Administrator

Administrator

ለአራተኛ ጊዜ የሚካሄደውና ለሀገራቸውና ለወገናቸው ላቅ ያለ አገልግሎት የሰጡ ዜጎች የሚከበሩበት የዓመቱ በጎ ሰው ሽልማት ሥነሥርዓት ነሐሴ 28 ቀን 2008 ዓ.ም በአዲስ አበባ አቤል ሲኒማ ይከናወናል፡፡
በ10 ዘርፎች ለ2008 የዓመቱ በጎ ሰው ሽልማት መብቃት አለባቸው የተባሉ ዜጎች በሕዝቡ የተጠቀሙ ሲሆን በየዘርፉ ከተጠቆሙት ዜጎች መካከልም ሥራዎቻቸው ተመዝነው በሽልማት ኮሚቴው አማካኝነት ሦስት ሦስት ዕጩዎች ተለይተዋል፡፡
በእነዚህ እጩዎች ላይ አምስት አምስት ዳኞች (በየዘርፉ) ድምጽ እየሰጡ መሆኑ የታወቀ ሲሆን የየዘርፉ ተሸላሚዎችም ነሐሴ 28 ቀን 2008 ዓ.ም በሚኖረው ሥነ ሥርዓት ይታወቃሉ ተብሏል። ሚዲያዎችና ሌሎች የመገናኛ አካላት፣እጩዎችን በማስተዋወቅና በማክበር፣ ለሀገራቸው በጎ የሚሠሩ ዜጎችን ለማብዛት የበኩላቸውን እንዲወጡ የበጎ ሰው ሽልማት ኮሚቴ ጠይቋል፡፡ ከዚህ በታች እጩዎቹ በየዘርፋቸው ቀርበዋል፡፡
መምህርነት
ተ/ ፕሮፌሰር ዘሪሁን አስፋው
ተ/ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና
መ/ር አውራሪስ ተገኝ
ንግድና ሥራ ፈጠራ
አቶ ብዙአየሁ ታደለ
አቶ ሳሙኤል ታፈሰ
አቶ ኢየሱስ ወርቅ ዛፉ
ማኅበራዊ ጥናት
ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ
ዶክተር አንዳርጋቸው ጥሩነህ
ፕሮፌሰር ባየ ይማም
ሳይንስ
ሎሬት ዶክተር መላኩ ወረደ
ዶክተር ዓለማየሁ ዋሴ
ዶክተር ውዱ ዓለማየሁ
ቅርስና ባሕል
የኢትዮጵያ ጥናት ተቋም (አዲስ አበባ     
           ዩኒቨርሲቲ)
ኢንጅነር ታደለ ብጡል
መ/ር ካሕሳይ ገብረ እግዚአብሔር
መንግሥታዊ የሥራ ኃላፊነትን በብቃት መወጣት
ኢንጅነር ዘውዴ ተክሉ
ዶክተር ተወልደ ብርሃን
          ገብረእግዚአብሔር
ዳኛ ስንታየሁ ዘለቀ
ስፖርት
አቶ ጌቱ በቀለ
ጋቶች ፓኖ
ዶክተር ይልማ በርታ
ኪነጥበብ (ድርሰት)
አቶ አስፋው ዳምጤ
ወ/ሮ ፀሐይ መላኩ
አቶ አውግቸው ተረፈ
ሚዲያና ጋዜጠኛነት
መንሱር አብዱልቀኒ
አቶ አጥናፍሰገድ ይልማ
አቶ ደረጀ ኃይሌ
በጎ አድራጎት
ዶክተር ቦጋለች ገብሬ
ወ/ሮ ፀሐይ ሮቺሊ
ወ/ሮ ዘውዲቱ መሸሻ

ቶታል ኢትዮጵያ ከኤም ብር ጋር በመተባበር አዲስ የተቀላጠፈ የሞባይል ክፍያ አሰራር መተግበር የጀመረ ሲሆን ደንበኞች ካሉበት ሆነው የድርጅቱን አጠቃላይ አገልግሎቶች በተመለከተ የተሟላ መረጃ የሚያገኙበት “ቶታል ሰርቪስስ” የተባለ አዲስ የሞባይል ስልክ አፕሊኬሽንም አስመርቋል፡፡
የቶታል ኢትዮጵያ የሽያጭና የማርኬቲንግ ስራ አስኪያጅ ክሪስቶፊ ፌራንድ ባለፈው ረቡዕ በተከናወነው የምረቃ ስነስርዓት ላይ እንዳሉት፣የሞባይል ክፍያ አሰራሩ የኩባንያው ደንበኞች በማንኛውም ጊዜ የተለያዩ ክፍያዎችን መፈጸም፣ ገንዘብ መላክ፣ የሞባይል ካርድ መግዛት፣ ገንዘብ ማስቀመጥ ወይም ማውጣትና መገበያየት የሚችሉበት ነው፡፡
የኩባንያው ደንበኞች በተመረጡ የቶታል ማደያዎች ይህን አስተማማኝ፣ ጊዜ ቆጣቢና ቀልጣፋ የሞባይል ክፍያ ዘዴ በመጠቀም ነዳጅ መግዛት፣ መኪና ማሳጠብ፣ የመኪና ዘይት መግዛት፣ የሱፐር ማርኬትና የካፌ አገልግሎቶችን መጠቀም ወዘተ ይችላሉ ያሉት ዳይሬክተሩ፤በቅርቡም ይህን አገልግሎት በሁሉም የቶታል ማደያዎች ለማስጀመር እየተሰራ እንደሚገን አስታውቀዋል። ቶታል ኢትዮጵያ ከዚህ በተጨማሪም ለደንበኞቹ ያለውን ተደራሽነት ለማስፋት በማሰብ፣ ደንበኞች ካሉበት ሆነው የሞባይል ስልኮቻቸውን በመጠቀም የድርጅቱን አገልግሎቶች በተመለከተ የተለያዩ መረጃዎችን ማግኘት የሚችሉበትን ቶታል ሰርቪስስ የተባለ አዲስ የሞባይል ስልክ አፕሊኬሽን አስመርቋል፡፡  
አዲሱ የሞባይል አፕሊኬሽን፣ የቶታል ኢትዮጵያ ደንበኞች ባሉበት ሆነው በስልኮቻቸው አማካይነት ያለ ውጣ ውረድ በአቅራቢያቸው  የሚገኘውን የቶታል ማደያ ለማወቅና የሚሰጡ አገልግሎቶችን የተመለከቱ መረጃዎችን ለማግኘት የሚችሉበት ነው፡፡ ደንበኞች አዲሱን የቶታል ሰርቪስስ የሞባይል አፕሊኬሽን፣ ከጎግል ስቶር ላይ ማውረድ እንደሚችሉ በመጠቆም፣ ቶታል ኢትዩጵያ ለደንበኞቹ ያለውን ተደራሽነት ለማሳደግ ትኩረት በመስጠት በፀሐይ ብርሀን የሚሠሩ መብራቶች በማደያው እንዲሁም በህዳሴ ሱቆች ላይ ማቅረቡንም አስታውሰዋል፡፡
ኤምብር በአገሪቱ የሚገኙ አምስት ታላላቅ የብድርና ቁጠባ ተቋማትን በማቀፍ የጀመረውን ዘርፈ ብዙ የሞባይል የፋይናንስ አገልግሎት በማስፋፋትና የደንበኞቹን ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ በማሳደግ፣ የተቀላጠፈ አገልግሎቱን በስፋት እየሰጠ እንደሚገኝም በምረቃ ስነስርአቱ ላይ ተገልጧል፡፡

