Administrator

Administrator

  የሰንበት ት/ቤቶቹ እንቅስቃሴያቸውን አጠናክረው እን
                         ‹‹መልካም ዜጋ የምታወጣው ተቋም በሙስና መጎዳቷ ለሀገርም ጉዳት ነው”፤ ወንጀሉ ላይ መንግሥት መዋቅሩን                         ጠብቆ ይገባል፤ በሃይማኖቱ መሸፈን አይችሉም››        ዶ/ር ሺፈራው ተክለ ማርያም


        ከመልካም አስተዳደር ዕጦት እና ከተጠያቂነት ሥርዐት መጥፋት ጋር በተያያዘ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር ውስጥ ሰፍኗል በተባለው ምዝበራ እና ሙስና  መንግሥት መዋቅሩን ጠብቆ ሕጋዊ ርምጃ እንደሚወስድ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ከትላንት በስቲያ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አመራሮች ጋር በተካሔደው ውይይት፣ መንግሥት ከሃይማኖት ተቋማት ጋር በሰላም እና በልማት ጉዳዮች ላይ አብሮ እንደሚሠራ የጠቀሱት የሚኒስቴሩ ከፍተኛ ሓላፊዎች፣ ‹‹ የሕዝብ ሀብት ለህዝብ ጥቅም መዋል አለበት፤ በሕዝብ ገንዘብ እንዲቀለድ አንፈልግም፤ መንግሥት ሰላምንና የሕግን የበላይነት ከማረጋገጥ አኳያ ደረጃውን ጠብቆና የሙስና ወንጀል መፈጸሙን አጣርቶ ርምጃ ይወስዳል፤›› ብለዋል፡፡
‹‹ሙዳየ ምጽዋቱን ማን ነው የሚጠቀምበት፤ ሕዝብ ይጥላል፤ ጥቂት ሰዎች መኪና እና ቤት ይሠሩበታል፤›› በማለት የአለመግባባት መንሥኤዎችን የዘረዘሩት ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ሙሉጌታ ውለታው፣ የሚዘርፉት ሃይማኖት ሳይኖራቸው በሃይማኖት ስም የሚነግዱ ግለሰቦች እና አካላት እንደኾኑ ገልጸዋል፡፡ በሚፈጽሟቸው ወንጀል ነክ ጉዳዮችም ‹‹መንግሥት ለምን ጣልቃ ይገባል አይባልም፤ ከሀገረ ስብከቱ ጋር ኾኖ ይከታተላል፤ ወንጀለኛውን ይይዛል፤ ይቀጣል፤ ያጸዳል፤›› ብለዋል፡፡
የግልጽነት እና የተጠያቂነት አሠራር ዘመኑ የሚጠይቀው እና መንግሥትም በአቋም ያስቀመጠው መኾኑን ያወሱት ሚኒስትር ዴኤታው፣ የሀገረ ስብከቱ ሰንበት ት/ቤቶች ሙስናና ብልሹ አሠራር እንዲወገድ፣ መልካም አስተዳደር እንዲሰፍንና ሃይማኖት እንዲጠበቅ የጀመሩትን እንቅስቃሴ አድንቀዋል፡፡ ‹‹እንቅስቃሴአችኹን ከሁከት በራቀ፣ ስልታዊ በኾነና በሰላማዊ መንገድ ቀጥሉ፤ መንግሥትም ድጋፍ ያደርግላችኋል፤›› ሲሉም አበረታተዋቸዋል፡፡
የሰንበት ት/ቤት አባላት ሰላም ፈላጊዎች እንደኾኑ የገለጹት የአንድነቱ አመራሮች በበኩላቸው፣ ለቤተ ክርስቲያን ሰላም መደፍረስ ዋነኛ ምንጩ የመልካም አስተዳደር ዕጦት እንደኾነ አስረድተዋል፡፡ እንደ አመራሮቹ፣ ቅዱስ ሲኖዶሱ እና ቅዱስ ፓትርያርኩ ሙስናንና ብልሹ አሠራርን ለማስወገድና ተቋማዊ ለውጥን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ውሳኔዎችን በየጊዜው ቢያሳልፉም ትግበራው አስተዳደራዊ መዋቅሩን ከላይ እስከ ታች በኔትወርኪንግ በተቆጣጠሩ ሙሰኞች ስለሚታገት ተፈጻሚ ለመኾን አልቻለም፡፡
ሙሰኞቹ÷ በሙዳየ ምጽዋት፣ በስእለትና በስጦታ ምእመኑ የሚሰጠውን ገንዘብ ለራሳቸው ዓላማና ጥቅም እያዋሉ፤ የአድባራቱን መሬትና ሕንፃ ከዋጋ በታች እያከራዩ በቤተ ክርስቲያኒቱ ጥቅሞችና መብቶች ከገቢያቸው በላይ ሕገ ወጥ ሀብት ያካብታሉ፤ በሦስትና በአራት ሺሕ ብር ደመወዝ ኤሮትራከር ይገዛሉ፤ ሕንፃ ይሠራሉ፡፡
