Administrator

Administrator

10 አገር አቀፍ ኮንሰርቶችን ለማቅረብ ማቀዳቸውን ገልጸዋል

የሃይንከን ኢትዮጵያ ብሔራዊ ብራንድ የሆነው ዋልያ ቢራና ዝነኛው ኢትዮጵያዊ ሙዚቀኛ፣ ዜማ ደራሲና አቀናባሪ ሮፍናን ኑሪ፤ “ዘጠኝ” በተሰኘ የሙዚቃ አልበም ላይ አጋርነታቸውን በማራዘም፣ ከትላንት በስቲያ

ሐሙስ ስምምነት ፈጽመዋል፡፡
ዋልያ ቢራና ሮፍናን አጋርነታቸውን ለቀጣይ 18 ወራት እንደሚቀጥሉ የተጠቆመ ሲሆን፤ በዚህ ጊዜ ውስጥም 10 አገር አቀፍ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን በክልል ከተሞች ለማቅረብ ማቀዳቸውን ይፋ አድርገዋል -

በሰጡት መግለጫ፡፡
በቅርቡ የሚለቀቀው የሮፍናን አልበም፣ በሙዚቃና በኪነጥበብ የኢትዮጵያን ልዩ ታሪክና ባህል የሚገልጽ ነውም ተብሏል፡፡
በዋልያ ቢራና በሮፍናን መካከል “ስድስት” በተሰኘው አልበም በነበረው ጥምረት የክልል ቱሪዝምን ያደመቁ ስድስት ኮንሰርቶችን በማዘጋጀት ተመልካቾችን ከመሳብም አልፎ ብዙ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ባወጣው

መግለጫ ያስታወሰው  ዋልያ ቢራ፤ በተጨማሪም በሮፍናን ማስተርክላስ የሮፍናንን የሙዚቃ ዕውቀት መሰረት አድርጎ፣ ከአንጋፋ ባለሙያዎች ጋር በመተባበር፣ ከሙያዊ ሥነምግባር እስከ የራስን ብራንድ ፈጠራ

ድረስ ከዋልያ ጋር በመሆን ያለውን ልምድ ማካፈል እንደቻለ አመልክቷል፡፡ሙዚቀኛው ሮፍናን በ“ዘጠኝ” አልበሙ የያዛቸው “ሐራንቤ” እና “ኖር” የተሰኙ አልበሞች በአንድ ቀን እንደሚወጡ የጠቆመው የዋልያ

ቢራ መግለጫ፤ ይህም ሮፍናንን በኢትዮጵያ ሁለት አልበሞችን በአንድ ቀን ያወጣ የመጀመሪያው አርቲስት እንደሚያደርገው ጠቅሶ፣ ዋልያ ቢራም የዚህ ታሪክ አካል በመሆኑ ታላቅ ኩራት ይሰማዋል ብሏል፡፡
“ከሮፍናን ጋር ያለን ጥምረት የሙዚቃ ኮንሰርቶችን ከመሥራት ባሻገር የአገራችንን ባህል ማጎልበት፣ ዕምቅ የራስ ጥበብን ማውጣት፣ የሥራ ዕድል መፍጠርና መልካም አመለካከትንም መቅረጽ ነው፡፡” ብሏል -

ዋልያ በመግለጫው፡፡ 

ሕፃናት ጸሐፍት ዛሬ መጻሕፍቶቻቸውን በጋራ ያስመርቃሉ



በከተማችን በየዓመቱ በጉጉት የሚጠበቀው ንባብ ለሕይወት ለተማሪዎችና ቤተሰቦቻቸው የሚያዘጋጀው ”ተማሪ ፌስት” የተሰኘ ትምህርታዊና አዝናኝ ፌስቲቫል ዛሬና ነገ በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል፡፡
“ተማሪ ፌስት” የተለያዩ ገፅታ ያላቸው ፕሮግራሞች ተቀናጅተው በአንድ መድረክ የሚቀርቡበት የቤተሰብ መርሃ ግብር ሲሆን፤ ከፕሮግራሞቹም መካከል የብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች ከወዲሁ በቂ የሥነ-ልቦና ዝግጅት