 - ያለቅጥ ወፍራችኋል፤ ሸንቀጥ እስክትሉ ህዝብ ፊት አትቀርቡም ተብለዋል
   የግብጽ መንግስት የብሮድካስቲንግ ተቋም የሆነው “ኢርቱ”፤8 ሴት የአገሪቱ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋዜጠኞችን “ያለቅጥ ወፍራችኋል፣ የምትመገቡትን ምግብ መጠን ቀንሳችሁ እስክትከሱና ሸንቀጥ እስክትሉ ድረስ ከህዝብ ፊት አትቀርቡም” በሚል ለአንድ ወር ያህል ጊዜ ከስራ ማገዱን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
“ዘ ኢጂፕሺያን ሬዲዮ ኤንድ ቴሌቪዥን ዩኒየን” የተባለው ተቋም ይሄን አስቀያሚ ውፍረታችሁን ይዛችሁ ከተመልካች ፊት አትቀርቡም በሚል በጋዜጠኞቹ ላይ የወሰደው ከስራ የማገድ እርምጃ፣የሴቶች መብቶች ተከራካሪ ቡድኖችን ማስቆጣቱን ዘገባው ጠቁሟል፡፡
“ዘ ውሜንስ ሴንተር ፎር ጋይዳንስ ኤንድ ሌጋል አዌርነስ” የተባለው የአገሪቱ የሴቶች መብት ተከራካሪ ቡድን፣ ውሳኔው ህገ-መንግስትን የሚጥስና በግብጻውያን ሴቶች ላይ የተቃጣ ጾታዊ ጥቃት ነው ሲል ተቃውሞውን በማሰማት ውሳኔው እንዲሻር ጥያቄ ማቅረቡን ዘገባው አመልክቷል፡፡ ጥያቄው የቀረበለት ተቋም ግን ውሳኔው በምንም አይነት መንገድ እንደማይሻር ማስታወቁን ቬቶ ኒውስ የተባለው የግብጽ ድረገጽ የዘገበ ሲሆን፣ የአገሪቱ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማትና ጋዜጠኞች በጉዳዩ ዙሪያ እየተከራከሩ እንደሚገኙም ተነግሯል፡፡

   በቅርቡ ከተቃጣበት የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ጋር በተያያዘ ከ26 ሺህ በላይ ዜጎችን ያሰረው የቱርክ መንግስት፣ ባጋጠመው የእስር ቤቶች መጨናነቅ ሳቢያ፣ ከመፈንቅለ መንግስቱ ጋር ባልተያያዙ ወንጀሎች የታሰሩ ነባር 38 ሺህ ያህል እስረኞችን ሰሞኑን እንደሚፈታ ማስታወቁን ሮይተርስ ዘገበ፡፡
ፕሬዚዳንት ጣይብ ኤርዶጋንን ከስልጣን ለማስወገድ የተካሄደው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ መክሸፉን ተከትሎ የአገሪቱ ፖሊስ በርካታ ቁጥር ያላቸውን ዜጎቹን እያፈሰ ወደ እስር ቤቶች ማጋዙ በእስር ቤቶች ላይ ከፍተኛ መጨናነቅ መፍጠሩን የጠቆመው ዘገባው፤የአገሪቱ የፍትህ ሚኒስትር በኪር ቦዝዳግ፣ ችግሩን ለመፍታት በማሰብ 38 ሺህ እስረኞችን ለመፍታት መወሰናቸውን እንዳስታወቁ ገልጧል፡፡በተለያዩ የወንጀል ክሶች ተጠርጥረው የታሰሩት እነዚህ 38 ሺህ እስረኞች ከእስር ይለቀቁ እንጂ ምህረት አልተደረገላቸውም ያሉት ሚኒስትሩ፤ ጉዳያቸው በፍርድ ቤት ተመርምሮ ተገቢው ቅጣት እንደሚጣልባቸው ማስታወቃቸውን ዘገባው አስረድቷል፡፡

ለአመታት በእርስ በርስ ጦርነት ስትታመስ የቆየችው የመን በመሰረተ ልማት አውታሮች ላይ በደረሰ ውድመትና በኢኮኖሚ ድቀት ሳቢያ በድምሩ 14 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ እንደደረሰባት ሮይተርስ ዘገበ፡፡
በየመን ላለፉት 16 ወራት በዘለቀው የእርስ በእርስ ጦርነት ከ6 ሺህ 500 በላይ ሰዎች ለህልፈተ ህይወት መዳረጋቸውንና ከ2.5 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ማፈናቀሉን የሚጠቁም ይፋ ያልሆነ ሪፖርት ማግኘቱን ያስታወቀው ሮይተርስ፤ከግማሽ በላይ የሚሆነው ህዝቧም የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ተጠቂ መሆኑን ጠቁሟል፡፡ በአገሪቱ የእርስ በርስ ጦርነት ሳቢያ በርካታ መሰረተ ልማቶች መውደማቸውንና የኢኮኖሚ ድቀት መድረሱን የጠቆመው ዘገባው፤በአገሪቱ የሚገኙ 1 ሺህ 671 ትምህርት ቤቶች መውደማቸውንና ውድመቱ 269 ሚሊዮን ዶላር ይደርሳል ተብሎ እንደሚገመት አስረድቷል፡፡
የህክምና አገልግሎት ሲሰጡ ከነበሩ የአገሪቱ 3 ሺህ 652 ተቋማት መካከል 900 ያህሉ አገልግሎት መስጠት ማቆማቸውን የገለጸው ዘገባው፤በዚህም 2.6 ሚሊዮን የአገሪቱ ህጻናት ለበሽታ የመጋለጥ አደጋ ላይ መውደቃቸውን አስረድቷል፡፡

    ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ጌታውን ወደ ጦር ሜዳ የሚወስድ ፈረስ ነበረ፡፡ ከጊዜ በኋላ ፈረሱ ማርጀቱ እየተሰማው መጣ፡፡ ፈረሱ በራሱ ጊዜ ለጌታው ማገልገሉን ትቶ የወፍጮ ቤት አገልጋይ ብሆን፤ ምናለበት ብሎ አሰበና ወደ ወፍጮ ቤት ለመቀጠር ሄደ፡፡ ባለወፍጮ ቤቶቹ፤ ‹‹ወደዚህ ለምን መጣህ?›› ሲሉ ጠየቁት፡፡ ፈረሱም፤ ‹‹እድሜዬ አረጀ፤ ቀጣዩን ዕድሜዬን የአሁኑን ማንነቴን ማረጋገጫ ማድረግ አለብኝ፤ ራሴን፣ የትላንት ማንነቴን ማረጋገጥ ማለትም፤ ይሄ ነው፡፡ ለፈረሱ፤ የወፍጮ ቤቱ ሕይወት እምብዛም ማራኪ አልሆነለትም፡፡ እንደ ከበሮው ምቱን ማጣጣም አልቻለም፡፡ ይልቁንም እያንዳንዷን እህል ለማድቀቅ፣ የእሱ የባርነት ጉልበት አስፈላጊ ሆነ፡፡ ኩራት ቀረ፡፡ ያም ሆኖ የዚህን ሥራውን ክብደት መሠረት አድርጎ፣ የበቆሎ መፍጨት ሥራውን መቀጠል ግድ ሆነበት፡፡ ‹‹ያገለገለ ፈረስ ሁሉ ወፍጮ ቤት እንዲሄድ አይመከርም!›› ይላሉ አዋቂዎች፡፡ ፈረሱ ግን ይሄ ፍልስፍና አልተዋጠለትም፡፡ ይህን ከባድ ሥራ ብሎ በወጉ ያስተዋለው ይህ ጉልበተኛ ፈረስ፤ ‹‹ጌታዬ! ከዕለታት አንድ ቀን፤ እኔ በጦርነት ቦታ ስመ ጥር አርበኛ ነበርኩ፡፡ ሴት ወንዱ እኔን ለማየት ከየቤቱ ወጥቶ አድናቆቱን ሲገልጥልኝ ከርሟል፡፡ የዛሬው የእኔ ቅርፅና መልክ ከዱሮው
በጣም የተለየ ሆኗል! ጦር ሜዳውን ትቼ ወደ ወፍጮ ቤት መምጣቴ ዛሬ በጣም ፀፅቶኛል፡፡አለው፡፡ባለ ወፍጮ ቤቱም እንዲህ አለው፤ ‹‹ስለትላንት መፀፀት ምንም ፋይዳ የለውም፡፡ ንብረትና ባለፀግነት፤ አያሌ ላይና ታች፣ ክፉ የጥረት ውጣ-ወረድ፣ በእጅህ ሊኖር ግድ ነው! መጠንቀቅ የራሳችን ዋና ጉዳይ ነው፡፡ ሁሉንም ነገር እንዳመጣጡ እንቀበለው፡፡ አንድ ወቅት ፈረሰኛ ነበርክ፤ አሁን ወፍጮ አስፈጪ ሆነሃል፡፡ ነገ ምን እንደምትሆን አይታወቅም፡፡ ሆኖም ነገንም በሰላም ለመቀበል ዝግጁ ሁን›› አለው፡፡