ይኹንና የተጠያቂነትና የግልጽነት አሠራር ባለመኖሩ ሲነቃባቸውና ተቃውሞ ሲበረታባቸው የበለጠ ወደሚዘርፉበት ቦታ በዕድገት እንደሚዘዋወሩ ጠቅሰው፣ ለዚኽም በጎጠኝነትና በጥቅም ትስስር ተሞልቷል ያሉት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ፅ/ቤት ተጠያቂ ነው ብለዋል፡፡ “ሀገረ ስብከቱ ሌባን አሳልፎ አይሰጥም፤ በሹመት እና በዝውውር ጉቦ እየተከፈለ አብሮ ይበላል፤” በማለት የወቀሱት አመራሮቹ፣ “የሕዝብ ንብረት እየባከነ ስለኾነ መንግሥት ጣልቃ ይግባልን፤ የመንግሥት ባለሥልጣናት ሀብታቸው ተሰፍሮ ተቆጥሮ ይታወቃል፤ አሠራሩ እዚኽም ይምጣልን፤” ሲሉ አመልክተዋል፡፡
ሙሰኞችን በመቃወማቸውና እውነቱን በመናገራቸው አሸባሪዎች ተብለው ለእስር እንደሚዳረጉ  አመራሮቹ ጠቁመው፣  የጸጥታ አካላት ርምጃ ከመውሰዳቸው በፊት ኹኔታቸውን በሚገባ እንዲያጣሩና ፍትሐዊ አሠራር እንዲከተሉ ጠይቀዋል። ከአስተምህሮ ውጭ የኾኑ ግለሰቦችን የማጋለጥ ድርሻ የእነርሱ መኾኑን ገልጸው፣ በዚኽም በአክራሪነት መፈረጃቸው አግባብነት እንደሌለው ተናግረዋል፡፡
“አክራሪነትና ጽንፈኝነት በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ መኖሩ የሚያከራክር አይደለም፤” ያሉት ሚኒስትሩ ዶ/ር ሺፈራው ተክለ ማርያም፣ ኾኖም ጥያቄው በሃይማኖት አጥባቂነት እስከተነሣ ድረስ ከአክራሪነት ስለሚያርቅና ከሙስና ስለሚጠብቅ የሚደገፍ መሆኑን ጠቁመው የፍረጃው አካሔድ ስሕተት መኾኑን አብራርተዋል። እንደ ሚኒስትሩ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ የማይፈቅደውን የአክራሪነት አስተሳሰብና ተግባር በሃይማኖት ሽፋን የሚያራምዱ ግለሰቦች ለተቋሙ ደኅንነት ሲባል መለየት አለባቸው፡፡
ሕዝብ ከተግባርም እንደሚማር ዶ/ር ሺፈራው ገልጸው፣ አትስረቅ እያሉ በሌላቸው ገቢ የሚልዮን ብር መኪኖችን የሚነዱ አካላት፣ ለሀገር መልካም ዜጋ የምታወጣውን ተቋም በማማሰን በሕዝብ ላይ ተጽዕኖ እየፈጠሩ ናቸው ብለዋል፡፡ ይህም ለሀገር የሚጎዳ በመኾኑ ድንጋይ በመወርወር ሳይኾን በምእምኑ ሰላማዊ እንቅስቃሴ በቀጣይነት መጋለጥ እንደሚገባቸው መክረዋል፤ የሰንበት ት/ቤት አባላትም ከቤተ ክርስቲያኒቷ አልፎ ለሀገርና ለዓለም የሚበቁ ሊቃውንቷን በማስተባበር ለመልካም አስተዳደር መስፈን የሚያደርጉትን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል፤ መንግሥትም ‹‹መዋቅሩን ጠብቆ በወንጀሉ ላይ ይገባል፤ በሕግም ይጠይቃቸዋል፤ በሃይማኖቱ መሸፈን አይችሉ፤›› ሲሉ አስታውቀዋል፡፡
በሚኒስቴሩ የስብሰባ አዳራሽ በተደረገው በዚኹ የግማሽ ቀን ምክክር ማጠናቀቂያ ላይ፣ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የዋና ክፍል ሓላፊዎች የተገኙ ሲኾን ሚኒስትሩም “የወጣቶቹን ጥያቄ እንደ ቀላል አትዩት፤ በአስቸኳይ ፍቱ” ሲሏቸው ተደምጠዋል፡፡
ቀደም ሲል ሚኒስቴሩ፣ ከሀገረ ስብከቱ የአድባራት አለቆች፣ ካህናት እና ሰባክያነ ወንጌል ጋር ተመሳሳይ ምክክር ያደረገ ሲሆን፤ ይኸውም በቅርቡ በሃይማኖት ተቋማት በሰላም አብሮ መኖር እና ጤናማ ግንኙነቶች ማስፈንን በተመለከተ በጋራ እንደሚካሔድ ለሚጠበቀው ውይይት ቅድመ ዝግጅት እንደኾነ ተጠቁሟል፡፡

የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር በአገር አቀፍ ደረጃ የንባብ ባህል እንዲዳብር “ከመንግሥት እና ከባለድርሻ አካላት ምን ይጠበቃል?” ለሚለው ጥያቄ መልስ ለመስጠት የሚያስችል አውደ ጥናት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ሥነ - ፅሁፍና ፎክሎር ትምህርት ክፍል ጋር በመተባበር በትላንትናው ዕለት በብሄራዊ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መፃህፍት ኤጀንሲ አዳራሽ አውደ ጥናት አካሂዷል፡፡ በአውደ ጥናቱ ላይ አቶ ደረጀ ገብሬ (ረ/ፕ) “የንባብ ባህልን ለማዳበር የባለድርሻ አካላት ሚና” በሚል ርዕስ እንዲሁም ዶ/ር ሙሉ ሰው አስራቴ፤ “የልሳነ ብዙ የቋንቋ ትምህርትና ፖሊሲ የንባብ ባህልን ለማዳበር የሚኖረው ተግዳሮት እና ዕድል” በሚል ርዕስ የውይይት መነሻ ሃሳቦችን ማቅረባቸው ታውቋል፡፡

  በአሌክስ አብርሐም በተፃፈው “ዶ/ር አሸብር” የተሰኘው የወግ ስብስቦች መፅሃፍ ላይ በነገው ዕለት ከ8 ሰዓት ጀምሮ በወ-መዘክር አዳራሽ ውይይት ይካሄዳል፡፡ ለውይይት መነሻ የሚሆን ሃሳብ የሚያቀርበው ደራሲና ጋዜጠኛ አለማየሁ ገላጋይ ነው ተብሏል፡፡
የመፅሃፍ ውይይቱ እናት ማስታወቂያ፣ የጀርመን የባህል ማዕከልና ወመዘክር በጋራ የሚያዘጋጁት እንደሆነ ታውቋል፡፡

