱን ሲዖል አድርጓት ነበር።
እውነት ነው፤ በጦርነቱ የአንድነት ኀይሉ አሸንፏል። የደቡቡ ወገን የሮበርት ሊ ጦር ተሸንፏል። ዩሊሰስ ግራንት ሲማርክ፣ሮበርት ሊ ከእነ ጦሩ ተማርኳል። ከጦርነቱ በኋላ ደብዛው ጠፍቶ የቆየው ጀኔራል ሸርማን፣

ዐሳውን ለማጥመድ ባሕሩን ብሎ አትላንታን በከባድ ምት ቢመታም፤የአትላንታ ቁስልና ጠባሳ፣መልሶ የአሜሪካ ነው። የገደለው ባልሽ የሞተው ወንድምሽ፣ሐዘንሽ ቅጥ አጣ፣ከቤትሽ አልወጣ ፤ነበር ነገሩ።
እውነት ለመናገር፣ከእርስ በርስ ጦርነት ይልቅ ከሌሎች ሀገራት ጋር የሚደረጉ ጦርነቶች ቀላል ናቸው። ለዚህ ደግሞ ማሳያዋ ራሷ አሜሪካ ናት። ለምሳሌ በዐለም ላይ ካደረገቻቸው ጦርነቶች ይልቅ የበርካታ ሰዎች

ሕይወት ያለፈው በእርስ በርስ ጦርነቱ ነው። በንጽጽር እንይ ከተባለ፣
በኮሪያ ጦርነት -  54,000
በቬትናም -  58,000
በሁለተኛው የዐለም ጦርነት-  400,000
በአንደኛው የዐለም ጦርነት-  117,000
በእርስ በርሱ ጦርነት - 620,000
የዜጎች ሕይወት ጠፍቷል።
ከዚህ በተጨማሪ፣  የደረሰው የኢኮኖሚ ቀውስ ቀላል አይደለም። ይህ ቀውስ የሚለካው ለጦርነቱ በወጣው ወጭና በጦርነቱ በወደሙት ንብረቶች ብቻ ከሆነ ግምታችን የተሳሳተ ነው። በጦርነቱ የሚያልቁት ወጣቶች

ጭንቅላትና አቅም፣ በገንዘብ የማይተመን ተዐምር ሠሪ ሀብት ነው።
ቅድም ካነሳነው የአሜሪካ ጦርነት ጀርባ፣ተገኘ ከሚባለው ድል በስተኋላ፣በርካታ የአሜሪካ እናቶች አልቅሰዋል። ኁልቁ መሳፍርት የሌላቸው  የሠርግ ሳይሆን የልቅሶ ድንኳኖች በየደጁ ተጥለዋል። በዚህ በተጣሉት የልቅሶ

ድንኳኖች ሳቢያ እንባ እንደጎርፍ ያፈሰሱት ጥቂት አይደሉም።
በተለይ በአሜሪካ ታሪክ ለሊንከን አድናቆት ያጎረፈለት አንድ ያልተለመደ ነገር ነበር። ያም አምስት ልጆቿን ላጣችው እናት በራሱ እጅ የማጽናኛ ደብዳቤ መጻፉ ነው። የሚገርም ነው። የአንዲት ታላቅ ሀገር

ፕሬዚደንት እስከመኖሯም ለማትታወቅ አንዲት መናጢ ደኻ እናት፣ ደብዳቤ መጻፉ ጉድ ያስብላል። ይሁን እንጂ በምንም ሁኔታ ላይመለሱ የተቀጠፉትን የሕይወቷን ተስፋዎች አይመልስልትም። ለሊንከን ታላቅ

የፖለቲካ ድል ነው፤ለእናትየው ግን የማይጠገን ስብራት ነው።
ጦርነቱ በድል ተጠናቅቆ ሲያበቃ፣በደማቁ ድል ማግስት ወደ ጎተራ የሚገባ አንድ ኩንታል እህል የለም። የሚለቀመው አጥንት ነው። የሚተርፈው ጸጸት ነው። የዚህ ዐይነት በርካታ ጦርነቶች አልፈዋል። እናቶች ልጆቻቸው

እንደ ችቦ እጅብ ብለው እየዘፈኑ ሄደው፣ላይመለሱ ነድደው ሲቀሩ፣ወገባቸውን አሥረው በእንባ ሲታጠቡ ማየት የሕዝቦች ዕጣ ነው። በነዚያ በነደዱት ወጣቶች ብርሃን ሀገር አትደምቅም፤ከአድማሱ ላይ ጨለማ

አይወገድም። እንደገና ሌላ ወጣት ይገበራል። አንዳንድ ሀገራት የዚህ ዐይነት ጦርነቶች እንዳይደገም፣ዳናቸውም ወደሚቀጥለው ትውልድ እንዳያልፍ፣ ከዚያችው ቀን ጀምረው መስመር ያበጃሉ። ለዚያ ሰቀቀን ሥዕል

ያበጁለታል፤ትዕይንቱ እንዳይደገም መሰመር ያሠምራሉ። አንዳንዶች ግን እንደ መዝሙር ያዜሙታል፤እንደ ውበት ይተርኩታል።
ቁስሉን እንደ ንቅሳት፣ሕመሙን እንደ ምቾት ያቀነቅኑታል።...የወንድ ልጅ እናት ታጠቂ በገመድ፣ልጅሽን አሞራ እንጂ አይቀብረውም ዘመድ፤ እያሉ እናት ወልዳ ለፍሬ ሳይሆን፣ወልዳ ለአሞራ መስጠት እንዳለባት

ይነገራታል። ወይም በሌላ ዜማ፣”መላኩ ተፈራ፣
የእግዜር ታናሽ ወንድም፣የዛሬን ማርልኝ
ዳግም ወንድ አልወልድም” ይባላል።
የጀግና እናት እንባ የሌላት ቋንጣ ሆና እየነደደች ትኖራለች። በአንድ ጦርነት ውስጥ እናት ብቻ ሳትሆን እናት ሀገርም ብዙ የተስፋ ቡቃያዎቿን ታጣለች። ጠመንጃ ይዘው በየፈፋው የወደቁ ልጆቿ መልክ ቢፈተሽ፣ብዙ

ሳይንቲስቶች፣ሺህ መሐንዲሶች፣ተመራማሪዎች፣ወዘተ ይኖራሉ። ይህን ለማየት በዐለማችን ላይ ከተደረጉ ጦርነቶች የተረፉና በኋላ የታላላቅ ግኝቶችና ውጤቶች ባለቤት የሆኑ ሰዎችን ማየት በቂ ነው።እንግዲህ እነዚህ

ትሩፋን ከሞት አፍ ስለወጡ ያንን ሠሩ እንጂ አብረዋቸው ወድቀው የቀሩት ምን ሊሠሩ ይችሉ እንደነበር የሚገምት የለም። ብቻ በድኑ ያምማል።
ታዲያ እነዚያ ሁሉ ወደ ተሰጥዖና ክሎታቸው ሳይደርሱ እሳት በልቶ ዐመድ ያደርጋቸዋል። ወጣቶች በጦርነት ውስጥ ሲማገዱ፣ያልተፈለፈሉ እንቁላሎች ናቸው። ገና ፍሬያቸው ሳይታይ፣ቀናየውን ሳያገኙ ከንቱ ሆነው

ይቀራሉ። ይህ በሰው ልጆች ታሪክ አሳዛኙ ትራጀዲ ነው።
ጦርነት አንዳንዴ ፈጣን ፈውስ፣ወሳኝ መፍትሔ ሊሆን ይችላል። ሰው በገዛ ሀገሩ በነፃነት እንዳይኖር፣ቀንበር ጫንቃው ላይ ሊጭኑበት “አጎንብስልኝ”ሲሉት፣ተቆጥቶ ከሺህ ቀን ባርነት የአንድ ቀን ነፃነት ሲል፣ያኔ “አንዱን

ወንድ እንደሺህ...መመረቅ ግድ ይላል። ሠፈር ተቀምጦ የሚያውደለድል፣ጦር ግንባር ሄዶ ጠላቱን አምሶ ሲያልፍ፣ የጀግና ዘፈን ይዘፈንለታል እንጂ ደረት ተጥሎ አይለቀስም። ጭካኔውም እንደ ርኅራኄ ይታያል።
በጀመርናት ኀያል ሀገር መሪ በትሩማን ገጠመኝ ሰው መግደል፣ ማረፍና ማሳረፍ የሚሆንበትን አጋጣሚ እንይ። ከዕለታት በአንዱ ቀን የ18ኛው ፕሬዚደንት የዩሊሰስ ግራንት ሴቶች ልጆች ትሩማን ቤት ይገኙና ሁሌ

የሚገርማቸውን ጥያቄ ይጠይቋቸዋል።
“ለመሆኑ ሒሮሽማና ናጋሳኪ ላይ ቦምብ ያስጣሉ ቀን እንቅልፍ ወሰደዎት?”
ሲሏቸው፣ መልሳቸው የሚያስደነግጥ ነበር።
“በጣም ኀይለኛ እንቅልፍ ነበር የወሰደኝ” አሉ።
”እንዴት በሰዎች ላይ ያንን ሁሉ እሳት አዝንበው፣ እንቅልፍ ሊወስዳቸው ቻለ?”ብለን መጠየቃችን አይቀርም። ይሁን እንጂ ጉዳዩ ሲፈተሽ፣የጦርነቱ መንሥዔና ዓላማ ሌሎችን ዕረፍት ለመንሳት ኂትለር የጠነሰሰው