    …
የአገራችን ሁኔታ ወደድንም፣ ጠላንም አሳሳቢ ነው! ነገ ምንም ይምጣ ምን ለመቀበል ዝግጁ መሆን አለብን፡፡ ቀውጥ እና ነውጥ ነገ የዕለት ሁኔታ ሊሆን ይችላል፡፡ ‹‹ኃይል ሁልጊዜ አያበላም››፤ ይላሉ አበው፡፡ ምክንያቱም ውሎ አድሮ ኃይል የለሹ ኃይለኛ ሊሆን ይችላልና ነው፡፡ ሰላም ያለ ተግባር ግልፅ አይደለም - አይገባም፡፡ ሰላምን ለማምጣት ሰላም- ለሚያሳጡ ጥያቄዎች መልስ መስጠት ግዴታ ነው፡፡ ጥንት የመንግሥት ለውጥ በተደረገ ማግሥት፤ አንድ መሰረታዊ ነገር በሃገሪቱ መሪ ተነግሮ ነበር፡፡ ‹‹ከእንግዲህ በኢትዮጵያ ምድር አንዲት ጥይት አትጮህም›› ተብሎ ነበር፡፡ ከዚያ ወዲያ የተከተለው ነገር ሁሉ ግን፤ ግምቱንና ትንበያውን ያስተባበለ ነው፡፡ በከፊል ከማህበረሰቡ፣ በከፊል ደግሞ ከመንግስት በመነጨ ግጭት፤ ‹‹የአንድ ጥይት- አይጮህም›› ፅንሰ- ሃሳብ እንደ ከሸፈ ጥይት መሆኑ በይፋ ታይቷል፡፡ ከዚያም አልፎ ተርፎ፤ ሀሳብን መግለፅ መታቀቡ የልብን መናገር አለመቻሉ፤ ለአንድ ሀገር ፍፁም አደጋ ነው። ‹‹ተናግሮ የትም አይደርስም›› ከሚል አምባገነናዊ ዕብሪት፤ እስከ  ‹‹እኔ እያወኩለት ምን ነገር ያስባዝተዋል›› እስከሚል ክልከላ ድረስ፤ ኢ-ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ መንሰራፋቱ ስህተት ላይ እንዳይጥለን መጠንቀቅ፤ እጅግ በጣም ወሳኝ
ነው! ሥራ- እጥነት አፍጦብናል። የኑሮ ውድነት የጥንቆላ ሳይሆን ነባራዊ ዕውነታ ነው፡፡ የቸገረው ሰው ጥያቄ ሲያነሳ መልስ እንጂ የነገ-ያልፍልሃል ራዕይ አያፅናናውም! በኃይል ሊገደብ ሲሞከር ደግሞ የባሰ ጥፋት ነው! ለማናቸውም ጥያቄ ህጋዊ መልስ ያስፈልገዋል የሚል መንግሥት፤ ህጋዊ ተቃውሞን አይንቅም። ማናቸውንም መሬት የያዘ እንቅስቃሴም ‹‹ከጀርባው የውጪ ኃይል አለበት››፣ ‹‹የአመለካከት ህፀፅ ነው››፣ ‹‹እኛ ከተነሳንበት ሀገራዊ ዓላማ ተፃራሪ ነው››፣ ‹‹ባለቤት የለውም›› ወዘተ በማለት ችግሩን እንዳናይ ሊያውረን አይገባም!! እሳት እየተቀጣጠለ እያለ፤ ‹‹እሳት የለም›› ብሎ መካድ ሳይሆን፤ አንድም እሳቱን የሚያቀጣጥሉ ኃይሎችን ልብ ብሎ ለይቶ መጠበቅና ተገቢ እርምጃ መውሰድ፤ ሁለትም ነገሩ ከቁጥጥር ውጪ እንዳይሆን በወቅቱ የእሳት አደጋ ሰራተኛ
መመደብና ረጋ ብሎ ማሰብ፤ ያሻል፡፡
ከዚህ ሁሉ ባሻገር ደግሞ፤ “እኔ ብቻ ነኝ እሳቱን የማጠፋው” ብሎ ግትር ከማለት ይልቅ፤ ሌላም ለሀገር የሚቆረቆር ዜጋ አለ ብሎ ማመን ዋና ነገር ነው! የፀጥታ ኃይሎችን አቅም ከማባከን ህዝቡበሰላማዊ መንገድ አስቦ፣ ተሳስቦ፣ መፍትሔ እንዲፈልግ መላ መምታት የተሻለ ነው፡፡መስማት የሚፈለገውን ድምፅ ብቻ የሚናገሩ ማህበረሰቦችን መሰብሰብ በኃይለስላሴም፣ በደርግም፣ አሁንም አላዋጣም፤ አያዋጣምም! በመሠረቱ ሀገራችን መበታተን የለባትም የሚለው የሁላችንም መፈክር ነው፡፡ የሥልጣን ክፍፍል፣ የሀብት ክፍፍል ማመላከቻ መሆን የለበትም፡፡ ባለሙያን እናክብር! ከሥር ያመረቀዘው ቁስል እስኪፈነዳ ጊዜ በሰጠን ቁጥር የህላዌ ገመዳችን እየሰለሰለ እንደሚሄድ አንዘንጋ፡፡ አንድ በሳል ፀሐፊ ስለ ኢህአዴግ መንግሥት አተያይ ሲሰጥ፤ ‹‹እኛ ስፉ እንጂ ጥፉ አንልም›› ይላል፡፡ ልብ ያለው ልብ ይበል! ራስን አለማሞኘት የችግራችን ግማሽ መፍትሔ ነው፡፡ ፅንፈኝነትን ግን አውቆ፣ ነቅቶ፣ በቅቶ መከላከል፣ ግዴታ ነው፡፡ ሆኖም እክሉን ለማስወገድ ከራስ መጀመር አሌ የማይባል ጉዳይ ነው! የችግር ሁሉ አዋቂ እኔ፣ መፍትሔውም እኔ ማለት፤ L’etat, c’est moi›› (መንግስትማ እኔ ራሴ ነኝ እንደማለት) እንዳለው የፈረንሳይ መሪ፤ አባዜ ይፈጥራል፡፡ ደርግ የሰራው ስህተት ሳናውቀው
እንዳይበክለን ማስተዋል እጅግ ብልህ ያደርገናል! ገለልተኛ የፓለቲካ ሂደት እንዲፈጠር መጣጣር
ወሳኝ ነው፡፡ አንዘናጋ! መምከርና መመካከር ዛሬ የማይታለፍ እርምጃ ነው! ብልህነት ነው!
የማንነት ጥያቄ ክስተት ሳይሆን በማናቸውም ጊዜ ህዝብ ሊጠይቀው የሚችል የለውጥ ነፀብራቅ ነው፡፡ ትልቁ ቁም ነገር በኃይል ሳይሆን በአግባቡ ጉዳዩን ማጤን ነው፡፡ ለመወያየት ዝግጁ መሆን ነው! ሁኔታዎችን እንደ ህዝብ ስሜት መከተል፤ ትላንትም፣ ዛሬም፣ ነገም ያለና የሚቀጥል ዕውነታዊ
ግዴታ ነው፡፡ እንደ ህዝቡ ዋና ስሜት ለመጓዝ እናስብ፡፡ ‹‹ሰው ቢለብስ እንደ አየሩ፤ ወፍ ቢጮህ
እንዳገሩ›› የሚለውን ተረት መቼም አንርሳ!

