Administrator

Administrator

  ፀሀፊና ተርጓሚ መክብብ አበበ የታዋቂውን ሩሲያዊ ደራሲ ፊዮዶር ዶስቶቪስኪ 10 አጫጭር ታሪኮችን ተርጉሞ ‹‹የሚያቄለው ሰው ህልም›› በሚል ርዕስ ለንባብ አበቃ፡፡
መድበሉ ‹‹ትንሹ ልጅ››፣ የገና ዛፍና ሰርጉ››፣ ‹‹ቦቦክ››፣ ‹‹ዘጠኙ ደብዳቤዎች››፣ ‹‹ታማኙ ሌባ››፣ ‹‹ፈሪዋ ልብ››፣ ጨዋ መንፈስ፣ ‹‹ገበሬ ማሬይ›› እና ‹‹ፓልዘንኮከ›› የሚሉ ታሪኮችን አካትቷል፡፡
ተርጓሚው ከዚህ ቀደም ‹‹ሰውና ሀሳቡ›› እና ‹‹ህይወት በጠንቋዩ ቤት ውስጥ” የተሰኙ መፅሐፍትን ለንባብ ማብቃቱ የሚታወስ ሲሆን በቀጣይም የፊዮዶር ዶስቶቭስኪን ‹‹የሌላ ሰው ሚስት›› ወይም ‹‹አልጋ ስር የተደበቀው ባልና አዞው›› ሥራዎች ለመተርጎም በዝግጅት ላይ መሆኑም ተገልጿል፡፡ ‹‹የሚያቄለው ሰው ህልም›› በ204 ገፆች ተመጥኖ፣ በ71 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

 በደራሲ ስዩም ገብረ ሕይወት ተጽፎ በ1994 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ለንባብ የበቃውና በድጋሚ የታተመው “ሚክሎል - የመቻል ሚዛን” የረጅም ልቦለድ መጽሃፍ፣ ዛሬ ተሲያት ላይ በጁፒተር ሆቴል ተመርቆ በገበያ ላይ እንደሚውል  ደራሲው በተለይ ለአዲስ አድማስ ገልጧል፡፡
ወጣትና አንጋፋ ገጣሚያን ስራዎቻቸውን በሚያቀርቡበትና የተለያዩ ኪነ ጥበባዊ ዝግጅቶች በተካተቱበት ፕሮግራም የሚመረቀው “ሚክሎል - የመቻል ሚዛን”፣ በደርግ መንግስት የመጨረሻ አመታት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተከስቶ በነበረው የፖለቲካ እንቅስቃሴና የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የብላቴ የጦር ማሰልጠኛ ዘመቻ ዋዜማ ላይ መቼቱን በማድረግ፣ የተለያዩ አገራዊ ጉዳዮችን በፍልስፍና እየነቀሰ የሚተነትን መጽሃፍ ነው፡፡
መጽሃፉ ጠንካራና ፈታኝ ሀገራዊ ጉዳዮችን በሠመረ ኪናዊ ውበት የሚዳስስ፣ የተሻለ ሀገራዊና ግለሰባዊ የእድገት ጥያቄዎችን እያነሳ ልማዳዊውን የማንነት ገበና የሚጋፈጥ፣ ሀገራዊ ብልፅግናን ከተፈጥሮአዊ አቅም ጋር አስተሳስሮ የሚመረምር፣ ለአንባቢ እጅግ የነጠሩ ቁም ነገሮችን የሚያስጨብጥና የሚያነቃ እንደሆነ ያነጋገርናቸው የሥነጽሁፍ ባለሙያዎች መስክረዋል፡፡
በ395 ገጾች የተቀነበበው መጽሃፉ፣ በቅድስተ ማርያም ዩኒቨርሲቲ አሳታሚነት በድጋሚ ታትሞ ለንባብ የበቃ ሲሆን፣ በተለያዩ የመጽሃፍት መደብሮችና በአዟሪዎች በ150 ብር የመሸጫ ዋጋ ለገበያ ቀርቦ እየተሸጠ ይገኛል፡፡
በአሁኑ ወቅት ኑሮውን በእንግሊዝ አገር ያደረገው ደራሲ ስዩም ገብረ ሕይወት፣ የ“ሚክሎል - የመቻል ሚዛን” ቀጣይ ክፍል የሆነውና ከ15 አመታት በፊት የጻፈውን “የማቃት አንጀት” የረጅም ልቦለድ መጽሃፍ በቅርቡ ለንባብ ለማብቃት እንቅስቃሴ እያደረገ እንደሚገኝም ለአዲስ አድማስ ገልጧል፡፡