ስለነበር፣ሌሎቹ የሚዋጉት ለህዝባቸው ሕልውናና ለሀገራቸው ሉዐላዊነት ስለነበር፣ጦርነቱን በድል ደምድሞ ከዚያ አንገፍጋፊ ስቃይ መውጣት ያስፈልግ ነበር።
ጦርነቱን ያለማሸነፍ ደግሞ የሚያስከትለው ፍዳ እንቅልፍ አይሰጥም። ይሁን እንጂ ጦርነትን ከሚያዝዘው በላይ ጦርነቱ ላይ በቀጥታ የተሳተፈው ወታደር የተለየ ስሜት ሊፈጠርበት ይችላል። በዚያው ጦርነት

የመጀመሪያውን ጄት ያበረረው ምክትል የመቶ አለቃ፣በሕይወቱ ላይ የተፈጠረው ቀውስ ሌላ ነበር። ያ ወጣት መኮንን ቦምቡን ሲጥል፣ የተጣለበት የከተማዋ ነዋሪዎች የጮኹት ጩኸት በእዝነ-ልቡናው

እየተሰማው፣ምስላቸው በዐይነ ሕሊናው እየታየው እንቅልፍ እምቢ አለው። ምንም ዐይነት ሱስ ያልነበረበት ሰው፣ሲጋራ ማጤስ፣መጠጥ መጠጣት ጀመረ። ጦርነት መልኩ ብቻ ሳይሆን ውጤቱም ልዩ ልዩ ነው።

ከጦርነቱ ዳር የሚያጋፍረውና ውስጥ ሆኖ የሚፋለመው የስሜት ድንበራቸው ይለያያል።
በአሜሪካው የእርስ በርስ ጦርነት ከግማሽ ሚሊየን በላይ ሕዝብ አልቆ፣ቁጥር ስፍር የሌለው ውድመት ደርሶ መጨረሻ ላይ የሁለቱ ወገን የጦር አዛዦች ሲገናኙ፣ ስለቀደመውና በሜክሲኮ ጦርነት አብረው በነበሩበት

ጊዜ ስለሠሩት የሼክስፒር ቴአትር ማውራት ጀምረው ነበር። የዚያ ሁሉ ሰው ደም መፍሰስ ከኪሳራና እልቂት ውጭ አንዳች ጥቅም የለውም። በምንም መንገድ ቢሰላ፣በየቱም አቅጣጫ ቢተነተን፣ ከኪሳራ የተለየ

ውጤት ሊያመጣ አይችልም።
የአሜሪካው ልዩነት ግን ያንን ጦርነት፣ “ጠባሳን ያየ በእሳት አይጫወትም” ማለታቸው ነው።
ለሀገራቸው ጥቅም ብለው እስካሁን ሲዋጉ እንኳ፣በገዛ ምድራቸው ሳይሆን በሌሎች ሀገራት ነው። እኛ ግን ዘመናችንን ሁሉ በጦርነት የፈጀን፣ጦርነት መዋጋት ብቻ ሳይሆን፣መፍጠር እንችላለን ብለን

የምንመጻደቅ፣ውርደትን እንደ ክብር የምንቆጥር ነን። ጀግና ብለን የምንዘፍንላቸውና ስማቸውን የምናነሳቸው እንኳ ጦር ሜዳ የዋሉ፣የውጭ ጠላት ብቻ ሳይሆን ወገናቸውን የገደሉትን ነው።
አሳዛኙ ነገር ብዙ ጊዜ ከፈረንጅ ብድር የምንወስደው፣ፋብሪካ ለመገንባት፣እርሻ ለማስፋፋት አይደለም፤ለመገዳደል ነው። የሥልጣን ውርርሳችንም ሁሌም በሚባል ደረጃ በጠመንጃና በኀይል ስለሆነ፣ከጥንት ጀምሮ በአንድ

እጃችን ጠመንጃ፣በሌላኛው ዳቦ ስንለምን እንኖራለን። የተፈጠርነው ለጦርነት እስኪመስል ድረስ ጭር ሲል አንወድድም፤በየትውልዱ የጦርነት እሳቶች ይነድዳሉ፤ወጣቶች እንደችቦ እሳት ውስጥ ገብተው ይነድዳሉ።

ወልዶ፣አሳድጎ ለእሳት መቀለብ ብርቃችን አይደለም። ወንድምን ገድሎ መፎከር እንደ እርም አይቆጠርም። በቀደሙት አባቶቻችን ዘመን እንደሚሰማው፣ልጃገረዷ ወፍጮ ላይ ሆና እህሉን እየሸረከተች፣ግጥም

ስትገጥም፣ዜማ ስታንቆረቁር ወንዱ ፈረሱን ጭኖ ለግድያ ይወጣል። ወይ ይገድላል፤አሊያም ይሞታል። በቅርቡ ዘመን ደግሞ ዘመናዊው ኪነት ጦር ግንባር ድረስ ሄዶ “ወደፊት በሉለት፣ይለይለት”ይላል።
ይህ በራሱ ሀገር ለማዳን ሲሆን ችግር የለበትም፤ምርጫ ሲጠፋ ሀገር መፍረስ አይገባትም። ግን ከጦርነት ሌላ ምርጫ የለም ወይ?...ችግሮችን ለመፍታት ተሞክሮ ካልተሳካ በስተቀር፣እርቅን ገፍተው ካልመጡብን

ለምን እንጋደላለን?...ለምን ገንዘባችን ይባክናል?..ሥራ አጦችን ጦር ሜዳ ወስደን ከምንማግድ፣ለምን ጠመንጃና መድፍ በምንገዛበት ብር ፋብሪካ አናቋቁምም?...እኛ ዕድገት አያስፈልገንም?...ጥሩ

ኑሮ፣ጥሩ ሕይወት አይገባንም?...በሳይንስና ቴክኖሎጂ፣በጥናትና በምርምር ከዐለም ሕዝቦች ጋር እኩል እንዳንራመድ ማን ከለከለን? ገንዘባችንስ ለልማት የሚውለው መቼ ነው?..አንጀታችንን አሥረን መልማት

ሲገባን፣አንጀታችንን አሥረን ከጠገበ ፈረንጅ መሳሪያ በመግዛት ኪሱን የምናሳብጠው እስከ መቼ ነው?
ፕሮፌሰር መስፍን፤ ስለ እኛ ጦርነት ወዳድነት እንዲህ ሲሉ ጽፈው ነበር፤
“...ጦርነትን፥ጀግንነትንና ገዳይነትን እንደ ትልቅ የክብርና የማዕረግ ምንጭ አድርጎ የሚመለከት ሕዝብ ታሪክ፤ በአጠቃላይ የጦርነት ታሪክ ቢሆን የሚያስደንቅ አይደለም። ሌላው ትልቁና አስገራሚው ነገር፣ጦርነቶቹ

በአብዛኛው በውጭ ሰዎች ቁስቆሳ የተደረጉና የተጀመሩ መሆናቸው ነው። በተለይ ቅኝ ገዢዎች በየዐውደ-ውጊያው ያጡትን ድል በተለያዩ ስልቶች በመጠቀም ሊበታትኑን ሞክረዋል።
አንዳንዶቹ እንድንገነጣጠል፣ሌሎቹ እርስ በርስ እንድንዋጋና ሰላም እንድናጣ ሌት ተቀን ሠርተዋል። እኛም ማስተዋል ስላቃቸን ጦር መዝዘን ተላልቀናል። በተለይ በቅርብ ዐመታት የብሔር ብሔረሰቦችን መብት ታክኮ

የመጣው ጥላቻ፣ ከመቼውም ጊዜ ይልቅ ሀገራችንን አደጋ ላይ ጥሏታል። በደርግ ዘመን በሕወሓት የሚመራው ኀይል አምፆ በተደረገው የዐሥራ ሰባት ዐመታት ጦርነት፣ የጠፋው የሰው ሕይወትና የባከነው ሀብት

ለልማት ቢውል ኖሮ ምን ያህል መራመድ እንችል እንደነበር መገመት አያዳግትም።
በወቅቱ ጭቆናን ተቃውሜያለሁ ያለው ደርግ፣ በተራው ጨቋኝ ሆኖ፣ዐማፅያን እግሩ ሥር ሲፈለፈሉ፣ከመደራደር ይልቅ በጠመንጃ ብቻ መፍትሔ ለማምጣት አስቦ የማያቋርጥ ጦርነት ውስጥ ገብቷል።

በቀጣዩ፣ሥልጣን ላይ የወጣው ወያኔ መራሹ መንግሥትም ከደርግ ስላልተማረ፣ወዲያውኑ ኦነግን ከመንግሥት መዋቅር በመንቀል የሴራ ፖለቲካውን ጀምሮ እርሱም በተራው እያሳደደ የሚገድለው አንድ ጠላት አዘጋጀ።

...እናም ተራራና ሜዳው ባሩድ ማሸተቱን፣ደም መጠጣቱን ቀጠለ። በምሥራቅ ኢትዮጵያም በተመሳሳይ ሌላ ተቃዋሚ ተፈጥሮ የተለመደው ደም የመፋሰስ መንገድ ቀጠለ።
በምሥራቅ ኢትዮጵያም በተመሳሳይ ሌላ ተቃዋሚ ተፈጥሮ የተለመደው ደም የመፋሰስ መንገድ ቀጠለ። ከዚያም በኋላ ሀገራችን ከጦርነት አላረፈችም። ከጦርነት የሚገኝ ምንም ትርፍ ያለመኖሩን እያወቅን እንኳ

ከጦርነት አንወጣም። እንደ ኅበረተሰብ እልኸኞችና ዳተኞች ስለሆንን፣ ነገሮችን በይቅርታና በእርቅ መፍታት አይሆንልንም። ስለዚህ በቅርብ ዐመታት እንኳ በሰሜን ኢትዮጵያ ዘግናኝ የሆነ ጦርነት አካሂደናል። ይሁንና