ቶሮንቶ ዩኒቨርሲቲ ዘንድሮ የግዕዝ ትምህርት ለመጀመር አስቧል
    ፎርብስ መጽሄት በቅርቡ ባወጣው የ2016 የአለማችን ከፍተኛ ተከፋይ ዝነኞች ዝርዝር ውስጥ የተካተተውና የወቅቱ የአለማችን የሙዚቃ ኮከብ እንደሆነ የሚነገርለት ትውልደ ኢትዮጵያዊው አቤል ተስፋዬ፣ በካናዳ በሚገኘው ቶሮንቶ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናት ፕሮግራም ለማስጀመር የሚያግዝ 50 ሺህ ዶላር (1.2 ሚ ብር ገደማ) በስጦታ ማበርከቱ ተዘገበ፡፡
የግራሚ ተሸላሚው ድምጻዊ አቤል ተስፋዬ፤ ቢቂላ አዋርድስ ከተባለ የኢትዮጵያውያን ማህበረሰብ ተቋም የቀረበለትን የገንዘብ ድጋፍ ጥያቄ በመቀበል ስጦታውን ያበረከተ ሲሆን፣ ተቋሙ በድምጻዊው ፈጣን ምላሽ መደነቁንና የገንዘብ ድጋፉ ባህላችንን ለመጠበቅና ለተቀረው አለም ለማስተዋወቅ አስተዋጽኦ ያበረክታል ሲል ምስጋናውን ማቅረቡን ዘ ቶሮንቶ ስታር ዘግቧል፡፡
“እጅግ ድንቁንና ጥንታዊውን የኢትዮጵያ ታሪክ ለተቀረው አለም ልናስተዋውቅ ነው፡፡ በካናዳ የኢትዮጵያ ጥናት ፕሮግራምን ለማስጀመር በሚደረገው ጥረት የበኩሌን ድጋፍ ለማድረግ በመቻሌ ኩራት ይሰማኛል” ሲል በትዊትር ገጹ ላይ የተናገረው አቤል ተስፋዬ፤ ሌሎችም ለዚህ ጅምር መሳካት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርቧል፡፡
በቶሮንቶ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናት ፕሮግራም ለማስጀመር ታስቦ እየተካሄደ በሚገኘው የገንዘብ ማሰባሰብ እስካሁን ድረስ ከ170 ሺህ ዶላር በላይ  መገኘቱን ያስታወሰው ዘገባው፤ ዩኒቨርሲቲው በዚህ አመት የግዕዝ ቋንቋ ጥናትን ለማስጀመር አቅዶ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝም ጠቁሟል፡፡
የቢቂላ አዋርድስ ፕሬዚዳንት አቶ ተሰማ ሙሉጌታ፣ በቶሮንቶ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናት ፕሮግራም መጀመሩ የአገሪቱን ጥንታዊ ስልጣኔዎች በመመርመር እንዲሁም ቱባ ባህላችንን፣ ታሪካችንንና ባህሎቻችንን ጠብቆ በማቆየት ረገድ ተጠቃሽ አስተዋጽኦ ያበረክታል ሲሉ መናገራቸውንም ዘገባው አመልክቷል፡፡
በኦሎምፒክ ጀግናው አበበ ቢቂላ ስም የተቋቋመው ቢቂላ አዋርድ፣ በኢትዮ-ካናዳውያን መካከል የአካዳሚክ፣ ሙያዊና የቢዝነስ ትብብር የመፍጠርና በጎ ፈቃደኝነትን የማጠናከር አላማ ይዞ እንደተመሰረተ የጠቆመው ዘገባው፣ ተቋሙ ከሁለት አመታት በፊትም ለድምጻዊ አቤል ተስፋዬ የሙያዊ ልቀት ሽልማት እንዳበረከተለት አስታውሷል፡፡
ለ117 አለማቀፍ የሙዚቃ ሽልማቶች በመታጨት፣ ሁለት የግራሚና ስምንት የቢልቦርድ ሽልማቶችን ጨምሮ 36 አለማቀፍና ክልላዊ የሙዚቃ ሽልማቶችን ያገኘውና በወቅቱ የአለማችን የሙዚቃ መድረክ አብሪ ኮከብ ሆኖ የወጣው የ25 አመቱ ድምጻዊ አቤል፤ፎርብስ መጽሄት በቅርቡ ይፋ ባደረገው የ2016 ከፍተኛ ተከፋይ 100 የዓለማችን ዝነኞች ዝርዝር ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ከተካተቱት 15 ዝነኞች መካከል አንዱ እንደነበርና  ከእነዚህ ዝነኞች መካከልም ከፍተኛውን ገቢ ማግኘቱን፣ ባለፉት 12 ወራት ብቻ 55 ሚሊዮን ዶላር ገቢ እንዳገኘም መዘገባችን አይዘነጋም፡፡




Monday, 15 August 2016 09:38

ጊዜ (ASIKO 2016)

(ካለፈው የቀጠለ)