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኢንፎርሜሽንና ኮምፒውተር ሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪውን ያገኘው ደራሲ ስዩም ገብረ ሕይወት፣ በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያውን ቤተ መጽሃፍትና ኮምፒውተር ማዕከል በማቋቋምና በማስተማር ያገለገለ ሲሆን፣ በብሪቲሽ ካውንስል በፕሮጀክት ማናጀርነትና በቤተ መጽሃፍትና ኢንፎርሜሽን አገልግሎት ዋና ሥራ አስኪያጅነት ለሰባት አመታት ያህል ሰርቷል፡፡

 አንድ የሩሲያ ተረት እንዲህ ይላል፡-
ባልና ሚስት ዓሳ ሊያጠምዱ ወደ አንድ ሀይቅ ይወርዳሉ፡፡ ገና መንገድ ሳሉ፤
ሚስት፤
“የሚያዙት ዓሳዎች ግማሾቹ ለልጆቻችን ምግብ ይሆናሉ፡፡ ግማሾቹን ደግሞ ወደ ገበያ ወስደን እንሸጣቸውና፤ ሌሎቹ ኑሯችንን ማሟያ ገንዘብ ያመጣሉ፡፡” ትላለች
ባል፤
“እስቲ መጀመሪያ ዓሳዎቹ ይገኙ፡፡ ከዚያ ደግሞ መረባችን የሚይዘውን ብዛት እንይ፡፡ የዛሬ ዓሳዎች እኮ እንደ ድሮዎቹ ዓሳዎች በማንኛውም መረብ ውስጥ ተንደርድረው ጥልቅ አይሉም”
ሚስት፤
“ዓሳ ዓሳ ነው፤ ብርብራ ካየ ዘሎ ጥልቅ ማለቱ አይቀሬ ነው”
ባል፤
“አይምሰልሽ፤ እኛ ያለን የዱሮ መረብ ነው፡፡ ዓሳዎቹ የአሁን ጊዜ ናቸው፡፡ የዱሮ መረብ በቶሎ ይበጣጠሳል፡፡ ወይ መረቡ በአዲስ ክር መሰራት አለበት፤ አሊያም ሙሉ በሙሉ ተለውጦ አዲስ መሆን አለበት፡፡ እንጂ የዛሬን ዓሶች ችሎ አፍኖ አያስቀምጥም”
ሚስት፤
“ግዴለህም ባሌ፤ አታስብ፡፡ ሀይቁም ያው የዱሮው የምናውቀው ሀይቅ ነው፡፡ ዓሳዎቹም የዱሮዎቹ ዓሳዎች ናቸው፡፡ ድንገት ተነስተው ብልጥ ዓሳዎች ሊሆኑ አይችሉም፡፡ እኛ ተጃጅለን፤ ቅልጥፍና አንሶን የማምለጥ እድል ካልሰጠናቸው ባንድ አፍታ እጃችን እናስገባቸዋለን”
ባል፤
“እስቲ ይቅናን! ወዳጄ”
ተያይዘው እሀይቁ ዳርቻ ደረሱ፡፡ መረቡን ዘረጉት፡፡ የተያዙት ግን በጣም ደቃቃ ደቃቃ ዓሳዎች ብቻ ናቸው፡፡
ሚስት፤ በጣም ገረማትና፤
“ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል፤ መረቡ ትናንሽ ዓሳዎችን ብቻ እየመረጠ ነው እንዴ የሚይዘው?” ስትል ባሏን ጠየቀችው፡፡
ባሏም፤
“ይሄውልሽ ጊዜው እንደዚህ ሆኗል፡፡ ትናንሾችን ዓሳዎች እኛ እንይዛቸዋለን፤ትላልቆቹ እርስ በርስ ይበላላሉ!!”
*       *      *
ዘመኑ እንደዚህ ነው! ትላልቆቹ ሌቦች አይነኩም፡፡ ትናንሾቹ ብቻ ይጠመዳሉ፡፡ ባለ ከፍተኛ ንግድና ሀብት ባለቤቶች የሚነካቸው የለም፡፡ ትናንሾቹ ጉልት ቸርቻሪዎች፣ ከገቢ ገማች እስከ ወንጀል መርማሪ ይፈራረቅባቸዋል፡፡ ይህንን ዕውነታ መለወጥ የትራንስፎርሜሽን ያህል ከባድ ነው፡፡ ምነው ቢሉ፣ ከባድ ከባድ፣ ንክኪ በሥሩ አለ፡፡ አብ ሲነካ ወልድ ይነካ ነው!