ከጦርነቱ ማግስት የሰበሰብነው ሬሳ እንጂ ሀብት አይደለም። ያፈራነው አካል ጉዳተኝነት፣ጉሥቁልናና ረሀብ እንጂ ጥጋብና ፍስሃ አይደለም።
ወያኔም ሆነ የመንግሥት ሠራዊት ያወደሙትን  ሀብትና ንብረት፣ መልሰን የምንተካው እኛው ራሳችን ነን። ትግራይ ውስጥ ትምህርት ቤቶች መቃጠላቸው ኪሳራው ዞሮ የሚያንኳኳው የኛኑ ቤት ነው። አማራ ክልል

የፈራረሱት ተቋማት፣ የትግራይንም ክልል ይጎዳሉ። እኛ ያፈረስነውን የምንገነባው ራሳችን እንጂ ሌላ ማንም አጥደለም፡፡  ዳቦ ስንለምን የምንለምነው ሁላችንም ነን።
ትናንት፣ከትናንት ወዲያ፣ዛሬም ጦርነት ውስጥ ነን። እረፍት ኖሮን አያውቅም፤ብራችን ለልማት አልዋለም።ቁስላችን አልደረቀም፤እንባችን አልታበሰም፤እልሀችን አልተነፈሰም። ታዲያ ጦርነት ጥቅሙ፣ሞትና ድኽነት

ከሆነ፣ለምን ምክክርና ውይይትን፣ሰላምና ይቅርታን ለምን አንሞክርም?...ምድራችን ከደም ለምን አታርፍም?...ለመሆኑ ሰው ዐይኑ እያየ፣ለኪሳራ ይነግዳል?...ኧረ ይህን ያደፈ ታሪክ፣በቃ የሚል ጎበዝ፣ጦርነትን

የሚንቅ ጀግና እንፍጠር!
ከአዘጋጁ፡-
ደራሲና ሃያሲ ደረጀ በላይነህ፣ ላለፉት በርካታ ዓመታት በዚሁ ጋዜጣ ላይ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ አያሌ መጣጥፎችን አስነብቧል፡፡ በርካታ የሥነጽሁፍ ሥራዎች ላይ ሂሳዊ ትንተና አቅርቧል፡፡ ደረጀ በላይነህ

ገጣሚና አርታኢም ነው፡፡ 12 ያህል መጻሕፍትን አሳትሞ  ለአንባቢያን አድርሷል፡፡

የመጨረሻ አመት የኮሌጅ ተማሪ ነበርኩ፡፡ ለገና ወደ ቤተሰቦቼ ዘንድ ስሄድ ከሁለት ወንድሞቼ ጋር አስደሳች ጊዜ እንደማሳልፍ ጠብቄአለሁ፡፡ ሦስት ወንድማማቾች በመገናኘታችን ደስታችን ወደር የለሽ ነበር፡፡ አባትና

እናታችን በስራ ተወጥረው ለዓመታት ተዝናንተው አያውቁም፡፡
ስለዚህ እኛ መደብሩን ለመጠበቅ ተስማማንና ለጥቂት ጊዜ ወጣ ብለው እንዲዝናኑ ነገርናቸው፡፡ ሁለቱም አልተቃወሙም፡፡ ወደ ቦስተን ለመጓዝ ሻንጣቸውን መሸከፍ ያዙ፡፡
ከጉዟቸው አንድ ቀን በፊት አባቴ እጄን ይዞ በቀስታ ከመደብሩ ኋላ ወዳለችው ማረፍያ ክፍል ወሰደኝ፡፡ ክፍሏ ጠባብ ናት - አንድ ፒያኖና ታጣፊ አልጋ ብቻ ነው የያዘችው፡፡
በእርግጥ አልጋው ሲዘረጋ ክፍሉ ይሞላል፡፡ አልጋው ግርጌ ተቀምጦ ፒያኖ ከመጫወት በቀር አያፈናፍንም፡፡ አባቴ ከአሮጌው ፒያኖ ጀርባ እጁን ሰደደና ትንሽዬ ሳጥን ጐትቶ አወጣ፡፡
ከዚያም ሳጥኑን ከፍቶ አሳየኝ፡፡ ተከርክመው የወጡ የጋዜጣ ፅሁፎች ናቸው፡፡ በመገረም አፌን ከፍቼ ፅሁፎቹን እመለከት ጀመር፡፡ ብዙዎቹን የናንሲ ድሪው የወንጀል ምርመራ ታሪኮች አንብቤአቸዋለሁ፡፡ እዚያ ሳጥን

ውስጥ የተቀመጡበት ምክንያት ግን አልገባኝም፡፡
“ምንድናቸው?” አልኩት፤ አባቴን ቀና ብዬ እያየሁት፡፡
“እኔ የፃፍኳቸው ታሪኮች ናቸው፤ ለአዘጋጁ የፃፍኳቸውም ደብዳቤዎች አሉበት” ሲል መለሰልኝ፤ ኮስተር ብሎ፡፡
አባቴ እያፌዘ እንዳልሆነ ከድምፁ ቃና ተረድቼአለሁ፡፡ በመገረምና ግራ በመጋባት መሃል ሆኜ ጋዜጦቹን ሳገላብጥ፣ ከእያንዳንዱ ፅሁፍ ሥር “ዋልተር ቻፕማን ኢኤስ ኪው” ተብሎ የተፃፈውን አየሁት - የአባቴ

እውነተኛ ስም ነው፡፡ ሳላስበው ደሜ መሞቅ ጀምሯል፡፡ “ለምንድነው እስከ ዛሬ ያልነገርከኝ?”  ጠየቅሁት፤ ንዴቴን እንደምንም ተቆጣጥሬ፡፡
“እናትህ ስለማትፈልግ ነው”
“ምኑን?” ድምፄ መጮሁን ያወቅሁት ዘግይቼ ነው፡፡
አባቴ ድምፄን እንድቀንስ በምልክት ነገረኝና፣ አስገራሚውን ልቦለድ የሚመስል ታሪክ አወጋኝ፤ ዝግ ባለ የተረጋጋ ድምፅ፡፡
“እናትህ ጋዜጣ ላይ መፃፌን አትወደውም ነበር…”
“ለምን? ለምንድነው የማትወደው?”
አሁንም ድምፄን እንድቀንስ አሳሰበኝ፤ እናትህ ከሰማች ትገለናለች በሚል፡፡
“በቂ ትምህርት ስለሌለህ ባትሞክረው ይሻላል ብላ ደጋግማ አስጠንቅቃኛለች”
የእናቴ ነገር ገርሞኝ ጭንቅላቴን ስነቀንቅ አባቴ ቀጠለ፤
“አንድ ጊዜ በፖለቲካ ምርጫ ልወዳደር ፈልጌ ነበር… ይሄንንም ባትሞክረው ይሻልሃል አለችኝ”
“ቆይ ለምን?” አሁንም እንደ አዲስ ጠየቅሁት፡፡
“ተሸንፈህ ታዋርደናለህ.. ክብራችንን እንደጠበቅን ብንኖር ይሻላል አለችኝና ተውኩት” አለኝ፤ በቁጭት በታሸመ ቃና፡፡
እናቴን የማላውቃት ያህል ተሰማኝ፡፡ አባቴ አንጀቴን እየበላው፣ እሷ እያስጠላችኝ መጣች - በልቤ ውስጥ፡፡ ይሄን ያህል ጨካኝ እንደነበረች አላውቅም ነበር፡፡ በእጆቼ ላይ ካሉት የአባቴ መጣጥፎች አንደኛውን

ሳላውቀው ማንበብ ጀምሬ ነበር፡፡ በመሃላችን የነገሰውን ዝምታ የሰበርኩት ግን እኔው ነበርኩ፡፡ አይኖቼን ከጋዜጣው ፅሁፍ ላይ ነቅዬ አባቴን ቀና ብዬ እያየሁ ጠየቅሁት፤
“ታዲያ ይሄ ሁሉ ፅሁፍ እንዴት ታተመ?”
“እስቲ ልሞክር ብዬ እሷ ሳታውቅ መፃፍ ጀመርኩ… እያንዳንዱ ፅሁፌ ጋዜጣው ላይ ሲወጣልኝ ከርክሜ አወጣውና እዚህች ሳጥን ውስጥ እደብቀዋለሁ… አንድ ቀን ሳጥኗን ለአንድ ሰው እንደማሳየው አውቅ ነበር”
“ለማን?” ሳላስበው ከአፌ ተስፈትልኮ የወጣ ጥያቄ ነው፡፡
“ላንተ ነዋ!” አለኝ፤ በእውነተኛ የአባትነት ፍቅር ትክ ብሎ እያየኝ፡፡ ዓይኖቼን ሰብሬ የጋዜጣው ፅሁፍ ላይ ተከልኳቸው፡፡ ሁለት ፅሁፎቹን አንብቤ እስክጨርስ አባቴ ቁጭ ብሎ እየተመለከተኝ ነበር፡፡
ቀና ብዬ ሳየው ትላልቅ ሰማያዊ ዓይኖቹ በእንባ እርሰዋል፡፡ መሃረቡን ከኪሱ ውስጥ አወጣና ዓይኖቹን ከጠራረገ በኋላ፤ “ባለፈው ጊዜ ያለ አቅሜ ትልቅ ነገር ሞከርኩ መሰለኝ ይኸው ሦስት ወሩ… አልወጣም”

አለኝ፤ በፈገግታ፡፡
“ሌላ ነገር ፅፈህ ነበር?” ጠየቅሁት፤ በጉጉት፡፡
“አዎ ብሄራዊ መራጭ ኮሚቴ እንዴት ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ሊመረጥ እንደሚችል አንዳንድ ሃሳቦችን ፅፌ ለሃይማኖታዊ መፅሄታችን ልኬ ነበር፤ ግን እስካሁን አልታተመም… ትንሽ ያለ አቅሜ ሳልንጠራራ