እንዲኖራቸው የሚያግዝ ገለፃ በመስኩ ባለሙያዎች እንዲሰጣቸው ማድረግ ነው፡፡  
ከ7ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ለሚማሩ ተማሪዎችም “ልዩ ተሰጥኦ ያሸልማል” በሚል መሪ ቃል ነፃ የትምህርት ዕድልና የተለያዩ ሽልማቶች የሚያስገኙ የተሰጥኦ ማሳያ ልዩ መድረክ እንደሚጠብቃቸው ለማወቅ

ተችሏል፡፡
በተመሳሳይ በዚህ ዛሬ በሚከፈተው የተማሪዎች ፌስቲቫል ላይ ሰባት ሕፃናት ያዘጋጇቸውን ሰባት መጻሕፍት በጋራ እንደሚያስመርቁ ተጠቁሟል፡፡
ሰባቱ ሕፃናት ጸሐፍት የ“ማርካን እና ሪማስ” ደራሲ የ7 ዓመቷ የማርያም ብሩክ፣ የ“ሁለቱ ጓደኛሞች እና ቤተሰብ” ታሪክ ደራሲ የ10 ዓመቷ አሜን ልዑልሰገድ፣ የ“ቅቤ እና ቋንጣ” ደራሲ የ10 ዓመቷ

ሔመን ብሩክ፣ የ“ሁለቱ” መጽሐፍ ደራሲ የ11 ዓመቱ ቢኒያም መለሰ፣ የ“እርሳስ እና እስኪርብቶ” ደራሲ የ12 ዓመቱ ዮናታን ልዑልሰገድ፣ የ“ሳራ እና ቢታንያ” ደራሲ የ 11 ዓመቷ ፈርደውስ ሡልጣን እና የ

“ላሊበላ” ደራሲ የ14 ዓመቱ ዮሴፍ መለሰ ናቸው፡፡
ዛሬ ቅዳሜና ነገ እሁድ  ከጠዋቱ 4፡00 እስከ ምሽት 1፡00 በሚቆየው ፌስቲቫል ላይ ስመጥር ምሁራንና ተወዳጅ አንባቢያን እውቀትና ልምዳቸውን ለታዳሚያን የሚያጋሩ ሲሆን፤ ከዚሁ ጎን ለጎን በርካታ

የቤተሰብ ጨዋታዎች፤ የልደት ፕሮግራሞችና ቤተሰብን ከልጆቻቸው ጋር የሚያሳትፉ ልዩ ልዩ አዝናኝ ዝግጅቶች መሰናዳታቸው ተነግሯል፡፡
ንባብ ለሕይወት ከተለያዩ አጋር ተቋማት ጋር በመተባበር በሚሊኒየም አዳራሽ ባዘጋጀው በዚህ የተማሪዎች ፌስቲቫል ላይ ቤተሰቦች በተመጣጣኝ የመግቢያ ዋጋ ጥሩ ጊዜ እንዲያሳልፉ አክብሮታዊ ግብዣውን

አቅርቧል።

የዛሬ 100 ዓመት በነጋድራስ ገብረሕይወት ባይከዳኝ በተጻፈው “መንግሥት እና የሕዝብ አስተዳደር” መጽሐፍ ላይ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነጥበባት ማዕከልና ተወዳጅ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን  

የሚያስተባብሩት ውይይት እንደሚካሔድ፣ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነጥበባት ማዕከል አስታወቀ፡፡
ዛሬ ከቀኑ 8፡00  ጉለሌ ጳውሎስ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው ማዕከል በሚደረገው ውይይት ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገዳ ጋር ቆይታ የሚኖር ሲሆን፤ ውይይቱን ዶ/ር እንዳለጌታ ከበደ እንደሚመሩት ለማወቅ ተችሏል፡፡