በሰለሞን ተሾመ ባዬ የተዘጋጀው “ፎክሎር ምንነቱና የጥናቱ የትኩረት አቅጣጫ” የተሰኘ መፅሃፍ የፊታችን ሐሙስ ከቀኑ 10 ሰዓት በብሄራዊ ሙዚየም እንደሚመረቅ ተገለፀ፡፡ በምረቃ ሥነ - ሥርዓቱ ላይ የተለያዩ ምሁራን የውይይት ሃሳብ የሚያቀርቡ ሲሆን ምሁራኑ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ፣ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዘሪሁን አስፋው፣ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራና አቶ እንዳለ ጌታ ከበደ እንደሆኑ ታውቋል፡፡ የመፅሀፉ ይዘት፡- የፎክሎር ፅንሰሀሳብን በሳይንሳዊ መንገድ ማብራራት፣ በአገራችን የሚገኙ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ያላቸውን ቃላዊ፣ ቁሳዊና መንፈሳዊ ባህሎችን መሰረት ያደረገ ትንተና መስጠት እና ሌሎችን ያካትታል ተብሏል፡፡ በ335 ገፆች የተዘጋጀው መፅሀፉ፤ በ120 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

ነፃነት ኪዳነማርያም የተፃፈው “የአሥመራው ታዳኝ” የተሰኘ ታሪካዊ ልብወለድ መፅሃፍ በነገው ዕለት ከጠዋቱ 3 ሰዓት ላይ መስቀል አደባባይ በሚገኘው ኢዮሐ ሲኒማ ይመረቃል፡፡ የመፅሀፉ ዋጋ 60 ብር እንደሆነ ታውቋል፡፡ ደራሲው ከዚህ ቀደም “ዋሻው” የተሰኘ ለአገሪቱ የመጀመሪያ የሆነውን የአኒሜሽን ፊቸር ፊልም ሰርቶ ለተመልካች ማቅረቡ ይታወሳል፡፡  

   በእስራኤል በዶክትሬት ዲግሪ የተመረቁ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ናቸው
    ኢትዮጵያዊው ምሁር ዶ/ር አንበሴ ተፈራ በእስራኤል የመጀመሪያው ከፍተኛ የዩኒቨርሲቲ መምህርና የፋካልቲ አባል በመሆን በቴል አቪቭ ዩኒቨርሲቲ ስራ መጀመራቸውን ጂዊሽ ኒውስ ድረገጽ ሰሞኑን ዘገበ፡፡
ዶ/ር አንበሴ በቴል አቪቭ ዩኒቨርሲቲ የእብራይስጥ ባህል ጥናት የትምህርት ክፍል የሴሜቲክ ቋንቋዎች ከፍተኛ መምህር ሆነው እያስተማሩ እንደሚገኙ የጠቆመው ዘገባው፣ ምሁሩ ከ15 አመታት በፊት የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ሲያገኙም በእስራኤል የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ እንደነበሩ አስታውሷል፡፡
በ1962 የተወለዱት ዶ/ር አንበሴ፤ የመጀመሪያና የሁለተኛ ዲግሪያቸውን በሊንጉስቲክስ በተቀበሉበት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለአምስት አመታት ያህል በመምህርነት ማገልገላቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ እየሩሳሌም ውስጥ ከሚገኘው ሂብሩ ዩኒቨርሲቲ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን መቀበላቸውንና በዩኒቨርሲቲው አማርኛ ቋንቋን ሲያስተምሩ እንደቆዩም አክሎ ገልጿል፡፡  
ዶ/ር አንበሴ፤ ሶስት መጽሃፍትንና ከ20 በላይ ጥናታዊ ጽሁፎችን ለህትመት ያበቁ ሲሆን፣ ከማስተማርና ከጥናትና ምርምር በተጨማሪም ለ13 አመታት ያህል ለእስራኤላውያን የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች አማርኛ ቋንቋን በማስተማርና በትምህርት ሚኒስቴር የአማርኛ ጥናቶች ብሄራዊ ሱፐርቫይዘር ሆነው በማገልገል እንደሚታወቁ ዘገባው ጠቁሟል፡፡