አልቀረሁም”
ይሄ ጉዳይ እኔ የማላውቀው የአባቴ አዲስ ገፅታ ቢሆንም፣ አንድ ነገር ማለት ነበረብኝ፡፡
“አይታወቅም … ሊወጣ ይችላል” አልኩት
“ምናልባት ይወጣ ይሆናል…
ግን አይመስለኝም”
ቁራጭ ፈገግታ እያሳየኝ የጋዜጣ ቁርጥራጮቹን ሳጥኑ ውስጥ ከቶ ዘጋባቸውና፣ ከፒያኖው ጀርባ ባለው ክፍት ቦታ መልሶ ወሸቀው፡፡
በነጋታው ወላጆቻችን በአውቶብስ ተሳፍረው ወደ ሃቨርሂል ዲፖት ሄዱ፡፡ እዚያ ሲደርሱ በባቡር ተሳፍረው ነው፣ ወደ ቦስተን የሚጓዙት፡፡ እኔና ሁለት ወንድሞቼ ፣ጂምና ሮን መደብሩ ውስጥ ስንሰራ ዋልን፡፡ ቀኑን

ሙሉ ስለ አባቴ ሳስብ ነበር፡፡
የአባቴን የጋዜጣ ፅሁፎች ደብቃ ስለያዘችው ትንሽዬ ሳጥንም ማሰላሰሌ አልቀረም፡፡ አባቴ መፃፍ እንደሚወድ ፈፅሞ አላውቅም ነበር፡፡ ስለዚህ ጉዳይ ለወንድሞቼ አልነገርኳቸውም፡፡
የአባቴና የእኔ ምስጢር ነዋ! የተደበቀችው ሳጥን ምስጢር!
የዚያኑ እለት ፀሃይ መጥለቂያዋ ላይ መደብር ውስጤ ቆሜ በመስኮት ስመለከት እናቴ ከአውቶብስ ስትወርድ አየኋት - ብቻዋን፡፡ አደባባዩን ተሻገረችና ጥድፍ ጥድፍ እያለች ወደ መደብሩ ገባች፡፡
“አባባስ?” ስንል በአንድ ድምፅ ጠየቅናት፡፡
“አባታችሁ ሞቷል” አለችን፤ አይኗ እንደደረቀ፡፡
ጆሮአችን የሰማውን በመጠራጠር ተከትለናት ወጥ ቤት ገባን፡፡ መሞቱ እውነት መሆኑን በደንብ አረጋገጥን፡፡ በፓርክ ስትሪት የምድር የውስጥ ለውስጥ ባቡር ጣቢያ በኩል ሲያልፉ ነው፣ ህዝብ መሃል አባታችን

ድንገት የወደቀው፡፡
አጐንብሳ ስትመለከተው የነበረችው ነርስ ወደ እናቴ እያየች፤ “ሞቷል!” አለቻት እንደዘበት፡፡
እናታችን በድንጋጤ እምታደርገው ጠፍቷት ዝም ብላ አጠገቡ ተገትራ ነበር፡፡ መንገደኞች ወደ ባቡር ጣቢያው ለመግባት ሲጣደፉ እየረጋገጡ አስቸገሯት፡፡ ለአንድ ሰዓት ያህል እግሯን አንፈራጣ የአባባን አስከሬን

ከመንገደኞች ስትከላከል ከቆየች በኋላ አምቡላንስ ደረሰ፡፡
እናታችንንና አስከሬኑን ይዞ በአካባቢው ወዳለው ብቸኛ የመቃብር ቤት ወሰዳቸው፡፡ ኪሱን ፈታትሻ ሰዓቱን አወለቀችለትና ባቡር ተሳፍራ ብቻዋን ወደ ቤት ተመለሰች፡፡
እናታችን ይሄን አስደንጋጭ ታሪክ የነገረችን አንዲትም እንባ ጠብ ሳታደርግ ነው፡፡
ሁሌም ቢሆን ስሜታዊ አለመሆን ለሷ የስርዓትና የክብር ጉዳይ ነው፡፡ እኛም ራሳችን እንድናለቅስ አልተፈቀደልንም፡፡ የመደብሩን ደንበኞች ተራ ገብተን ማስተናገድ ያዝን፡፡ አንድ የመደብሩ የዘወትር ደንበኛ መጣና፤
“ዛሬ ሽማግሌው የት ገባ?” አለኝ
“ሞተ” አልኩት “ኦው… በጣም አሳዛኝ ነው” ብሎ ሄደ፡፡
የደንበኛው አጠያየቅ አሳብዶኝ ነበር፡፡
 አባቴን እንደ ሽማግሌ አስቤው አላውቅም፡፡ በእርግጥ እሱ 70፣ እናቴ 60 ዓመቷ ነበር፡፡ ሁልጊዜም ጤናማና ደስተኛ ሆኖ ነው የኖረው፡፡ ጤና የሌላትን እናታችንን አንዴም ሳይነጫነጭ ተንከባክቧታል፡፡  አሁን ግን

“ሽማግሌው ሞቷል፡፡”
በነጋታው ቁጭ ብዬ ለቤተሰቡ የተላኩ የሀዘን መግለጫ ካርዶችን ከፖስታ ውስጥ እየከፈትኩ ስመለከት አንድ የቤተ ክርስትያን መፅሄት አየሁኝ፡፡ ሌላ ጊዜ ቢሆን የሃይማኖት መፅሄት ትኩረቴን አይስበውም ነበር፡፡

ምናልባት የአባቴ ፅሁፍ ወጥቶ እንደሆነ ለማየት፣ መፅሄቱን ማገላበጥ ያዝኩ፡፡ የአባቴ ፅሁፍ ታትሟል፡፡ መፅሄቱን ይዤ ወደ ትንሿ ክፍል ሹልክ ብዬ ገባሁና በሩን ቆልፌ ተንሰቅስቄ አለቀስኩ፡፡ እስከዚያች ቅፅበት

ድረስ ራሴን አጀግኜ ነበር፡፡ አባቴ የሰጠው ደፋር ሃሳብና ምክር መፅሄቱ ላይ ታትሞ ስመለከት ግን ከአቅሜ በላይ ሆነብኝ፡፡ ጽሁፉን አነብና አለቅሳለሁ፤ ከዛ ደግሞ አነባለሁ፡፡
ከፒያኖው ኋላ የተወሸቀችውን ሳጥን አውጥቼ በውስጡ ያሉትን ፅሁፎች ማገላበጥ ጀመርኩ፡፡ ሳገላብጥ ከሰር ካቦት ሎጅ የተፃፈለትን ባለ ሁለት ገፅ ደብዳቤ ተመለከትኩ፡፡ አባቴ ለጻፈው  የምርጫ ዘመቻ ሃሳብ

የተላከለት የምስጋና ደብዳቤ ነበር፡፡ እስካሁን ስለዚህች ሳጥን ምስጢር  ለማንም ሰው አውርቼ አላውቅም፡፡ ምስጢሩ የእኔና የአባቴ ነው፡፡
(በኢየብ ካሣ “Chicken Soup For The Soul” መፅሐፍ ላይ የተተረጎመ)

Saturday, 20 April 2024 12:41

ሥነ ቃላችን በጥቂቱ

እኛ ኢትዮጵያን እንደ ሌላ ሐብታችን ሁሉ ጥቂትም ቢሆን ያልተጠቀምንበት የሥነ ቃል ቅርሳችን ነው፡፡ ከ80 በላይ ብሔረሰብ እንዳለው አገር፤ የረዥም ዘመን ታሪክ ባለቤት ከመሆን አንፃር በርካታ ባህልና ትውፊት

እንዳለው አገር፣ ተዝቆ የማያልቀው የሥነ ቃል ሀብታችንን አልነካነውም፡፡ እንዲሁ ነገር ማጣፈጫ ከማድረግ ውጪ ብዙ አልሰራንበትም ፡፡
እንደ ሀገራችን ከፍታ፤ ውበትና ትንግርት፣ በሥነ ቃሉ ዘርፍ ብዙ አልገፋንም ፡፡ እያንዳንዱ ሐዘን ደስታችን ፤ዕድገት ውድቀታችን ፤ ማግኘት ማጣታችን ፤ እያንዳንዱ ክንውናችን የራሱ እሴትና መሠረት ያለው

መሆኑን፣ ለጥያቄ ለናሙና ያህል በማቅረባቸው ማሳያዎች ለማንበብ እሞክራለሁ፡፡
አንድ ማህበረሰብ የየዕለት ውሎውን፤የዘመናት ተግባሩን ፤ታሪካዊ እውነቱን በሥነ ቃል አማካኝነት ያስተላልፋል፡፡ ጥቃቅን ከሚመስሉ የዕለት ተዕለት ክስተቶች ተነስቶ ብዙ ማለት፤ ብዙ መፃፍ ይቻላል፡፡
ከ80 ብሔረሰብ በላይ ያላት አገር ማለት በሥነ ቃል ሐብቷ የበለጸገች ናት ማለት መሆኑን  አያጠራጥርም፡፡ ሥነ ቃሎች በበርካታ ሥፍራዎች በተመሳሳይነት ፤በቅርጽ ግን በልዩነት ልንመለከታቸው ወይም

ሊያጋጥሙን ይችላሉ፡፡ ማህበረሰባችን ለእያንዳንዱ ተግባር ሥነ ቃሉን ይጠቀማል፡፡ በአመጽ፤ በእርሻ፤ ፤በጦርነት፤ በሰላም፤ በሠርግ በለቅሶው….፡፡ በምሳሌ እያስደገፍን ለማቅረብ እንሞክር ፡፡ ሥነ ቃሎች