በሃገራችን በጃዝ ሙዚቃ ዘርፍ ከ50 ዓመታት በላይ የሚታወቀው  አርቲስት ሙላቱ አስታጥቄ (የክቡር ዶ/ር)፣ ከአድናቂዎቹ ጋር የሚገናኝበትና እራት የሚበላበት ልዩ ምሽት መዘጋጀቱ ተገለጸ፡፡
የታዋቂ ኤቨንት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሳሙኤል አበራና የጃዝ ንጉስ ሙላቱ አስታጥቄ፣ የእራት ምሽቱን አስመልክቶ ባለፈው ሳምንት  ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫው ላይ እንደተብራራው፤ አርቲስት

ሙላቱ አስታጥቄ፣ የካቲት 9 ቀን 2016 ዓ.ም ምሽት፣ በግዮን ሆቴል በሚገኘው አፍሪካ ጃዝ መንደር፣ ከአድናቂዎቹ ጋር ተገናኝቶ ራት እንደሚበላና ፊርማውን እንደሚያኖር ታውቋል፡፡ የፎቶግራፍ መነሳት መርሃ

ግብር እንደሚኖርም ተነግሯል፡፡ በዝግጅቱ ላይ ተጋባዥ እንግዶችና ታዋቂ የኪነጥበብ ባለሙያዎች እንዲሁም የአርቲስቱ  አድናቂዎች ይገኛሉ ተብሏል፡፡
የተለያዩ ኹነቶችን በማዘጋጀት የሚታወቀው ታዋቂ ኤቨንት፣ ከዚህ ቀደም አርቲስት ሰላም ተስፋዬን በሸራተን አዲስ ሆቴል ከአድናቂዎቿ ጋር በማገናኘት፣ ራት የመብላትና የፎቶግራፍ መነሳት መርሃ ግብር በስኬት

ማካሄዱ ተመልክቷል፡፡  
በውጭው ዓለም ይህን መሰሉ ዝነኞችን ከአድናቂዎቻቸው ጋር የማገናኘትና አይረሴ ቅጽበቶችንና አጋጣሚዎችን የመፍጠር መርሃ ግብሮች በእጅጉ የተለመዱና የሚዘወተሩ እንደሆኑ ይታወቃል፡፡
የጃዝ ንጉሱ አርቲስት ሙላቱ አስታጥቄ በአገሩ ብቻ ሳይሆን፣ በውጭው ዓለም  የሙዚቃ መድረኮችም ከፍተኛ አድናቆትንና ዕውቅናን ያተረፈ አንጋፋ  የሙዚቃ ባለሙያ  ነው፡፡


ከማኅበራዊ ድረገፅ

 ዋስይሁን ተስፋዬ)

ይህ ናይጄሪያዊ ህጻን  ተስፋ ይባላል .. ለባእድ አምልኮ እራሳቸውን ያስገዙት ቤተሰቦቹ ለሞት አሳልፈው ሊሰጡት ከቤት አውጥተው በጭካኔ በጎዳና ላይ ሲወረውሩት ምንም አልመሰላቸውም።  ምክንያቱም

ለነሱ ከዚህ ነብስ ከማያውቅ ምስኪን ህጻን ይልቅ .. የህጻኑን “ሟርተኛ”  እና “መአት አምጭ”  .. መሆን የተነበየላቸው  ጠንቋይ ያስፈራቸዋልና፣ አውጥተው ከጎዳና ጣሉት.። (በነገራችን ላይ በባእድ

አምልኮ ምክንያት ህጻናትን አውጥቶ መጣል በናይጄሪያ የተለመደ ነው)  በዚህ ምክንያት፤ የጭካኔ ውሳኔ ተወስኖበት  ከሞቀ ቤት ወጥቶ የተጣለው ይህ ህጻን  ቤተሰቦቹ እንዳሰቡት ቶሎ የሚሞት አልሆነም

...... ከእናቱ እቅፍ ተነጥቆ እራሱን ባገኘበት  አንዲት መንደር ውስጥ በትናንሽ እግሮቹ ከወዲያ ወዲህ እየባዘነ ያገኘውን ለቃቅሞ እየበላ .. በወደቀበት ተኝቶ እየተነሳ ከሩቅ የታሰበለትን በጎ ነገር ያወቀ