Saturday, 01 August 2015 14:06

በሚቀጥለው ቅዳሜ …

ወደ ኢትዮጵያ ጠቅልዬ ልመለስ ነው ስል በአሜሪካ ያሉ ሚዲያዎች መጥተው ነበር ቺካጐ ትሪቡን “አዲስ አበባ ዎን፤ ቺካጐ ሎስት” ብሎ ፅፏል በኢትዮጵያ በደቡብ በሸዋ፣ በጐንደር ገጠሮች 30 ት/ቤቶች አሠርቷል
በአያት አካባቢ ሪል ኢስቴት እየሠራ ነው “አይዞን” የተባለ 12 ዘፈን የያዘ አዲስ አልበሙን በቅርቡ ያወጣል
ጋንግስተሮች በ30 ሞተርሳይክሎች እያባረሩ ሊገሉት ሲሉ አምልጧልከአርቲስት ዘለቀ ገሠሠ ጋር ያደረግነውን ግሩም ቃለ ምልልስ በሚቀጥለው ሳምንት ያንብቡት  

 ምርጫው አገሪቱ በዴሞክራሲ መራመዷን ያሳያል ብለዋል
               - የዋነኛው ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ሌላ ምርጫ እንዲካሄድ ጠይቀዋል
   አወዛጋቢውና ደም አፋሳሹ የብሩንዲ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ባለፈው ማክሰኞ የተካሄደ ሲሆን ለመምረጥ ከተመዘገቡት 3.8 ሚሊዮን የአገሪቱ ዜጎች መካከል 74 በመቶው ድምጻቸውን እንደሰጡ የብሩንዲ የምርጫ ኮሚሽን ፕሬዚደንት ፔሪ ካልቬር ዳይካሬ ባለፈው ረቡዕ መናገራቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
ህገ መንግስቱ ከሚፈቅድላቸው ውጪ ለሶስተኛ ዙር የስልጣን ዘመን በምርጫ ለመወዳደር መወሰናቸው ከፍተኛ ተቃውሞ ያስነሳባቸው የብሩንዲው ፕሬዚዳንት ፔሪ ንኩሩንዚዛ፣ ሃሳባቸውን እንዲቀይሩ ጫና ቢደረግባቸውም በእምቢተኝነት በተወዳደሩበት ምርጫ ድምጽ የሰጡ ሲሆን ምርጫው ብሩንዲ በዲሞክራሲ አንድ እርምጃ ወደፊት መራመዷን የሚያሳይ ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡
የአገሪቱ ቀንደኛ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ የሆኑት አጋቶን ርዋሳ በበኩላቸው፣ አገሪቱ እንደ አገር እንድትቀጥልና የከፋ ደም መፋሰስ እንዳይከሰት ከተፈለገ፣ የምርጫው ውጤት ይፋ በተደረገ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ብሄራዊ የአንድነት መንግስት ሊያቋቁሙ ይገባል ሲሉ ለፕሬዚዳንት ንኩሩንዚዛ ጥሪያቸውን እንዳቀረቡ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
ምርጫው የአገሪቱ ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ራሳቸውን ባገለሉበት ሁኔታ የተከናወነ በመሆኑ አሳታፊ አይደለም ያሉት ርዋሳ፣ የሚቋቋመው ጊዜያዊ የብሄራዊ አንድነት መንግስት በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ሌላ ምርጫ እንዲያካሂድም ጠይቀዋል፡፡
አሜሪካ የመንግስት ሃይሎች ተቃዋሚዎችንና የሲቪክ ማህበራትን በሚያዋክቡበት፣ መገናኛ ብዙኃን በተዘጉበትና መራጮች በሚገደዱበት ሁኔታ የተደረገው የብሩንዲ ምርጫ ተዓማኒነት የለውም ማለቷን የዘገበው አሶሼትድ ፕሬስ፣ ካለፈው ሚያዝያ ወር ጀምሮ ምርጫው ባስነሳው ብጥብጥ ከ100 በላይ ዜጎች መሞታቸውንና ከ170 ሺህ በላይ የሚሆኑትም አገር ጥለው እንደተሰደዱ አስታውቋል፡፡
የተመድ ዋና ጸሃፊ ባንኪ ሙን በበኩላቸው፤የብሩንዲ የፖለቲካ ሃይሎች አገሪቱንና ህዝቧን ወደ ከፋ ጥፋት የሚያስገቡና በአካባቢው አለመረጋጋትን የሚያስከትሉ ተግባራትን ከመፈጸም እንዲታቀቡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በመዲናዋ ቡጁምቡራና በሌሎች የአገሪቱ አካባቢዎች በተቃዋሚዎችና በመንግስት ወታደሮች መካከል ግጭት በቀጠለበት ሁኔታ ማክሰኞ ዕለት የተከናወነው ምርጫ የድምጽ ቆጠራ ረቡዕ መጠናቀቁን የዘገበው አልጀዚራ፣ ፕሬዚዳንት ፔሪ ንኩሩንዚዛ በሰፊ ልዩነት ያሸንፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክቷል፡፡