ባለፈው ሳምንት ASIKOን ለመዳሰስ መንደርደሪያዎችን በመዘርዘር በአሁኑ ወቅት፤ በተለይም በዘመነኛ የኢትዮጵያዊ ሥነ-ጥበብ አውድ መጠየቅ የሚችሉ፤ መጠየቅ ያለባቸውንና መልስ እንኳን መስጠት ባንችል፣ ለጥያቄዎቹ መልስ እንድናፈላልግ የሚያስችሉ ውይይቶችን መጀመር ያለብን ወሳኝ ጊዜ ላይ መሆናችንን በማተት ነበር ጽሑፌን ያቀረብኩት፡፡ በዛሬው ተከታይ ክፍል፤ ስለ ሥነ-ጥበብ ስንነጋገርና ጠቅለል ያሉ ነገር ግን ወደ እኛ ወደ ዘመነኛው የኢትዮጵያ ሥነ-ጥበብ ውይይት ስንገባ፣ልናነሳቸው ለሚገቡ ጥያቄዎች መልስ ለማፈላለግ መንገዶች ሆነው በASIKO የተካተቱ አቀራረቦችን በዝርዝር እያነሳን እንመለከታቸዋለን፡፡
Elevator Pitch:  (የሊፍት ውስጥ ፈጥ ያለ ንግግር)፡- ውድ ነገር ቢኖር ጊዜ ነው፡፡ ለመስራት በቂ ጊዜ ያለው ባለሙያ፤ስለ ስራው ጥናት ማድረግ፣ ማሳወቅና ማስተዋወቅ የሥራው አካል እንደሆነ ግልፅ በመሆኑ ጥናት የምናደርግበት፣ የምናሳውቅበትንና የምናስተዋውቅበትን መንገዶች የማወቅና በዝግጁነት መጠበቅ የአንድ ሰዓሊም ሆነ አጋፋሪ ሙያዊ ሃላፊነትም ጭምር ነው፡፡ በሥነ ጥበቡ ዓለምም ሆነ በሌሎች ዘርፎች በሙያው ላቅ ያለ ደረጃ ያላቸው ሰዎች በአንፃራዊነት ጊዜ የሚያጥራቸው ሰዎች እንደሆኑ ይታወቃል፡፡ እነዚህ ሰዎች፤የመንግስት ባለስልጣናት፣ባለሀብቶች ወይንም በሀላፊነት ቦታ የተቀመጡ የምንፈልጋቸው ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ እነዚህ ለሙያችን መበልፀግ ወሳኝ የሆኑ ሰዎችን ለምሳሌ በሊፊት ውሰጥ ድንገት ብናገኛቸው ምን አይነት አቀራረብ ይዘን ነው  ልናናግራቸው የምንችለው/ እንዴትስ ነው ስለ ሥራችን Highlight ወይም ብልጭታ ልንሰጣቸውና የተሟላ የሥራ ዕቅድ ይዘን እንድንቀርብ የሚያስችል እድል መፍጠር የምንችለው? ይህን አይነት አጋጣሚዎች ከግንዛቤ አስገብቶ፣ ሙያዊ ዝግጅት ማድረግ፣ አንደኛው የASIKO አቀራረብ ሲሆን ተሳታፊያን፣ ይህንን ልምምድ እንዲያደርጉ እድል ይሰጣቸዋል፡፡
ይህንን አቀራረብ ወደ ሀገራችን አምጥተን ስናየው፣ በአንድ በኩል አስቂኝ በሌላም አሳዛኝ ሆኖ ይታየኛል፡፡ አስቂኙ፤ አብልጫው የሀገራችን ሰዓልያን ስለ ሥራቸውም ሆነ ስለ ሥነ-ጥበባዊ ማንነታቸው ለተገቢው አካል የተመጠነ Highlight ወይም ብልጭታ ከመስጠት የተቆጠቡ ናቸው፡፡ በዚህ የንግግር ባሕላችን አለመዳበር ምክንያት ለምንሰራው ስራ ተገቢውን አትኩሮት ላናገኝ እንችላለን፡፡ የሃገራችን የሥነ-ጥበብ ተመልካች፣ በቂ የሥነ-ጥበብ ግንዛቤ የሌለው በመሆኑም ይህ የንግግር ባሕል አስፈላጊ ነው፡፡ ሌላኛው የዚህ ስራን የማስተዋወቅ ነገር አስቂኝነት አሳዛኝ የሚሆነው በሀገራችን አውድ በተለይም ስለ ሥራቸው ያለማቋረጥ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ የሚናገሩ መኖራቸው ነው፡፡ ታዲያ አስቂኝነቱ ወደ አሳዛኝነት የሚቀየረው እንዲህ አይነቱ ተናጋሪዎች፣ ወደ ስራቸው ስንመጣ ያወሩት ሁሉ ሃሳብ ይሆናል፡፡ በስራው (በእይታ)) ሌላ ይሆንና ወሬው ብቻ ስራ ይሆናል፡፡ በዚህ መንገድ የመንግስት ባለስልጣናትን፣ ባለሃብቶችንም ሆነ ባለሙያዎችን በእንቧይ ካብ ‘ሞልተው’ ለሙያውም ሆነ ለሠዓልያን ተገቢውን ክብር እንዳይሰጥ ያደረጉ እጀ ሰባራዎች ብዙ ናቸው፡፡ ስለዚህም፣ እንደ የሥነ-ጥበብ ባለሙያ (ሠዓሊ፣አጋፋሪ፣ደጋፊ… ወዘተ) የሰዎችን ቀልብ ለመግዛት ብቻም ሳይሆን የተገዛውን ቀልብ ለማርካትና ተገቢውን ቦታ ለማስያዝ የሚያስችል ከASIKO አቀራረብ አንዱ የሆነው Elevator Pitch አይነተኛ መማሪያ ሊሆን ይችላል፡፡ የትኛው ባለሥልጣንና ባለሃብት ነው እንኳን ሊፍት ውስጥ ይቅርና ቢሮው  ሃምሳ ጊዜ ተመላልሰህ ያገኘኸው እለት እንኳን ጆሮ የሚሰጥህ? የሚልም ይኖራል፡፡ እውነት ነው፡፡ ነገር ግን ጆሮውን ዳባ ያለበሰ በሞላበት፣ ጆሮ መኮርኮሪያ ማዘጋጀት የኛ የባለሙያዎች ኃላፊነት ነው፡፡
Crit- (Criticism) ሂስ፡- ከአቻ የሙያ አጋሮች፣ ከቀደምት (Senior) ባለሙያዎችም ሆነ በሌሎች የሙያ ዘርፎች ከሚገኙ ባለሙያዎች ጋር ስለምንሰራቸው የሥነ-ጥበብ ውጤቶች አስተያየትና ሂስ ለመቀበል ዝግጁ መሆን ይጠበቅበናል፡፡ በሥነ-ጥበቡም ሆነ በሌሎች የሙያ ዘርፎች በምናገኛቸው አጋጣሚዎችም ሥነ-ጥበባዊ ማንነት ያለው አስተሳሰብና ሂስ መስጠትም ከአንድ ሠዓሊም ሆነ የሥነ-ጥበብ ባለሙያ የሚጠበቅ ነው፡፡ በASIKO ባህል ስራን አቅርቦ መተቸትና ሂስ መቀበል የተለመደ ነው፡፡ ሂስ ሲባል ደግሞ እንደተገኘ መውቀጥ ሳይሆን ምክንያት ደርድረው ማሳመን፣ ሰዓሊው የሰራውንም ሆነ የሥነ-ጥበብ አጋፋሪው(Curator) ያጋፈረው ሥራ ውስጥ በተመሳሳይ መልኩ የተሰሩ ሥራዎችን የመዳሰስና የማጥናት፤ ተመሳስሎዎችን የመንቀስና ተቃርኖዎችን የመለየት እንዲሁም የዚህ ሁሉ ትንተና ጠቀሜታን ከተሰራውና ከሚሰራው ስራ ጋር ማያያዝ የሂስ መሰረታውያን ናቸው፡፡ የASIKO ተሳታፊያን በዚህ የሂስ ባህል እጅግ ተጠቅመዋል፡፡ ሥራቸውን ለማሻሻልም ስንቃቸውን ይዘዋል፡፡
በኢትዮጵያ የሥነ-ጥበብ ታሪክ ውስጥ ሊጠቀሱ ከሚችሉት ሃያሲያን መሃከል የ1970ዎቹና ለ1980ዎቹ የሥነ-ጥበብ ታሪክ ምሁሩና አጥኚው ሃያሲ ስዩም ወልዴ ራምሴ እና በ1960ዎቹ  ደግሞ ገጣሚ ሰለሞን ደሬሳ ሲሆኑ የኢትዮጵያ የሥነ-ጥበብ ላይ ሂስ በመስጠት ይታወቁ ነበር፡፡ ነበር፡፡ ነበር። ነበር፡፡ ነበርንም ማንሳት አንድ መጽናኛ ሊሆን ይችላል፡፡ ከ1990ዎቹ መጀመሪያ እስከ አሁን ዘመን ድረስ የሥነ-ጥበብ ታሪካችን የሂስ ድርቅ የመታው፤ የግልፅ ውይይትና የትችት መጋኛ የቆለፈውና ዝምታው አላስችል ሲል ሹክሹክታና ሃሜት ያጀበው ታሪክ ነው ያስተናገድነው፤እያስተናገድንም የምንገኘው፡፡ የሥነ-ጥበብ እውቀት ያላቸውና ያከማቹ የሥነ-ጥበብ ማኅበረሰቡ አባላትም ሆነ ሰዓሊያን፤ ሂስ ለመሰጣጠት ተነሳሽነት ያጡበት ምክንያቶች ይኖራሉ፡፡ ሆኖም ዝምታ መፍትሄ ሊሆን አይችልም፡፡ የአንድ ሀገር ሥነ-ጥበብ ስኬት ሊኖረው የሚችለው በመጀመሪያ ደረጃ የሥነ-ጥበብ ማኅበረሰቡ ራሱ የሂስና የትችን ባህል ሲኖረው ነው። የሚሰሩት የሥነ-ጥበብ ውጤቶች ላይ ምክንያታዊ ሆኖ መቅረብ ሲቻል፤ ከሥነ-ጥበብ ማህበረሰቡ በዘለለ አመለካከቱ የሰላ፣ አተያዩ የዳበረና ግንዛቤውን ሊያሰፋ የሚችል መዛኝ ማኅበረሰብ (Critical Mass) መፍጠር ይችላል፡፡
ንባብና ምርምር (Reading and Research):- ሥነ-ጥበብ እይታ ላይ መሰረት ያደረገ ነው፡፡ የምንሰራውን ሥነ-ጥበብ ማጠናከርም ሆነ ሥነ-ጥበባዊ አድማሳችንን ለማስፋት ንባብ ወሳኝ ነው። የሥነ-ጥበብ ታሪክን ለማወቅ፣ የሠዓልያንን የተሰጥኦና የመነቃቂያ ርዕስ ጉዳይን ይበልጥ ለመረዳት፣ ርዕሰ ጉዳዩ ሊነካካ የሚችላቸው ሌሎች ርዕሰ ጉዳዮችን፣ በሚሰራበት ርዕስ ጉዳይ ዙሪያ የሚሰሩ የሌሎች ሰዓሊያንን ሥራዎች ማጥናት ሁሉ ከአንድ ሠዓሊ፣ የሥነ-ጥበብ ባለሙያም ሆነ ሥነ-ጥበብን ለመረዳት ከሚፈልግ ማንኛውም ሰው የሚጠበቅ ስራ ነው፡፡ ASIKO የዚህን ጠቀሜታ ያሰመረ ልምድ ነበረ የተወልን፡፡