ይመስል ሞትን እንቢ ብሎ ....የሌሊቱ  ውርጭና የቀኑ  ሃሩር እየተፈራረቀበት፣ በጽናት ቢቆይም  8ኛው ወር ላይ ግን ለሞት እጁን የሰጠ መሰለ ..
እነዚያ ወዳላሰበበት የመሩት ሰዎች የሚወረውሩለትን ወደ አፉ እንዲያደርግ የሚረዱት እግሮቹ ረሃብ አዛላቸው ..እናም አንድ ሌሊት ከተኛበት ሜዳ ላይ መነሳት እንዳቃተው ቀረ .........በዚህ ቅጽበት

..Anja Ringgren በምትባል በጎ አድራጊ ተመስለው የፈጣሪ እጆች ወደሱ ቀረቡ፤ በሆላንዳዊትዋ በጎ አድራጎት ሰራተኛ ከወደቀበት ቦታ ተገኝቶ ሲነሳ የጎድን አጥንቶቹ የሚቆጠሩ፣ ከህይወት ይልቅ ለሞት

የቀረበ በፓራሳይት የተጎዳ በረሃብ የደቀቀ ... እጅግ አሳዛኝ ህጻን ነበር፡፡ ይህች መልካም ሴት ከወደቀበት አንስታ፣ አዲስ ህይወትና አዲስ ስም ሰጠችው፡፡እናም የሞት አፋፍ ላይ ላይ ወዳለው ምስኪን ህጻን

ተጠግታም...
“ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተስፋ (HOPE) ይባላል “ .. ስትል አንሾካሾከችለት፡፡
***
አሁን ያ ሁሉ አልፏል .. HOPE በአንድ ወቅት ከሞት ጋር ፊት ለፊት ተገናኝቶ የሚያውቅ አይመስልም .... በአካሉ በርትቶ ደስ የሚል ቆንጅዬ ልጅ ሆኖ፣ በበጎ አድራጊዋ Anja Ringgren

በሚመራው የበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥ ከሚያድጉ ህጻናት ጋር እየኖረ ነው፡፡....
ከተስፋ በተጨማሪ፤ በተመሳሳይ ሌሎች ህጻናትን ከወደቁበት አንስታ ያሳደገችው በጎ አድራጊዋ Anja Ringgren፤ እነዚህ በወላጆቻቸው ተገፍተው የተጣሉ ህጻናት ከየት እንደመጡ፣ ወላጆቻቸው እነማን

እንደሆኑ ሊያውቁ ይገባል ብላ ታምናለችና. .. በቅርቡ በህጻንነት እድሜው አውጥተው የጣሉትን የተስፋን ወላጆች አፈላልጋ ነበር። በአንድነት ተስማምተው ልጃቸውን የጣሉት ባልና ሚስት ትዳራቸው ፈርሶ

በመለያየታቸው ምክንያት እናትየውን ማግኘት ባይቻልም፣ ከአባቱ ጋር እንዲገናኝና አባቱ እሱ መሆኑን እንዲያውቅ  አድርጋው ነበር። HOPE አባቱን ካገኘና አብሮ ፎቶ ከተነሳ በኋላ፣ ከወደቀበት ወዳነሳችው አሳዳጊ

እናቱ ቤት ተመልሷል።
እዚህ ላይ ግን በጭካኔ አውጥቶ የጣለው አባት፣ ያለሀፍረት ልጁን ለማግኘት መፈለጉ ለብዙዎች አስገርሟል።
***
ቅን ልብና መልካም አስተሳሰብ ካለ ተአምር መስራት ይቻላል፡፡

በግርማ ሙዚቃዎች ውስጥ ሁሉ ያለችው ሴት አንድ ናት፡፡ የሚወዳት የሚያኮርፋት፣ የሚቀርባት የሚርቃት እሷን ብቻ ነው - እጸገነትን፡፡ እጸገነት ገብረሥላሴ የልጅነቱ ናት፤ የልጁም እናት፡፡ በንጹሕ ልቡ የወደዳት፤