ከሚተላለፍባቸው መካከል ተረት፤አፈ ታሪክ ፤ሀተታ ተፈጥሮ፤ምሳሊያዊ አነጋገር፤ እንቆቅልሽ፤የሥራ ዘፈኖች፤ የክብረበዓል ዘፈኖች እና የልጆች ጨዋታዎች ይገኙበታል፡፡ ከእነዚህ የሥነ ቃል ምንጮች ምን ያህል ክፍሎችና

ዘርፎች፣ በአካባቢያችሁ  አስተዋውቃችኋል ብለን ብንጠይቅ፣ ገና ብዙ እንደሚቀረን መረዳት ይቻላል፡፡
የየክልልና የዞን ባህልና ቱሪዝም ቢሮዎች መሥራት የሚገባቸውን ትተው በሌላ እሴት በማይጨምሩ ተግባራት ተጠምደው ይውላሉ፡፡ ሥነ ቃሎቻችን አይደለም ለክልል ለሀገር፤ከሀገርም በላይ ለአህጉርና ለዓለም

አደባባይ ማዋል እንችላለን፡፡
በሥነ ቃሎቻችን መውደቅ መነሳታችን ፤ ማግኘት ማጣታችን ፤ደስታ ሀዘናችን፤ታሪክ ድርጊታችንን ማሳየት፤ ማስተማር እንችላለን፡፡ በመጸሐፍ ፤ በፊልም፤ በዘፈኖች አካትተን፣ በማቅረብ እንደ ማጣፈጫ መጠቀም

እንችላለን፡
እስኪ ዘወትር በንግግራችንና በጽሑፋችን ከምንጠቀምበት የሥነ ቃል ዘርፎች አንዱ በሆነው ምሳሌያዊ አነጋገር እንጀምር፡፡ ብዙም የማይዘወተሩትን ለማሳያት ያህል፡-
ተስካር ያየ ተማሪ ሸቀጥ ያየ አጣሪ
ዝንብ ቢጠራቀም
ጠጉራም ውሻ አለ ሲሉት በራብ ይሞታል
ፈላጻ በአየር ውስጥ አልፎ ፍለጋ አይተውም
ለቀንዳም በሬ ቤት አትከልክለው፤ ቀንዱ ይከለክለዋል
ለመከራ የጻፈው ቢነግድም አያተርፍም
በሰም የተጣበቀ ጥርስ ቢስቁበት አይደምቅ፤ቢበሉበት
ሰው ሆኖ የማይበላ፣ እንጨት ሆኖ የማይጨስ
ብረት ካልፈላ አይላላ
ደም ማልቀስ ድንጋይ መንከስ……..
ተባባሪ ፕሮፌሰር ዘሪሁን አሰፋ፣ ነፍስን ይማርና፣ በጻፈው የሥነ ጽሑፍ መሰረታዊያን መጸሐፍ ገጽ 33 ላይ  ምሣሌያዊ አነጋገር ሲገልጽ፤ ሀ ምሳሌ አነጋገሮች በውስጣቸው አምቀው የያዟቸው ሃሳቦች፣ ከማህበረሰቡ

የዕለት ተዕለት ኑሮ ገጠመኝና  ምልከታ የተገኘ ሲሆኑ፤  ማህበረሰቡ የሚያምንባቸውና ታዋቂነታቸውን ያረጋገጠላቸው የሃሳብ መግለጫዎች ናቸው >> ይላል፡፡
የምሳሊያዊ አነጋገርን ሚስጥር ለመረዳት የተነገረበትን አውድ በውሉ ማወቅ አስፈላጊነው፡
ሚስጥሩ የሚታወቅ    ፍችው በመሆኑ ከተነገረበት ሁኔታውም ለብቻው ተነጥሎ የሚሰጠው ትርጉም አንዱን አቅጣጫ ብቻ የሚያመለክት ይሆንል፡፡
እንደ ምሳሊያዊ አነጋገር ሁሉ ሌሎችም የሥነ ቃል ዘርፎች በምሳሌ እያስደገፍን፣
ሁለተኛው ምልከታችን እንቆቅልሽ ላይ ማድረግ እንችላለን፡፡ እንቆቅልሽ በተለይ (ታዳጊና) የልጆች አእምሮን ንቁ ለማድረግ ፤ግንዛቤያቸው እንዲሰፋ ፤እንዲመራመር ፣ እንዲተጉ፣ እግረ መንገዳቸውንም ሥርዓትና ደንብ

እንዲያውቁ ማድረጊያ ቅርስ ነው፡፡ በእንቆቅልሽ በጥያቄ ከመፈተኑ በተጨማሪ ለማዝናናት፤ሳቅ ለመማርም ይሆናል፡፡ ለምሌ ያህል ፡-
ለማታምነው ፊቷ ፡ ምራቅ ነው ቅባቷ - ድመት
ቡቱቶ ለባሽ - ሰውን ለማኖር የተፈጠረ - እንሰት
አልቀረም ተቀጥቅጦ - አስተኛችው ፈርጦ ፈርጦ - ጌሾ
ሺህ አይን አለው፤አጥንት የለውም - እንጀራ
ዓይንዋን ተኩላ ገበያ የምትወጣ - ባቄላ
ወገበ ጎባጣ ሁሉ ቆምጣ ቆምጣ - ማጭድ
ከመሬት ወድቄ አንስቼ ብይዘው አለቀ - በረዶ
እንቆቅልሽ ፤ተባባሪ ፕሮፌሰር ዘሪሁን፣ በመጽሐፍ በተለያየ ክፍሎች መድቦ አሳይቶናል፡፡ በሰው የአካል ክፍሎች ፡ በእንስሳት በተክሎች ፤ በምግብ አይነቶች ፤ በእህል አይነቶች፣ .በቤት ውስጥ ቁሳቁሶች፤ በሥራ

መሣሪያዎች በተፈጥሮ ገጽታዎች ከፋፍሎ ለንባብ አብቅቶልናል፡፡ የምወደው መምህሬ ዘሪሁንን አመሰግናለሁ፤ መሬቱ ይቅለልህ ከማለት ውጪ ምን ማለት ይቻለኛል፡፡
ለማሳያ ያህል ይህን  ካልኩ፣ በየክልሉና ዞን የሚገኙ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ቢሮዎች፣ ሥነ ቃላቶችን ለማሳደግ ፤አደባባይ ላይ ለማውጣት መትጋት እንደሚኖርባቸው ለማሳሰብ እወዳለሁ፤ በበርካታ የስራ ዘርፍ፤

ባህላዊ ዘፋኞች፣ የክብር በዓል ዘፋኞች፤ የልጆች ጫዎታዎች፤ መጣጣጥፎች፤ አፈ ታሪኮች ተረቶች ተሰብስበው ጥቅም ላይ ማዋል ይገባል፡፡ በዝባዝንኬ ጉዳይ ተጠምዶ ከመዋል ለሀገርም ለክልልም ሆነ ለዞን እሴት

የሚሆን  ሥራና  ባህል ላይ  ቢተኮር ተገቢ ይመስለኛል፡፡
(ጽሑፉን ለማደራጀት የተጠቀምኩት የመምህሬ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዘሪሁን አሰፋው መጸሐፍ.፤ “1የሥነ ጽሑፍ መሠረታውያን“ መሆኑን እየገለጽኩ እሰናበታለሁ፡፡)

“ሁሉንም ሞክሩ የተሻለውን ያዙ” የሚለውን አባባል ቢያንስ እስከ 1966 ዓ.ም ድረስ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርስቲ (የዛሬው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ) ገብቶ የተማረ ተማሪ ያውቀዋል። በየዲግሪው ላይ የተፃፈ

 መሪ ቃልና ጥቅስ ነው። በህይወታችን ውስጥ በርካታ ውጣ ውረዶች ይገጥሙናልና በየፈርጅ በየፈርጃቸው እየሞከርን፣ እየወደቅን እየተነሳን፣ በጎና ሰናይ የሆኑትን እየለየንና እያጠናከርን፣ የሚበጀንን መያዝ አለብን፤

ለማለትም ነው። በእርግጥም በእያንዳንዱ ሙከራ ወቅት፣ እንቅፋት፣ ችግርና መከራ መኖሩ አይቀሬ ነውም ለማለት ነው። ለዚህ አብነት ይሆነን ዘንድ የሚከተለውን የአበው ወግ እንይ።
ሁለት ደገኛ ገበሬዎች፤ ኑሮ አልገፋ ብሎ ቁም ስቅላቸውን ያሳያቸዋል። አንዴ ዝናቡ እምቢ ይላል። አንዴ በሬዎቹ ይለግማሉ። አንዴ ደቦ ወጪዎች አይመቻቸወም። አንዴ ደሞ ሰብሉን ተባይ ይፈጀዋል። በእጅጉ

ይቸገራሉ። አዝመራውም አልሰምር ይላል።
አንደኛው ገበሬ አንድ ቀን መላ ዘየደ። ንግድ መጀመር አለብኝ ብሎ ወሰነና አዲስ ሙከራ ጀመረ። በሬዎቹን ሁሉ ሸጠ። የዘር እህሉንም ከሰቀለበት አውርዶ፣ ለቤት የሚፈልገውን ያህል አስቀረና አውጥቶ ሸጠ።

ከዚያም ባገኘው ገንዘብ ወደ ቆላ ወርዶ ለማረሻ ለዶማና ለማጭድ ወዘተ መሥሪያ የሚሆን ብረታ ብረት ገዛ። የገዛውንም ብረታ ብረት ወስዶ ለአገሬው ደገኛ ህዝብ ቸበቸበው። ቀስ በቀስ ኑሮው ተለወጠ።