የASIKO ሲምፓዚየም፡- በመጨረሻው የASIKO ሳምንት የተካሄደው የሁለት ሰዓት ተኩል አጠር ያለ ሲምፖዚየም በአይን ገላጭነቱ አይነተኛ ነበር፡፡ የሲምፖዚየሙ ርዕስ ‘የሥነ-ጥበብና የሥነ-ጥበብ አጋፋሪነት ትምህርት ቀጣይ ጉዞ በአፍሪካ’ የተሰኘ ነበር፡፡
ሲምፖዚየሙ ከሀገራችን፣ ከአፍሪካና ከተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች የታደሙ ባለሙያዎችን ያሳተፈ ነበር፡፡ ሲምፖዚየሙ በዋናነት የሚሞግተው፣ የሀገራችንም ሆነ የሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የሥነ-ጥበብና የሥነ-ጥበብ አጋፋሪነት ትምህርት በምዕራባውያንና በአውሮፖውያን ሥርዓተ ትምህርት የተቃኘ መሆኑን ነው፡፡ ይህንን እውነት ለመቀየር በሚደረግ ጥረት ስለ ሀገራችንም ሆነ ስለ አህጉራችን እውነታዎች ቦታ የሚሰጥ ሥርዓተ ትምህርት በመቅረፅ ሂደት ውስጥ ሊያጋጥሙን የሚችሉ ፈታናዎችን በመዳሰስ፤ ከመንግስት፣ ከሠዓሊያንና ከሥነ-ጥበብ ባለሙያዎች የሚጠበቁ ኃላፊነቶችን ያመላከተ ነበር፡፡ የASIKO ተሞክሮ በወሳኝነት የሥነ-ጥበብና የሥነ-ጥበብ አጋፋሪነት ትምህርትን ሥርዓተ ትምህርት ለመቅረፅ ሀገራዊም ሆነ አህጉራዊ አውዶችን ማካተት ያለው ፋይዳ ያትታል፡፡ በሲፖዚየሙ ከተነሱ ጥያቄዎች መካከል፡- በአፍሪካ ሀገራት እየተሰጠ ያለው የሥነ-ጥበብ ስርዓተ ትምህርት ምን ያህል የሠዓልያንን ፍላጎት የሚያሟላ ነው? ከ21ኛው ክፍለ ዘመን እውነታዎች ጋር ለመራመድ የሚያስችል የሥነ-ጥበብና የሥነ-ጥበብ አጋፋሪነት ትምህርት በአፍሪካ ለመቅረፅ ምን ዓይነት አማራጭ ሞዴሎችን መጠቀም ይቻላል? በአፍሪካ የሚኖሩና የሚሰሩ ሠዓሊያንም ሆኑ የሥነ-ጥበብ አጋፋሪዎች ለሚኖሩበት እውነታ ሂሳዊና ወሳኝ የሆነ ሥራ ለመስራት የሚያስችላቸው ሥርዓተ ትምህርት ምን ሊመስል ይችላል? የሚሉ ጥያቄዎች ይገኙበታል፡፡ አህጉራዊና ሀገራዊ አማራጮችን ማሰስና መጠቆም ላይ ያተኮረው ይህ ሲምፖዚየም፤ የሥነ ጥበብ አጋፋሪነት ትምህርትን በተመለከተ በተለይ ለሀገራችን አውድ አንገብጋቢ የሚሆነው የአጋፋሪነት ሙያን ሥራ ላይ ማዋል እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ ከአ.አ.ዩ አለ የሥነ-ጥበብና ዲዛይን ት/ቤት፣ የሥነ-ጥበብ ትምህርት ክፍል በሲፖዚየሙ የተጋበዙት ሠዓሊና መምህር ክብሮም ገ/መድህንና መምህር አበባው አያሌ ያሰመሩበትም፣ የሥነ-ጥበብ ትምህርትን ለማዳበር ርብርቦሽ  ማድረግ በሚያስፈልግበት በዚህ ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ላይ የትምህርት ክፍሉ እንዲዘጋ ከዩኒቨርሲቲው ትዕዛዝ በመምጣቱ ሳቢያ፣ የትምህርት ክፍሉን ከመዘጋት በመታደግ ሂደት ውስጥ አማራጭ የሥርዓተ-ትምህርት በመቅረፅ፣ ት/ክፍሉ ወደ ‘ሥነ-ጥበብ ታሪክ’ ትምህርት ክፍልነት ለመቀየር እየተደረገ ያለውን ጥረት አስገንዝበዋል፡፡ በተለይ አቶ አበባው አያሌው፤ በት/ቤቱ በተለያየ ዘመን የተካሄዱትን የሥርዓተ-ትምህርት ለውጦችን በማንሳት ከመደበኛ ሥርዓተ ትምህርት ውጪ ያሉትን አማራጮች መመልከት ጠቃሚ እንደሆነም አስገንዝቧል። ረዳት ፕሮፌሰር ሠዓሊና ቀራፂ በቀለ መኮንን በበኩሉ፤ በሃገራችንም ሆነ በአህጉራችን የሥነ-ጥበብ ትምህርት ቅኝት ውስጥ ‘በአንድ ፈረስ ላይ ብቻ የመረባረብ’ ልምድ ያካበትን መሆኑን በመግለፅ፣ ሥርዓተ-ትምህርታችንን ለማሻሻል አማራጭ ፈረሶችን መግራት እንደሚያስፈልግ ጠቁመው፤ የASIKOን ቅርፅ እንደ ማሳያ አመላክተዋል፡፡
አሁንና እዚህ (Here and Here): የአሲኮ ትርዒት፡- የASIKO መርሃ ግብር ማጠናቀቂያ የነበረው የሥነ-ጥበብ ትርዒት ነበር፡፡ ትርዒቱ በአስኒ ጋለሪ የተካሄደ ሲሆን ሦስት ክፍሎች ነበሩት፡፡ የመጀመሪያ ድንበርን የተመለከተ ሲሆን በአፍሪካ ውስጥ መዘዋወርና ድንበር መሻገር ያለውን ውጣ ውረድ የሚያስቃኝ ነበር፡፡ ተሳታፊያኑ ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት የቪዛ ችግር የገጠማቸው ከመሆኑም በላይ በየመንገዱ ‘አፍሪካ!’ እየተባሉ መጠራታቸው ስለ አፍሪካዊነት ከኢትዮጵያውያን ጋር በሚያደርጓቸው ውይይቶች፣ ኢትዮጵያውያን አፍሪካውያን ሳይሆኑ ኢትዮጵያውያን ብቻ እንደሆኑ የሚያስቡ መሆናቸው በተሳታፊያኑ ዘንድ ግርምት የፈጠረ ነበር፡፡ ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሃገራት አንዷ መሆን ብቻም ሳይሆን ለአፍሪካዊነት የተጫወተችው ሚና ጉልህ ነው፡፡ ሆኖም ይህ ወደ ሕዝቡ ሲወርድ ቦታ የሌለው በመሆኑ ተሳታፊያኑ ስለ አፍሪካዊነት እንዲያስቡበት አድርጓቸዋል፡፡ በትርዒቱም፡- ማንነት፣ ድንበር፣ መሰናክልና ስደት በአህጉሪቱ ያላቸው ገፅታ ተንጸባርቋል፡፡ የትርዒቱ ሁለተኛ ክፍል በቅርቡ የተመረቀው የአፍሪካ ፓስፖርትን መሰረት ያደረገ ፓስፖርት ሠዓሊያኑ የሰሩበት ክፍል ሲሆን ይህን ፓስፖርት ያልያዘ ማንኛውም ጉብኚ ወደ መጀመሪያው የትርዒቱ ክፍል መግባት አይችልም ነበር፡፡ ይኸም ተመልካቹን አሳታፊ በማድረግ ስለ አፍሪካዊ ማንነት፣ ድንበርና ስደት- -- ጥያቄዎችን በማስነሳት ውይይት እንዲፈጠር አስችሏል፡፡ የትርዒቱ የመጨረሻ ክፍል ‘ጉርሻ’ ነበር። እንደ አንድ የኢትዮጵያ ባህል፡- ጉርሻ በተለምዶ ፍቅርና መተሳሰብን መግለጫ ነው፡፡ በዚህ ትርዒትም በጋቢ የተሸፈነና ሶስት ቀዳዳዎች ካሉት ሳጥን መሳይ መከለያ ውስጥ ብቅ የሚሉ እጆች፤ጉርሻ ይዘው ጎራሹን ይመግባሉ፡፡ የአጉራሾቹ እጆችና የያዙት ምግብ እንጂ ፊታቸውና ገፅታቸው አይታይም፡፡ አጉራሹ ጎራሹንም አያይም፡፡ ይህ መሆኑ ፍቅርም ሆነ አመኔታን ያለ ቅድመ ሁኔታ መስጠትና መቀበልን እንድናስብ የሚያደርግ ነበር፡፡ በትርዒቱ ሦስቱም ክፍሎች በሠዓልያኑ የተሳሉ ሥዕሎችን አናይም። ሀሳቦችን የሚወክሉ መስተጋብሮችን በኩልኮላ (Installation) እና ትግበራ (Performance) አማካኝነት ያነሳል፡፡ በዚህም አፍሪካን ዋነኛ ትኩረት በማድረግ የአፍሪካን ጊዜ ‘አሁን’ በማለትና አፍሪካን እንደ ቦታ በመውሰድ፣ ‘እዚህ’ በማለት፣ በዚህ ወሳኝ ጊዜ ሊነሱና ሊዳሰሱ የሚችሉት አህጉራዊ ጉዳዮችን ያነሳል፡፡
ማጠቃለያ፡- እንደ ታላቅ መድረክነቱ፤ ASIKO አያሌ ጉዳዮችን አስተማሪ ሆኖ አልፏል፡፡ ዋናው ቁም ነገር፤ ወደ እኛ ወደ ራሳችን ዓውድ ስንመለስ.፣ ልናበራይ የምንችለውን መንቀስና ተግቶ መስራት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሥነ-ጥበብ፤ ከአፍሪካ ሥነ-ጥበብ አንዱ የሚሆንበትን ብሎም በዓለም የሥነ-ጥበብ መድረክ መቀላቀል የሚያስችለንን የሥነ-ጥበብ ማንነት፤ በሀገር ደረጃ የመገንባት፣ የሥነ-ጥበብ ሥርዓተ-ትምህርታችንን በራሳችን ቅኝት ውስጥ ለመቃኘትና አደጋ ላይ ያለውን ወሳኝ የሆነው የሥነ-ጥበብ ትምህርትን አቅጣጫ መግራት፣ ግለሰብ ሰዓሊያንንና የሥነ-ጥበብ አጋፋሪዎችንን እንዲሁም የሥነ-ተመልካችና አድናቂውን ሳይቀር ያለበትን የቤት ስራ ለመስራት፣ ሂስ  ለመስጠት፣ ጥያቄዎችን ለመፍታትና ውይይቶችን ለመጀመር ይህ ወሳኝ ጊዜ - ASIKO አመልካች ነበር፡፡ ቸር እንሰንብት!