የምትወደው፡፡ “ሴት አላምንም” ፣ “ትወጅኝ እንደሁ”፣”ቁርጡን ንገሪኝ” እና “ፍቅር እንደክራር”ብሎ ያዜመላት፡፡ “ይበቃናል” ብሎ ያንጎራጎረውም ለእጸገነት ነው- የራቀችው ቢመስለው፡፡ ግን አይሆንለትም፡፡

“ጥሩልኝ ቶሎ” ይላል፡፡
አቃተኝ ፍፁም መለየት
እሷን ከመሰለ ወጣት
ጥሩልኝ ቶሎ በፍጥነት
ትድረስ በነፍሴ ሳልሞት
ፍፁም ፍፁም አልተዋትም
ካለሁ በሕይወት አረሳትም...
“ጥሩልኝ ቶሎ” የግርማ የአፍላነት ዜማ ነበር፡፡ ኋላ ግን የአሳዛኝ ሕይወቱ ማጀቢያ ሙዚቃ ሆነ፡፡ በፍቅራቸው ሰሞን ስትጠፋበት “ጥሩልኝ ቶሎ” ብሎ ያንጎራጎረላት እጸገነት፤ በጎልማሳነቱ ዘመን ጥላው ሔደች -

ወደ አምላኳ፡፡ ግርማ ከዚያ በኋላ ሙዚቃን ፈራ፡፡ በብዙ ጉትጎታ ተመልሶ ሲመጣም ከእጸገነት መራቅ ተሳነው፡፡ “Mistakes on purpose” ብሎ በሰየመው የሙዚቃ አልበሙ ላይም “በመልክሽ

አይደለም” በተሰኘ ዜማው፤ የልጅነት ፍቅሩን ዘከረ፡፡ በካንሰር ሕመም ካለፈች 32 ዓመታት ቢሞላትም፣ ዛሬም ፎቶዋን አቅፎ እንደሚተኛ አንጎራጎረ፡፡
እስኪመሽ እናፍቃለሁ፤ እስክተኛም እጓጓለሁ፤ ምክንያቱም ጸጊን ስለማገኛት አለ፡፡ ግርማ ዕድሜውን ሙሉ የዘፈነላት ሴት አሁንም አብራው እንዳለች ያስባል፡፡ በጊዜ ቤቱ ገብቶ ከፎቶዋ ጋር ሲጫወት ያመሻል፡፡ እኔም

ተራው ደርሶኝ በድጋሚ እስካገኛት እያለ፡፡...!

የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር በ4 ዘርፍ ሽልማቶችን ይሰጣል
በጉባኤው ከ100 በላይ ድርጅቶች ይሳተፉበታል ተብሏል



60ኛው ዓመታዊ የህክምና ጉባኤና ዓለማቀፍ የጤና አውደ ርዕይ ሊካሄድ ነው
የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር በ4 ዘርፍ ሽልማቶችን ይሰጣል
በጉባኤው ከ100 በላይ ድርጅቶች ይሳተፉበታል ተብሏል

ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ማግኘት የሚችል ጤናማና የበለፀገ ማህበረሰብ የማየት ራዕይ ያነገበው የኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር፣ ዘንድሮ 60ኛውን ዓመታዊ የህክምና ጉባኤና ዓለማቀፍ አውደ ርዕይ፣ ከየካቲት

29-30 ቀን 2016 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል እንደሚያካሂድ አስታወቀ፡፡
ዓመታዊው የህክምና ኮንፈረንስ በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚኖሩ ዕውቅ የህክምና ባለሙያዎች ያላቸውን ዕውቀት፣ የምርምር ግኝቶችንና የህክምና ልምዶችን ለመለዋወጥ የሚረዳ መድረክ መሆኑን የገለፀው