  እ.ኤ.አ በ2050 ሮቦቶችንና ሰዎችን ኳስ ለማጋጠም ታቅዷል
    በቻይና በተከናወነውና 40 የአለማችን አገራት ቡድኖች በተካፈሉበት የዘንድሮው የአለም ሮቦቶች የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር ጃፓን ማሸነፏን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
በጃፓኑ ቺባ ኢንስቲቲዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ የተሰሩ ሮቦቶችን የያዘው ዘ ብሬንስ ኪድስ የተባለው የጃፓን የሮቦቶች ቡድን፣ የቻይናውን ዚጁዳንሰር አቻውን አንድ ለባዶ በማሸነፍ ነው ዋንጫውን ለመሳም የበቃው፡፡
የአለማችን ሮቦቶች የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር እ.ኤ.አ ከ1997 ጀምሮ በየአመቱ ሲከናወን እንደቆየ ያስታወሰው ዘገባው፣ በውድድሩ የሚሳተፉ አገራት ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱንም ጠቁሟል፡፡
የአለማችን ሮቦቶች የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር በሮቦቲክስ ዘርፍ የተሻለ ፈጠራን የማበረታታትና የማስፋፋት አላማ እንዳለው የጠቀሰው ዘገባው፣ እ.ኤ.አ በ2050 በሮቦቶችና በሰዎች መካከል የእግር ኳስ ውድድር የማካሄድ  እቅድ መያዙንም አክሎ ገልጧል፡፡

 የአንበሳ ጀግንነት ከአዳኝ ቀስት አያድነውም።
የአፍሪካውያን አባባል
ደስተኛ ህዝብ ታሪክ የለውም፡፡
የቤልጂየሞች አባባል
ጦርነት ላልቀመሱት ጣፋጭ ነው፡፡
የላቲኖች አባባል
ሽንፈት የሚመረው ስትውጠው ብቻ ነው፡፡
የቻይናውያን አባባል
እውነት የያዘን ሆድ በበላ እንኳን አይበሱትም፡፡
የሃውሳ አባባል
እሳት ያቃጠለው ሰው ሁልጊዜ አመድ ያስፈራዋል፡፡
የሶማሌያውያን አባባል
መጥበሻው ካልጋለ ማሽላው አይፈነዳም፡፡
የዮሩባ አባባል
ዝሆን ላይ የሚጮህ ሞኝ ውሻ ብቻ ነው፡፡
የአንጎላውያን አባባል
በግድ ድስት ውስጥ የገባ አጥንት ድስቱን መስመሩ አይቀርም፡፡
የቼዋ አባባል
አይጥ የገደለ ዝሆን ጀግና አይባልም፡፡
የካሜሩያውያን አባባል
ትዕግስት የገነት ቁልፍ ነው፡፡
የአልባንያውያን አባባል
ቤትህን ከመምረጥህ በፊት ጎረቤትህን ምረጥ፡፡
የሶሪያውያን አባባል
ፈረሱ ከሚጠፋ ኮርቻው ይጥፋ፡፡
የጣልያኖች አባባል
ምንም ዓይነት ምስጢርህን ከራስህ አትደብቅ፡፡
የግሪካውያን አባባል
የሥራ ፈት ምላስ ፈፅሞ ሥራ አይፈታም፡፡
የአፍሪካውያን አባባል