• “የዘመናት ብሶት የወለደው” ኢህአዴግ፤ ብሶተኞችን አይሰማም!?
• የሩብ ክፍለ ዘመን ዕድሜ ያስቆጠረው “ዲሞክራሲያችን” ፈሪ ነው!!

ሰሞኑን በኦሮሚያና አማራ ክልሎች፣ብዙ ሺዎች የተሳተፉበት የህዝብ ተቃውሞን ተከትሎ፣  በተከሰቱ ግጭቶች ከ140 በላይ ዜጎች በጸጥታ ሃይሎች መገደላቸው ተሰምቷል፡፡ በእጅጉ ያሳዝናል፡፡ (ጦርነት ሆነ እኮ!!) በነገራችን ላይ ኢህአዴግ የዘንድሮ ተቃውሞ፣ከወትሮው በእጅጉ የተለየ መሆኑን አንድም አላጤነውም አሊያም ማጤን አልፈለገም፡፡ (እውነታውን ማወቅ   ያጥወለውላል!)
በኦሮሚያ ክልል ተቃውሞ ከተጀመረ 9 ወር ገደማ ሊሆነው ነው፡፡ እስካሁን 500 ሰዎች ገደማ ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ ግጭቱን ተከትሎ በትንሹ ከ10ሺ የማይንስ ነዋሪ ለእስር መዳረጉን ሪፖርቶች ይጠቁማሉ፡፡ በኢህአዴግ የሥልጣን ዘመንና በእኛ ዕድሜ፣ በዚህ መጠን ህዝባዊ ተቃውሞና በዜጎች ላይ የተፈጸመ ግድያ (አንድ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ) አላየንም፡፡  (ኢህአዴግ ደግሞ አሁንም አላየም!) ዛሬም ማታ ማታ በኢቢሲ የምንሰማው፣ ልማታዊ ዜናዎችና ፕሮጀክቶችን ነው፡፡ (#ጸጉራም ውሻ አለ ሲሉት ይሞታል!” አሉ˜)
ለመሆኑ ሁላችንስ በህይወት አለን እንዴ? በዚህ ምስቅልቅል፣ በዚህ ቀውስ፣በዚህ መተራመስ፣በዚህ አለመደማመጥ፣ በዚህ ጭለማ ---- መሃል እስትንፋስ ስላለን ብቻ እየኖርን ነው ማለት አንችልም፡፡ (እያልኖርንም ነው ሊባል ይችላል!!!) ኢህአዴግ ሁሌ መዘግየት ይወዳል፡፡ ምክር ለመስማት----ይዘገያል፡፡ የህዝብ ቅሬታ ለማጤን-----ይዘገያል፡፡ ለህዝብ ቅሬታ  ምላሽ ለመስጠት---- ይዘገያል፡፡ አገር ላይ እየመጣ ያለውን አደጋ ለመገመት--------ይዘገያል፡፡ ሁሌም ይዘገያል---ኢህአዴግ ነፍሴ!
 የህዝብ ተቃውሞ እየተባባሰ ሲመጣ፣ከተለመደው የሰበብ ክሊሼው ተላቅቆ፣ በፍጥነት ወደ መፍትሄ ቢያመራ ኖሮ፣ ቢያንስ ወደ መጨረሻ ግድም የተከሰቱ ግጭቶችና እልቂቶችን ማስቀረት ይችል ነበር፡፡ በዚህም የዜጎችን ህይወት ከጥፋት፣ንብረቶችን ደግሞ ከውድመት ያተርፍ ነበር፡፡ (በትንሹ 140 ዜጎች  ሞተዋል!) ዕውነቱን ለመናገር------ይሄ ማስቀረት ይቻል የነበረ ዕልቂት ነው!!!
የሰሞኑ አሰቃቂ ጥፋትና ውድመት ውስጤን ሲረብሸኝ ሰነበተና ድንገት አንድ ሃሳብ ብልጭ አለልኝ። እናም እንዲህ አልኩ፡- ከእንግዲህ የማንወደውን ብቻ ሳይሆን፤የማይወደንንም አንመርጥም!! እውነቴን ነው ----- ከአሁን በኋላ ወደ ምርጫ ውድድር ለሚመጡ ወይም  ለሥልጣን ፉክክር ለሚቀርቡ ፓርቲዎች፣ የመጀመሪያው መስፈርት፣ለዜጎች የሚሰጡት ክብር ነው፡፡ ህዝቡን ከልባቸው ይወዱታል? ከምር ይቆረቆሩለታል? ለዜጎች ህይወት ዋጋ ይሰጣሉ? በስደት ለሚኖር ኢትዮጵያዊ መብትና ነጻነት ይከራከራሉ? ይሄን የሚያሟሉ መሆናቸው በዲኤንኤ ይሁን በሌላ ሲረጋገጥ ብቻ ነው ለሥልጣን የሚወዳደሩት፡፡ የወደፊት መንግስታችን፤ ሥልጣን ብቻ የሚወድ ሳይሆን እኛንም ጭምር የሚወድ መሆን አለበት፡፡ የማይወደን አይገዛንም!!!
ላለፉት 25 ዓመታት፣ ወደንም ይሁን ሳንወድ የገዛን ልማታዊው መንግስት፤ዜጎቹን ለመውደዱ ማረጋገጫ ማቅረብ ይከብዳል፡፡ ዜጎቹን የሚወድ ቢሆን ኖሮ፤ #ያለ ፈቃዴ ሰልፍ  ወጣችሁ” ብሎ የሃይል እርምጃ ይወስድ ነበር!? (ግን መንግስት የት ነው የሚከሰሰው?) እኔ የምለው --- በሰሞኑ ተቃውሞ ለምንድን ነው የበርካቶች ህይወት ያለፈው? ባለፈው ቅዳሜና እሁድ የሞቱ ዜጎች ቁጥር በእጅጉ ያሻቀበው፣መንግስት ማስጠንቀቂያ ከሰጠ በኋላ ሰዎች ለተቃውሞ በመውጣታቸው ነው የሚሉ ወገኖች አሉ፡፡ (አንድ ወዳጄ፤#መንግስት ማስጠንቀቂያውን በቃና ቲቪ ቢያስተላልፈው ይሻል ነበር አለችኝ!!)  
እናላችሁ---- በአንድ በኩል የተናገሩት ከሚጠፋ በሚል ብሂል፣በሌላ በኩል ኢህአዴግ አልቆለታል ባዮችን እንዳላለቀለት ለማሳየት (#ትዕግስት ፍርሃት አይደለም” ዓይነት!!) ለተቃውሞ የወጡ ዜጎች ላይ የሃይል እርምጃ የተወሰደ ይመስላል፡፡ ምናልባት እኮ ጠንካራነቱን ለማሳየት የፈለገው ለአንዳንድ ዳያስፖራ ታጋዮችና ፖለቲከኞች ይሆናል፡፡ የሞቱት ግን ኑሮአቸው እንዲሻሻል፣መብታቸው እንዲከበር፣ ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል እንዲሰፍን-----አደባባይ ወጥተው የጮሁ ምስኪን ኢትዮጵያዊያን ናቸው፡፡
አሳዛኙ እውነታ ደግሞ ምን መሰላችሁ? በዚህ የቀውስ ወቅት እንኳን የሩብ ክ/ዘመን ዕድሜ ያስቆጠረው #ዲሞክራሲያችንም” ሆነ ኢህአዴግ ማስፈራሪያ ያደረገው ህገ-መንግስታችን፤ ዜጎችን ከሞትም ሆነ ከመቁሰል እንዲሁም ከእስር አልታደጓቸውም፡፡ (የ25 ዓመቱ ጎረምሳ “ዲሞክራሲያችን” አሁንም ፈሪ ነው!!) እንደኔ  እንደኔ፣መንግስት ጥንካሬውንና ጀግንነቱን ማሳየት የነበረበት ህገ-መንግስቱን በማክበር ነበር!! አህአዴግ ነፍሴ ያደረገው ግን የተገላቢጦሹን ነው፡፡ (Cገ-መንግስት ያስፈለገው ጥይት እንዲቀር መስሎኝ?!) ለካስ በትልቁ ተሳስቼአለሁ!!
     በነገራችን ላይ ኢህአዴግ፤ለህዝብም ሆነ  በፓርቲ  ተደራጅቶ ለሚካሄድ የተቃውሞ ሰልፍ፤ተመሳሳይ ስሜትና ምላሽ ይኖረዋል ብዬ አስቤም አልሜም አላውቅም፡፡ (ለካስ ህዝብም ተቃወመ ሰማያዊ፤ለውጥ የለውም!!!) ይገርማል፤ግን እንዴት ለውጥ የለውም? ለምሳሌ ሰማያዊ ፓርቲ፤አነሰም በዛም የሥልጣን ተፎካካሪው ነው፤ስለዚህ ተቃውሞውን ብቻ ሳይሆን የሚተነፍሰውንም አየር ጭምር ቢፈራ ችግር የለውም። ህዝብ አደባባይ ወጥቶ፣ብሶትና በደሉን ቢያቀርብ ግን ምን ያስፈራል?? አሁን ለምሳሌ በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች፣ ህዝቡ ምን የሚያስፈራ ነገር ጠየቀ? ምን የማይቻል ነገር አድርጉልኝ አለ?? (መቼም ሥልጣን አጋሩኝ አይልም!) ቢጠይቅ እንጀራውን---- ቢጠይቅ አርሶ የሚበላበትን መሬቱን----ቢጠይቅ ለልጆቹ ት/ቤት---- ቢጠይቅ ፍትህ----ቢጠይቅ መብትና ነጻነቱን----ቢጠይቅ ወህኒ የተወረወሩ የትግል ጓዶቹ------ ከእስር እንዲፈቱለት ነው፡፡ ቢጠይቅ በጸጥታ ሃይሎች ለተገደለበት ወንድሙ ወይም ልጁ ካሳ ነው፡፡ በቃ ይሄው ነው!!!
እኔማ----ህዝቡ ተጠራርቶ፣ለተቃውሞ አደባባይ የሚወጣው ችግር አናቱ ላይ ሲቆለልበትና በደልና ግፍ ሲበዛበት እንደሚሆን ከኢህአዴግ ነፍሴ የበለጠ የሚረዳ የለም ብዬ ደምድሜ ነበር፡፡ (በ82“ብሶት የወለደው የኢህአዴግ ሰራዊት” ያለውን አስታውሼ እኮ ነው!!!) የተሸወድኩት ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ? ከ25 ዓመት ብሶትና በደል አልባ የሥልጣን ዘመን በኋላም፣ የሌሎችን ብሶትና በደል የሚያዳምጥበት ጆሮ ይኖረዋል ብዬ መገመቴ ነው!!! (ያውም ራሱ በዳይና ብሶት ፈጣሪ በሆነበት አገር!!) በእውነቱ ይቅርታ የመጠየቅ ታላቅ ልማድን ከራሱ ከኢህአዴግ ተውሼ፣እነሆ ይቅርታ እጠይቀዋለሁ!! (ለሽሙጥ ሳይሆን ከልቤ!!) እንዴ----ገና ለገና ከብሶትና ከበደል የተወለደ ፓርቲ ነው ብዬ፣የመላዕክት ሥራ እንዲከውን መጠበቄ ታሪካዊ ስህተት ነው፡፡ (ግፋ ቢል የኮሙኒስቶች ስብስብ ይሆናል እንጂ ፈጽሞ የመላዕክት ስብስብ አይሆንም!!!)  
 ሰሞኑን ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም በፌስቡካቸው ላይ ባሰፈሩት አጭር ማስታወሻ ፅሁፌን እቋጫለሁ፡- ሰላማዊ ተቃውሞን ‹‹በቁጥጥር ሥር አውለነዋል›› ማለት ራሱ ሰብዓዊ መብቶችን ማዳፈናን ማወጅ ነው፡፡ ሰላማዊ ተቃውሞ መፈቀድ አለበት፤ መደመጥ አለበት፣ ሰላማዊ መልስ ማግኘት አለበት፣ እስከ መቼ ነው ሁሉንም ዓይነት ልዩነት በጡንቻ እየዳመጡ (መቆጣጠር) የሚቻለው? መቼ ነው ገዢዎቻችን የሚማሩት? ለመሆኑ የመማር ችሎታስ አላቸው ወይ?”