ማህበሩ፤ የፓናል ውይይቶችም እንደሚካሄድበት ጠቁሟል፡፡
በህክምና ጉባኤው የሙያ ማሻሻያ ሥልጠናዎች እንደሚሰጡና የሳይንሳዊ ግኝቶች የሚቀርቡበት ክፍለ ጊዜም መዘጋጀቱ ተገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር 60ኛው ዓመታዊ የህክምና ጉባኤና ዓለማቀፍ የጤና አውደ ርዕይ ላይ ከ600 በላይ የተከበሩ የህክምና ባለሙያዎች፣ ከተለያዩ ክልሎች የሚመጡ የማህበሩ አባላት ተወካዮች፣ የተለያዩ

የጤና ባለሙያዎች ማህበራትና ስፔሻሊስቶች ማህበራት የተውጣጡ ተወካዮች እንዲሁም የህክምና ኮሌጅ ሃላፊዎች ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡
በአውደርዕዩ ከ100 በላይ ድርጅቶች እንደሚሳተፉበትና ከ2ሺ በላይ ሰዎች ይጎበኙታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ማህበሩ ጠቁሟል፡፡ በየዓመቱ የሚጠበቀው የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር የሽልማት መርሃ ግብርም በአራት

ዘርፎች እንደሚሰጥ ታውቋል፡፡ ሽልማቶቹም፤ “የኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር የዓመቱ ምርጥ የህክምና ተማሪዎች ሽልማት 2016”፣ “የኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር የህይወት ዘመን ሽልማት 2016”፣”የኢትዮጵያ

ሕክምና ማህበር ተፅዕኖ ፈጣሪና ምርጥ ወጣት ሃኪም ሽልማት 2016” እና “የኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር የ2016 የዓመቱ ምርጥ ተቋም” ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ የሕክምና ማህበር የተመሰረተው በ1954 ዓ.ም መሆኑ ይታወቃል፡፡