አዱኛም አገኘ። ለውጡ በቀዬውም በአገሩም ተወራ፤ ተሰማ። ሀብቱ ጣራ ነካ። ይጭነው አጋሰስ ይለጉመው ፈረስ በደጅ በግቢው ሞላለት።
“አያ፤ እንዲህ ባንዴ የሆንከው ምን ዘዴ ከውነህ ነው ጃል?” ብሎ ይጠይቀዋል።
ምን የዱሮ ገበሬ የዛሬ ነጋዴ፤ የተሰማራበትን ሙያ ያስረዳዋል። ወደዚህ ስራ ቢገባ፣ በቀላሉ ካብታም እንደሚሆን ይገልጸለታል።
ሁለተኛው ገበሬም፤ ሳይውል ሳያድር ምክሩን ተቀብሎ በስራ ላይ አዋለና፣ ያለ የሌለ ንብረቱን ወደ ገንዘብ ለወጠ። ንግድ ጀመረ።
ቆላ ወረደ። ያገሩን ብረታ ብረት ገዛ። ተሸከመናም ሽቅብ ወደ ደጋ መንገድ ጀመረ። ሆኖም፤ ገና ዳገቱን አጋምሶ ሳያበቃ በተሸከመው ብረታብረት ክብደት ሳቢያ፣ ወገቡንም ጉልበቱንም ከዳውና ተዝለፍልፎ ወደቀ።

አወዳደቁም አጉል ነበርና አረፋ አስደፈቀው።
አንድ መንገደኛ የሰፈር ሰው ድንገት ሲያልፍ  አይት ኖሮ ወደሱ ቀርቦ፤ “አያ እገሌ፤ምን ሆነህ ነው?” ሲል ይጠይቀዋል።
ገበሬውም፤ “ወይ ወዳጄ፤ ያ ጎረቤቱ አያ እገሌ የሠራኝን ሥራ ለጠላት አይስጥ!” አለና መለሰለት።
“ምን አደረገህ? የልብ ወዳጁ እማይደለህ እንዴ? በሞቴ ንገረኝ፤ ምን አደረገህ?”
“ትርፉን ነግሮ መከራውን ሳይነግረኝ፤ ይሄው ለዚህ ዳረገኝ!!” አለው።
***
ሁሉም ስራ ችግሩ የሚታወቀው ሲሞከር ነው። ንግዱ፣ ትምህርቱ፣ ልማቱ፣ አስተዳደሩ፣ ፓርላማዊ ሥነ-ስርዓቱ፣ ምርጫው፣ ፍትሐዊ ባህሉ ወዘተ--ሁሉም ተሞክሮ፣ ተሰርቶ ታይቶ ነው። ካላዋጣ ደግሞ ካፈርኩ

አይመልሰኝ ሳይሉ፣ የማይሰራውን ፈጥኖ ጥሎ ሌላ መንገድ መፈለግ ግድ ነው። ስህተትንም በወቅቱ አርሞ፣ ሰናዩን አለምልሞ፣ ጠንካራውን አጎልብቶ፣ መያዝ ደግ ነው። ይህን ለማድረግ ደግሞ ከአምናው ምን

ተምረናል?  ለነገስ ምን ጨብጠናል? የማለት ድፍረትና ግልጽነት እንዲኖረን ያሻል።
አዲስ ፈር ለመቅደድ መስዋዕትነትን መክፈል፣ ያልተሞከረውን መሞከር፣ ያልታየውን ማየት ያስፈልጋል። ትላንት በሀሄድንበት መንገድ ዛሬም ብንመላለስበት ኮቴአችንን ከመጨረስ በቀር፣ ወደላቀ ግብ መድረስ እርም

ነው። ትላንት በተሟገትንበት፣ በተዛለፍንበት፣ ላንደማመጥ በተጯጯህንበት ሸንጎ ዛሬም ያንኑ እሪታና ጩኸት፣ ያንኑ ችኮላና ድንፋታ፣ ያንኑ እርግማንና ውግዘት ብናላዝን ብናስተጋባበት፣ ድምጻችን ከመዛሉ፣ ጉዟችን

ከመሰናከሉ በቀር ብዙ አንራመድም። ከመበቃቀል መተራረም፣ ቂም ከማርገዝ  የቂምን ሥነ-ነገር መርምሮ ለመንቀል መጣጣር፤ ዋና ጉዳይ የሚሆነውም ለዚህ ነው።
ከቶውንም ትላንት እጅግ ጨለማ የመሰለንን ንፍቀ ክበብ፣ ዛሬ በመጠኑ እንኳን ደብዛዛ ውጋጋን ካየንበት ውጋጋኑን ለማስፋት እንጂ “ይሄውላችሁ፣ ዛሬም በደምብ አላነጉትም!” እያልን ቡራ-ከረዩ ብንል፤ አንድም

የለውጥን አዝጋሚ ሂደት መካድ፣ አንድም ያ ውጋጋን ብሩኅ ፀዳል እንዳገኝ የእኛን አስተዋጽኦ መንፈግ ይሆናል። ባለፈው፣ ባልሞከርነው ነገር ሳቢያ ባጠፋነው ጊዜ ስንፀፀት፣ አዲስ ሙከራ የምናደርግበትን ሌላ ውድ

ጊዜአችንን እንዳናጨልም መጠንቀቅ ይበጃል። ሀገራችን አሁን ላለችበት ቦታ የበቃችውኮ በደጉም በክፉውም ሂደት ሳቢያ ነው። ማህበረሰባችንም እንደዚያው። ክፉውን አስወግዶ አንድ እርምጃ ለመራመድ ግን አዲስ

ሙከራ እንደሚያስፈልግ በመገንዘብ መንቀሳቀስን ይጠይቃል። የሌሎችን ድምፅ በትዕግስት መስማት፣ መንገዳቸውን በጥሞና ማየት፣ እኛ ያደረግንላቸወን ያህል እነሱም ያደርጉ ዘንድ ሁኔታዎችን ማመቻቸት። ለዚህ

ደግሞ ትርፉን ብቻ አውቀን መከራውን ሳናውቅ ከተጓዝን ህልማችን ሁሉ ከላይ እንደተጠቀሰው ገበሬ ጉልበት አጥቶ ይወድቃል። የራዕያችንም ክንፉ ከወዲሁ ይሰባበራል። ተስፋችን ሳይጫር ይከስማል። በዚህ መንገድ

የሄዱ ጳጳሱም፣ ሼኪውም፣ ሹሙም ዜጋውም፣ የፖለቲካ ቡድኖቹም፣ መንግስታዊ የሆኑና ያልሆኑ ድርጅቶቹም አበክረው ማስተዋል ያለባቸው ቁምነገር ይሄ ይመስለናል።
“ያለፈ ጥረታችንን ሳስታምመው ትዝ ሲለኝ
ከሞከርነው ነገር ይልቅ ያልሞከርነው ነው እሚቆጨኝ”
ለማለት መቻል አለብን እንደ “ቴዎድሮስ”። ያልሞከርነውን ለመሞከር ዝግጁነት ወሳኝ ነው!! የመንፈስም የአካልም። ከዚያ በኋላ “ሁሉንም ሞክሩ፤የተሻለውን ያዙ”! ለመባባል እንችላለን።

ብልፅግና “የሚዲያ ሠራዊት” አደረጃጀት የለም ሲል አስተባበለ

በገዢው ብልፅግና ፓርቲ በተለይም በአዲስ አበባ ከተማ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ስር የሚንቀሳቀሱና ‘የሚዲያ ሠራዊት’ የሚል ስያሜ የተሰጣቸው የፓርቲው አባላት፤ መንግሥትን በሚተቹና በሚቃወሙ ግለሰቦች

ላይ ሐሰተኛ መረጃ የማሰራጨት ዘመቻ ሥርጫትላይ መሳተፋቸውን   ቢቢሲ ባደረገው ምርመራ ማረጋገጡን አመለከተ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወረዳ አመራሮችም በፓርቲው የወረዳ መዋቅሮች ትዕዛዝ በተለይም የመንግሥትን ገፅታ በሰው ሰራሽ መንገድ ለመገንባት ፌስቡክ ላይ በሚደረጉ አሳሳች ዘመቻዎች ላይ እንደሚሳተፉ

የቢቢሲ ምርመራ ያሳያል። ቢቢሲ ለዚህ ምርመራ በአዲስ አበባ ከተማ የወረዳ አመራር፣ የፓርቲ አባል እንዲሁም በከተማዋና በፌደራል መንግሥት መሥሪያ ቤቶች ውስጥ የሚሰሩ የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊዎችና

ባለሙያዎች አነጋግሯል።
በተጨማሪም  በአዲስ አበባ ከተማ ሰባት ክፍለ ከተሞች ውስጥ የሚገኙ የፓርቲው የወረዳ መዋቅሮች በዋትስአፕና ቴሌግራም ግሩፖች ውስጥ ለሶሻል ሚዲያ ዘመቻዎች የተለዋወጧቸውን መልዕክቶች ተመልክቷል።

በግሩፖቹ ውስጥ ለወረዳ አመራሮችና ሚዲያ ሠራዊት አባላት የሚሰጡ ትዕዛዞችንና አፈጻጸማቸውን የተከታተለ ሲሆን የፌስቡክ ዳታዎችን በመውሰድም መተንተኑን ይጠቅሳል።
ሜታ (ፌስቡክ) ለቢቢሲ በሰጠው ምላሽ፤ “ሐሰተኛ አካውንቶችን” በመጠቀም “በኢትዮጵያ መንግሥት” የፌስቡክ ልጥፎች ላይ “ብዛት ያላቸው አዎንታዊ አስተያየቶች” መሰጠታቸውን በምርመራ እንደደረሰበት