   በዘንድሮው የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ሪፐብሊካንን ወክለው በመወዳደር ላይ የሚገኙት አወዛጋቢው ዕጩ ዶናልድ ትራምፕ፤ ለደጋፊዎቻቸው ባደረጉት የምረጡኝ ቅስቀሳ ላይ፣ “ፕሬዚዳንት ባራክ ሁሴን ኦባማ÷ የአሸባሪው ድርጅት አይሲስ መስራች ናቸው” ሲሉ መናገራቸውን ኤቢሲ ኒውስ ዘገበ፡፡ ትራምፕ ባለፈው ረቡዕ ምሽት በፍሎሪዳ ሰንራይዝ ከተማ ባካሄዱት የምረጡኝ ቅስቀሳ ንግግራቸው ላይ፣“አይሲስን የመሰረቱት ፕሬዚዳንት ኦባማ ናቸው” በማለት ሶስት ጊዜ ደጋግመው የተናገሩ ሲሆን “ከእሳቸው ጋር በመሆን አሸባሪውን ድርጅት የመሰረቱትም ተንኮለኛዋ ሄላሪ ክሊንተን ሳይሆኑ አይቀሩም” ሲሉ ወንጅለዋቸዋል፡፡
አወዛጋቢው ትራምፕ፤በንግግራቸው ወቅት ኦባማን በሙሉ ስማቸው ባራክ ሁሴን ኦባማ ብለው መጥራታቸው፣ ፕሬዚዳንቱ የእስልምና እምነት ተከታይ ናቸው የሚለውን ሃሜት ለማጉላት በማሰብ ነው ያለው ዘገባው፤ኦባማ ስለ ሽብርተኝነት ሲያወሩ አክራሪ እስላማዊ ሽብርተኝነት ብለው ለመናገር አይደፍሩም ሲሉ መንቀፋቸውንም ጠቁሟል፡፡ ፡፡
“ሂላሪ ክሊንተንም ፕሬዚዳንት ኦባማን ላለማስቀየም ሲሉ ይህንን አባባል በንግግራቸው ላይ ተጠቅመውት አያውቁም” ያሉት ትራምፕ፣ ይህም የሆነው ኦባማን ካስቀየምኩ የከፋ ነገር ይገጥመኝ ይሆናል በሚል ስጋት ነው ብለዋል፡፡ ዘ ኢንዲፔንደንት በበኩሉ፤ትራምፕ የወቅቱን የአሜሪካ አስተዳደር ከአይሲስ ምስረታ ጋር በተያያዘ ተጠያቂ ሲያደርጉ የመጀመሪያ ጊዜያቸው እንዳልሆነ በመጠቆም፣ ባለፈው ሃምሌ ላይም አይሲስን የፈጠሩት ሄላሪ ክሊንተን ናቸው ማለታቸውን አስታውሷል፡፡