በቅርቡ 16 እህት ኩባንያዎችን እንደሚከፍት ተጠቁሟል
* በቀጣዮቹ ወራት 24 የቴክኖሎጂ ፕላትፎርሞችን ተደራሽ ያደርጋል

ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ፤ ከገበሬው ቴክኖሎጂ ሶሉሽን የተሰኘ እህት ኩባንያ በመመሥረት ስድስት የቴክኖሎጂ መተግበሪያዎችን አስተዋወቀ፡፡ TርTዝ ብላክ፤ የቴክኖሎጂ መተግበሪያዎቹን ያስተዋወቀው ከትላንት በስቲያ ሐሙስ ሰንጋተራ በሚገኘው የኩባንያው ዋና መ/ቤት ውስጥ በተዘጋጀው ከገበሬው ቴክኖሎጂ ሶሉሽን  የምረቃ ሥነስርዓት ላይ ነው፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ መሥራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ፣ ኩባንያው ያበለፀጋቸውን ስድስት የቴክኖሎጂ መተግበሪያዎችን ያስተዋወቁ ሲሆን፤ ፐርፐዝ ብላክ በቀጣይ ወራት 24 የቴክኖሎጂ ፕላትፎርሞችን ተደራሽ እንደሚያደርግም አብስረዋል፡፡
ኩባንያው ትኩረቱን ቴክኖሎጂ ላይ ያደረገበትን ምክንያት ያስረዱት ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ፤ የTርTዝ ብላክ ኢትዮጵያ ትልቁ ዓላማው፣ የጥቁር ህዝቦች ኢኮኖሚ ልህቀትን መፍጠር በመሆኑ ነው ብለዋል፡፡
“TርTዝ ብላክ ኢትዮጵያ የንግድ አክሲዮን ማህበር፣ በዓለማቀፍ ደረጃ በጥቁር ህዝቦች ላይ ለዘመናት የቀጠለውን አድሎአዊ ሥርዓት በቢዝነስ ሞዴል በሚረጋገጥ የኢኮኖሚ የበላይነት ለማመዛዘን የተቋቋመ ኩባንያ ነው፡፡” ተብሏል፡፡
ባለፈው ሐሙስ በተካሄደው የከገበሬው ቴክኖሎጂ የምረቃ ስነስርዓት ላይ ስድስት የቴክኖሎጂ መተግበሪያዎች የተዋወቁ ሲሆን፤ ኩባንያው ከዚህ ቀደም ኢ-ኮሜርስ ማስተዋወቁ ይታወሳል፡፡በከገበሬው ቴክኖሎጂ ሶሉሽን አማካኝነት ከተዋወቁት መተግበሪያዎች ውስጥ “የከገበሬው የግብርና ምርቶች አቅርቦት” መተግበሪያ አንዱ ሲሆን፤ ገበሬው ከሸማቹ ጋር የሚገናኝበት መድረክ ነው ተብሏል፡፡“ገበሬዎች ምርታቸውን ከሸማቹ ጋር ማገናኘት አለመቻላቸው ነው ድሃ አድርጎ ያስቀራቸው” ያሉት ዶ/ር ፍስሃ፤ ይሄ የቴክኖሎጂ መተግበሪያ  ገበሬውን ከሸማቹ ጋር ያገናኘዋል ብለዋል፡፡
ሌላኛው መተግበሪያ “የከገበሬው ኮንስዩመር ብድር ማኔጅመንት” በሚል የሚታወቅ ሲሆን፤ ይህም ሸማቹ የብድር አገልግሎት የሚያገኝበት መድረክ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ሦስተኛው የቴክኖሎጂ መተግበሪያ የኢ-ለርኒንግ አስተዳደር ሥርዓት ነው ተብሏል፡፡ ከገበሬው ቴክኖሎጂ ሶሉሽን ምረቃን አስመልክቶ የተሰራጨው መረጃ እንደሚገልፀው ይህ መተግበሪያ፤ “በተለያዩ የትምህርት መስኮችና ከ77 በላይ የሚሆኑ ልዩ ልዩ የክህሎት ማበልፀጊያ ሥልጠናዎችን በበይነ መረብ አማካኝነት ባሉበት ሆነው መከታተልና አቅምን ማጎልበት የሚቻልበት ሲሆን፤ በሌላ በኩል ደግሞ በተለያየ መስክ እውቀትና ችሎታ ያላቸው ግለሰቦችም ዕውቀታቸውን የሚያጋሩበት ድረ ገፅ ነው፡፡” ከእነዚህ በተጨማሪ “የከገበሬው ቴሌቪዥን መረጃ ማሰራጫ”፣ እንዲሁም “የከገበሬው ኦርደር እና ዴሊቨሪ መቆጣጠሪያ” እና ሌሎች መተግበሪያዎች በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ ተዋውቀዋል፡፡
ኩባንያው በጥቂት ወራት ውስጥ የቴክኖሎጂ ፕላትፎርሞቹን ቁጥር 24 እንደሚያደርስ ያስታውቁት የፐርፐዝ ብላክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ፤ የኛ ዓላማ እነዚህን ፕላትፎርሞች የሁሉም የመገልገያ መድረክ ማድረግ ነው ብለዋል፡፡
TርTዝ ብላክ ኢትዮጵያ በሁለት ዓመት ውስጥ አድጎና አዋቂ ሆኖ ልጅ ለመውለድ በቅቷል ያሉት ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ፤ በቅርቡም 16 እህት ኩባንያዎችን እንደሚከፍት አስታውቀዋል፡፡
 ራዕዩ በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ተቀዳሚ የግብርና ምርት አቅራቢ መሆን እንደሆነ የሚገልፀው TርTዝ ብላክ፤ ተልዕኮው ደግሞ በኢትዮጵያ የኑሮ ውድነትን ታሪክ ማድረግ እንዲሁም ኢትዮጵያ ለሌሎች የአፍሪካ አገራትና ጥቁር ማህበረሰብ ለሚገኝባቸው አገራት የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የተነሳሽነት ምንጭና አርአያ መሆን ነው ይላል፡፡ 

Page 13 of 700