አስታውቋል። ሜታ፤ በዚህ ድርጊት ላይ በተሳተፉ ሐሰተኛ አካውንት እና ገፆች ላይ እርምጃ መውሰዱን የገለጸ ሲሆን፣ ቢቢሲ ሲከታተላቸው የነበሩ አካውንቶችም እንዲወገዱ ተደርገዋል።
የብልፅግና ፓርቲ በበኩሉ፤ ‘የሚዲያ ሠራዊት’ የሚባል አደረጃጀት “አለመኖሩን” በመግለፅ ለቢቢሲ በሰጠው የፅሁፍ ምላሽ፤ ጉዳዩን አስተባብሏል። የፓርቲው ዋና ፅህፈት ቤት፤ “በተለይ ‘ሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ

ንግግር ተብለው ሊቆጠሩ የሚችሉ ጽሑፎችና ምስሎች ተሠራጭተዋል’ በሚል የተገለጸው ፍጹም ተቀባይነት የሌለው አገላለጽ ነው” ብሏል።
የብልፅግና ፓርቲ ‘የሚዲያ ሠራዊት’ አባላት ፌስቡክ ላይ የሚያርጓቸውን ዘመቻዎች በተመለከተ ለሦስት ወራት ያካሄደውን ምርመራ ውጤት በዝርዝር አስነብቧል።
ከሦስት ወራት በፊት ጥር 2 ቀን 2016 ዓ.ም. ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ገደማ ጀምሮ “አቡነ ጴጥሮስ ከሀገር ኮበለሉ” የሚሉ ልጥፎች በበርካታ የኢትዮጵያውያን የፌስቡክ አካውንቶች እና ገጾች መሠራጨት ጀመሩ።
በፎቶና ጽሁፍ ከተቀናበረ ምስል ጋር የተሠራጩት እነዚህ ልጥፎች ፌስቡክ ላይ የወጡት፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ አቡነ ጴጥሮስ ከአዲስ አበባ ወደ አሜሪካ መጓዛቸውን ተከትሎ

ነበር። የፌስቡክ አካውንትና ገጾች እንደተለጠፈ ቢቢሲ አረጋግጧል። ከግራፊክስ ምስሎች ጋር የተለጠፈው ይህ ጽሁፍ፤ ጥር ሁለት ቀን ብቻ  ቢያንስ 898 ጊዜ ፌስቡክ ላይ ተጋርቷል።
የምስሉ መግለጫ, አቡነ ጴጥሮስ “ኮብልለዋል” በሚል ፌስቡክ ላይ ከተሠራጩት ልጥፎች ውስጥ አብዛኛዎቹ “ፅንፈኝነት_ይውደም” እና “መከላከያ_የሀገር_ጋሻ” የሚል ሀሽታግ ተያይዞባቸዋል ይላል- የቢቢሲ

ምርመራ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን “የማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየተናፈሰ ያለው ወሬ እጅግ የተሳሳተ” መሆኑን በመጥቀስ፣ ጉዳዩን ያስተባበለችው በማግስቱ ነበር ያለው ቢቢሲ፤ ስለጉዳዩ ጥያቄ የቀረበላቸው

አቡነ ጴጥሮስ፤ አስተያየት መስጠት እንደማይፈልጉ መግለፃቸውን አስታውሷል።
ይህ መረጃ ከተሰራጨ ከአንድ ወር ገደማ በኋላ “ኮብልለዋል” የተባሉት አቡነ ጴጥሮስ ወደ ኢትዮጵያ ቢመለሱም፣ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ወደ መጡበት እንዲመለሱ መደረጋቸውን

አስታውሷል።
በዕለቱ ስለ ሲኖዶሱ ዋና ፀሐፊ “መኮብለል” ፌስቡክ ላይ የተሠራጩት መረጃዎች፤ በመደበኛ የፌስቡክ ተጠቃሚዎች የተሰራጩ የተለመደው ዓይነት የሐሰተኛ መረጃ አልነበሩም። ቢቢሲ ባደረገው ክትትል፤ የመረጃዎቹ

ሥርጭት ካለፈው ዓመት ጥር ጀምሮ ከቤተክርስቲያኒቱ ጋር ቅራኔ ውስጥ የገባውን መንግሥት ከመሠረተው ገዢው ብልፅግና ፓርቲ ጋር ግንኙት እንዳለው የሚያሳዩ ማስረጃዎችን አግኝቷል። የብልፅግና የሚዲያ

ሠራዊት አባላት በዚህ ዘመቻ እንዲሳተፉ ያደረገው የቂርቆስ ክፍለ ከተማ የወረዳ የፓርቲ መዋቅር ብቻ አልነበረም። በቦሌ ክፍለ ከተማ ውስጥ የሚገኙ የብልፅግና ፓርቲ አባላትም የአቡኑን “መኮብለል” የሚገልጹ

ጽሁፎችና ምሥሎች እንደተላኩላቸው በቦሌ ክፍለ ከተማ የወረዳ አመራር የሆኑ ግለሰብ ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።
በወረዳው የፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት አመራር አባላት የዋትስአፕ ግሩፕ ላይ እነዚህ ምሥልና ጽሁፎች የተላኩት፤ “ዘመቻ አድርጉ” ከሚል ትዕዛዝ ጋር መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
“ግሩፑ ላይ የተላከው ጽሁፍ የአቡነ ጴጥሮስን ዜግነት ይገልጽና ‘ከሀገር ወጡ፣ ኮበለሉ’ ይላል። ‘የውጭ ዜግነታቸውን ሽፋን አድርገው የተለያዩ የሐሰት ሰነዶችን በማዘጋጀት ከሀገር በሕገ ወጥ መንገድ ወጥተዋል’

ይላል” ሲሉ፣ በዋትስአፕ ግሩፑ ላይ የተለቀቀው ጽሁፍ በዕለቱ በፌስቡክ ላይ ከተሠራጨው ጋር ተመሳሳይ እንደሆነ ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።
የአቡነ ጴጥሮስ ጉዳይ፤ በአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ፅህፈት ቤት የወረዳ መዋቅሮች አስተባባሪነት የተደረገ ብቸኛው የፌስቡክ ዘመቻ አይደለም ብሏል- በምርመራው ውጤት።
ሆኖም የብልፅግና ፓርቲ ለቢቢሲ በሰጠው ምላሽ፤ “የሚዲያ ሰራዊት” የሚባል አደረጃጀት የለም ሲል ጉዳዩን ሙሉ በሙሉ አስተባብሏል።

አልነጋም፤ ካሳንቺስ ሰውዬው መኖሪያ ቤት በር ላይ ደርሰናል።
ደወልን፤ ስልክ አነሳ። አሁን ልቤ ዐረፈ። ብዙ ጊዜ መንገድ ስለመኼድ ስንመካከር ደስ ብሎት ይሰማል። ዐልፎ ዐልፎ ደግሞ ይሳተፋል። “እዚኽ ደርሰን እንዲኸ አድርገን” ዓይነት። ከዚያ ጠዋት እንቀጣጠራለን። በሰዓቱ ግን የእሱ ስልክ አይሰራም።
ሻንጣውን አንጠልጥሏት ወጣ።
መንገዳችንን ቀጠልን።
እንዲህ ሆነን ማፌድ ደርሰናል። ዛሬም ድረስ ዓሌክስ እግሩ ከቤት ይውጣ እንጂ፣ የሆነ ቦታ ሲደርስ ለቦታው ስርዓት እንደምን ተገዢ እንደሆነ ያየሁበት ጉዞ ሆነ።
መስቀል ልናሳልፍ የደጉ ሰው ነዳ ሽጉሞ ቢሎ እንግዶች ሆነናል። መስከረም እኩል ሲሆን እኖር፣ ማፌድ ባሩኝ የምትባለው ትንሽ መንደር ገባን።
ከዚያ በኋላ አምስት ቀናት ቆየን። ዝም ብዬ ሳስበው ይደንቀኛል። ዓለማየሁ ገላጋይ ጥቂት ሰአት ከሰው ጋር ሲያሳልፍ የዚያን ሰው ሁሉን ነገር የነጠቀ የሚመስለው፣ ሽቁጥቁጥ ነው። በእኔና የማፌድ ቀናት ግን መሰልቸት አልታየበትም። ያደምጣል፤ ደግሞ እግሩ አይድረስ እንጂ፣ ንባቡ የደረሰበት ቀዬ ብዙ ነውና፣ ከሚያውቀው እያነሳ ይጠይቃል።
የስነ-ሰብ ጥናት ባለሙያዎች እንደ እሱ ያሉትን ሰዎች Cultural Intelligence ያላቸው ይሏቸዋል። ዓሌክስ እንዲህ ያለ ሰው እንደሆነ አምናለሁ። ባህልን የሚረዳው በብልሃት ነው። በዚያ ላይ ትርጉም የሚሰጥበት ብቃት ያስቀናኛል።
ደመራ የለኮሰን ቀን ከቤቱ አባወራዎች ጋር ረዥሙን የችቦ ጫፍ እሳት አስነክሶ፣ በዚች የባሩኝ መንደር ጀፈሮ ላይ ሲራመድ፣ አንድ መስቀል ከቀዬው ያልተለየ ጉራጌ ይመስል ነበር።
ዓሌክስ ሌላ አካባቢ ሲቀላቀል ሰላማዊ ስለሆነ አይረብሽም። በአካባቢውም ላለመረበሽ ራሱን ከስፍራው ጋር በጣም ያቆራኛል። ከጉራጌ ምድር ስንመለስ፣ የጉዟችን ምክንያት ለሆነው ወንድማችን ሃይሉ ሰለሞን “ሰውዬው እሺ ብሎ ከቤቱ ይውጣ እንጅ ቆይታውን ማጣጣም የሚችል የጉዞ ሰው ነው” አልኩት። ተሳሳቅን።
አካባቢን የሚረዳበት መንገድ በስራዎቹ ላይ ፍንትው ብሎ ይታያል። ለምሳሌ “የሞጆ ቀትሮችን” በ”የብርሃን ፈለጎች” ላይ ሳነብ፤ የኢኮሎጂ ትዝብቱና የገለፃ ርቀቱ ደራሲው በእርግጥም መቼቱን ማሳወቅ ብቻ ሳይሆን፣ ሳይንሳዊ በሆነ ሚዛን መረዳት ላይም የሚከበር ሰው ነው እላለሁ።
ከተፈጥሮ ያለውን ዝምድና በሥራዎቹ ተመልክቻለሁ። መራር ድምፆች በሰው በአካባቢና በተፈጥሮ ህልውና መስተጋብር ተጋምደው ይሰማሉ። “ታለ፤ በእውነት ስም” ላይ “ከተማ ሙቀት እና ጩኸት ነው.” ይላል። ይኼ አሁን የረቀቀው የተፈጥሮ ጥበቃ የሳይንስ ሊቃውንት ይዘውት ብቅ ያሉት የአካባቢ ፍልስፍና ነው። ዓለማየሁ በአጭሩ የGlobal Warming እና Sound  Pollution ችግር ከከተሜነት ቅጥ ማጣት ጋር የተሳሰሩበትን ቀውስ ትብታብ ያሳየናል። ወረድ ብሎም፤ “… ህይወት በከተማ ውስጥ ቅጥ አጥታለች፤ ተፈጥሮ ህብረ ዝማሬዎቿን ይዛ ተሰድዳለች። ወፎች- አይዘምሩም፣ ውሆች ፀናፅናቸውን አያንሿሹም፣ ዛፎች ከነፋሳት ጋር አይላፉም። ከዚህ በመነሳት፣ ዓለም አረንጓዴ ትችት ለሚለው ዘመነኛ አብዮት ዓለማየሁ Ecocriticismን በፈጠራ ሥራዎቹ በማሳየት ለአካባቢው የቀረበበትን ስሱ ልብ እንድናይ አድርጎናል።
ብዙ ጉዞዎችን አብረን ተጉዘናል። ለቀናት ቆይተናል። ምርጫው ያለበትን ቦታ በቅጡ መረዳት እንደሆነ አይቻለሁ። በእድሜ ጠና ካሉ ሰዎች ጋር መጨዋወት ይመርጣል። ብዙ ሰአት ወስዶ ራሱን እየነቀነቀ ያደምጣቸዋል።
ብዙዎች Bibliophile or Bookworm ስለሆነው ዓለማየሁ ያውቃሉ። እሱ ግን Empathetic የሚሉት ዓይነት ሰው ነው። ጥልቅ ብሎ ያደምጣል፤ ይረዳል። ከተረዳው ነገር ጋር አብሮ ይኖራል። ደጋግሞ “ለተፈጥሮ ግድ የለኝም። ፏፏቴ ለማየት ገደል ባልወርድ እመርጣለሁ” ይለኛል። ይሄንን እንዳልቀበል ያደረጉኝ ጉዞዎች ግን ነበሩን። ተራራው አጠገብ አብረን ስንቆም፣ ተራራውን የተመለከተበትን ስስት አልረሳውም።
ወደ አንኮበር አብረን ተጉዘናል። እመ ምህረት ተራራ አጠገብ ቆመን ለተፈጥሮው እጅ ሲሰጥ አይቻለሁ። ከዚያ የማያቆም ጥያቄ ቀጠለ፤ መኪናው እንዲቆም አሳሰበ።
“ቁንዲ የምትታይበት እንቆምና ፎቶ እንነሳለን፣” ይለናል። በእርግጥ ወደ ቁንዲ እንሂድ አይበል እንጂ ቁንዲ አጠገብ መድረስ ግን መሻቱ እንደሆነ ተረዳሁት። እንዲያ ባይሆን፣ ቅንብቢት በዚያ መልኩ መች ትገለጽ ነበር? ያለፈባቸውን ብቻ የሸኖ ጎዳናዎች በዚያ መልኩ ሊረዳቸው እንደምን ይችላል?
ተራራ ብቻ ሳይሆን፣ ውኃም ትንፋሹን ስትር አድርጎ ተፈጥሮን ያደምጥ ዘንድ ያደርገዋል። ወደ ጣና አብረን ተጉዘናል፤ በተደጋጋሚ። ጀልባ ላይ ከወጣ በኋላ ዐይኑን ባሕሩ ላይ ተክሎ ዝም ይላል። ያን ዓይነት ምሳጤውን የማስታውሰው፣ በሰዎች መካከል ሆኖ ዐልፎ ዐልፎ እጁን አፉ ላይ ያደርግና በሐሳብ ሩቅ ሲሄድ ነው። ይሄንን አይነት ስሜት በሀዋሳ የሀይቅ ዳርቻ አሞራ ገደል አረፍ ብለን ስንጫወት፣ እሱ ዐይኖቹን ሰድዶ ከፍቅር ሐይቁ ጋር ሲነጋገር አይቼበታለሁ። በጥልቅ ስለሚረዳው አካባቢ አንዳች ነገር ሲገልጽ ይነዝራል። ጎንደርን “የህልሜ ከተማ” ሲላት የቀናሁት ቅናት አሁንም አልለቀቀኝም። ወደ ጎንደር ስንሄድ ብዙ ጊዜ ሳይደርስ መመለስ የማይፈልግበት ቦታ ሞኝ መቆሚያ ነው። ለምን እንደሚወደው አላውቅም። ቦታው የጉልበት ሠራተኞች አሰሪ ጥበቃ የሚቆሙበት ሲሆን፣ ዓሌክስ በጎንደር ቆይታው አንዱን ቀን ሞኝ መቆሚያ ደርሰን እንምጣ ሳይለን አይቀርም።
ገና የፋሲል ከተማ ሲደርስ “ዋሴ ነጋሽ ሞኝ መቆሚያ ደርሰን አንመጣም?”ይጠይቃል። እንስቃለን። ወግ አጥባቂዎቹ አካባቢዎች አብረን ስንቆይ ወግ አክባሪው ዓለማየሁ ስፍራውን መስሎ የብዙ አባቶችን ልብ በልቶ ይመለሳል። ትዝታዎቹ ሆነው ይቀራሉ። ዓሌክስ ወደ ፀሐይ መውጫ ሲሄድ ደግሞ ቀላልና ተግባቢ ሰው ሆኖ ይገለጣል። የባሕር ዳር ልጆች የሚያውቁትን ዓሌክስ የድሬ ልጆች ኤውቁትም፤ ሁለቱንም የሚያውቀው ዓሌክስ ግን ቦታን፣ ሰውንና ባህልን የሚረዳበት መንፈሱ ድንቅ ነው።
በነገራች ላይ፣ ኣለማየሁ ገላጋይ ደርሼ ጥምድ ያደረኩት ሰው ነበር። በእልህ ሥራዎቹን አላነብም ብዬ ብዙ አመጽኩ። በጣም ብዙ ጊዜ። ለምን እንዲያ እንደሆንኩ  ሳስበው ብቻዬን ፈገግ እላለሁ። በሰዎች ጥያቄና ምልጃ አንድ መጽሐፉን ለማንበብ ተስማማሁ። “ወሪሳ”ን አነበብኩ። ከዚያ በኋላ በሆነው ተቃራኒ ስሜቴ በጣም እገረማለሁ።
ዓለማየሁ አምጰርጵርን ብቻ ሳይሆን፣ እኔንም አምጰረጰረኝ። ያለ ዕረፍት ሌሎቹንም ስራዎቹን አከታትዬ አነበብኩ። አንድ ቀን ሳገኘው ነገርኩት። አቀርቅሮ አድናቆቴን እንደ ሸክም ቆጥሮብኝ ዐለፈ። የጋራ ወዳጆች ነበሩን። አስደናቂው ነገር ግን  ትውውቃችን የጠነከረው በጉዞ ሆነ። ወደ ባሕር ዳርና ጎንደር አብረን ተጓዝን፤ ለወዳጅነታችን የማዶ ለማዶ በራፉን የገነጠልንበት ቆይታ ሆነ። እንዲህ እንደ ቀልድ አመት ዓመቱን እየወለደ፣ ቢያንስ በሳምንት አንድ ቀን አብረን የምንውል ወዳጆች ሆንን።
“ወሪሳ” አስማት የሆነ ሥራው ነው፤ ብዙ ሰውም ይጋራኛል። “በፍቅር ስም”፣ “ታለ፤ በእውነት ስም” እና “ሐሰተኛው፤ በእምነት ስም” እጅግ የወደድኳቸው ስራዎች ናቸው። ከኢ- ልቦለዶቹ “ኢሕአዴግን እክሳለሁ” ያስገርመኛል፡፤ “ውልብታ” ሳትገባኝ የቀረች ስራ ናት።
በወዳጅነታችን የደረስኩበት ድምዳሜ ሰውዬው ዓለማየሁ፣ ከደራሲው ዓለማየሁ በላይ አስደናቂ ሰው ነው የሚል ነው። ስሱ ልብ አለው፤ ትልልቆቹን ያከብራል፤ ከነክብራቸው በደስታ ያልፉ ዘንድ ቁጭት መሰናክላቸውን የሚያነሳ መንገድ ጠራጊ ነው። ታዳጊዎችን አቅጣጫ ለመምራት መንገድ ቆሞ ይጠብቃል። ራሱን ዝቅ አድርጎ ከፍ የሚሉበትን ይመራል። ኣለምን ይንቃታል። ስስት አያውቅም፤ ጊዜውን፣ ገንዘቡን፣ ፍቅሩን የማይሰስት ወዳጅ ነው።
ምንጭ፡ -“መልክአ ዓለማየሁ” ፤ቴዎድሮስ አጥላው (አርታኢ)

Page 1 of 702