ስለሆነም የላይኞቹ ክፉኛ ይጮሀሉ!! የታችኞቹ ወንጀሉ የዓለም መጨረሻ እንደሆነ አድርገው ያወራሉ፤ ይጮሃሉ! ባለ ፎቆቹ፣ ባለ ቪላዎቹ፤ ባለ ብዙ ኤከር መሬት ባለቤቶቹ፤ ንፁሀን ሆነው ቁጭ ይላሉ! በየሸንጎውም ላይ ጨዋዎቹ እነዚህ ባለፀጎች ይሆኑና የክብር እንግዶች ተብለው ክብር ትሪቡን ውስጥ ይቀመጣሉ፡፡ አዳዲስ ተቋም ሲመረቅ መድረኩን ይሞላሉ፤ ግንባር ግንባር ቦታውን ያጣብባሉ! በደህና ጊዜ የአባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ እያሉ፣ የአንበሳውን ድርሻ ሲቀራመቱ የነበሩ ናቸው፡፡
በሌላ ወገን፤ ዝቅተኛው መደብ፣ ሱቁ ሲመዘበር፣ ያልሆነ ዋጋ ሲተመንበት፣ ሰሚ ያጣ ጩኸት ሲጮህና የአገር ያለህ፣ የመንግሥት ያለህ ሲል፤ “ስህተት ያለ ነገር ነው፤ ለቅሬታ ሰሚ አመልክት እንጂ ምን ታካብዳለህ” ይሆናል የምላሹ ዘይቤ! ሱቃቸውን ዘግተው የጠፉ፣ ዕቃቸውን ያሸሹ፣ ንብረት አናስገምትም ያሉት ዕውን ከግንዛቤ ማነስ ነውን? ግንዛቤ እንዲጨብጡ ተደርጎስ፣ ወደ ሰላማዊ ኑሮአቸው ተመልሰዋል ማለት ዕውን ነባራዊው ሀቅ ነውን? መሬትና ሰማይን ያነካካ ገመታ፣ የምስኪኑ ችርቻሮ ነጋዴ ደስታ ሊሆን ይችላልን? ግልፁ ጨዋታ ሌባው በወርቅ አልጋ፣ በእርግብ ላባ ላይ፣ ከዝሆን ጥርስ በተሰራ ፎቅ ውስጥ መኖሩ ነው! ማን ይንካው? የማይታረቁ ግጭቶች ተፋጠው ይገኛሉ!! የማይታረቁ ግጭቶችን ለመፍታት ቢያንስ ገጣሚና ፀሐፌ - ተውኔት መንግሥቱ ለማ፤ በባ‘ለ ካባና በባለዳባ’ ተውኔታቸው ውስጥ፡-
“ቀማኛን መቀማት፣ ከሌባ መስረቅ ……….. (‘ቅ’ ይጠብቃል)
ከማቅለል ከሆነ፣ የድሆችን ጭንቅ ………….. ( ‘ቅ’ ይጠብቃል)
በእኔ ቤት፣ ፅድቅ ነው፣ አንድ ሰው ይሙት …………(‘ሙት’ ይጠብቃል)
አንድ መቶ ሺ ሰው፣ ኪኖር በምፅዋት!!” …..…………(‘ዋት’ ይጠብቃል)
ያሉትን ማስታወስ ግድ ይሆናል!!
“እገሌ የእኛ ወገን ነው አይነካም”፤ “እገሌ የሌላ ወገን ነው፤ በለው!”፤ “እገሌ የማንም አይደለም ጊዜውን ይጠብቅ” …. “እነ እገሌን ተውዋቸው የኛ ናቸው” … “እነገሌን ግፏቸው ጠላት ናቸው” … ዓይነት አካሄድ፤ ቢያንስ ‹ከልጅ ልጅ ቢለዩ ዓመትም አይቆዩ› አለማወቅ ይሆናልና ልብና ልቦና ይስጠን!!
የሀገራችን አንድ ፈታኝ የሆነ ችግር፣ “ህዝቡ አያውቅም” የሚለው መላምታዊ ድንቁርና ነው፡፡ የነቃው፣ ህዝቡን በትግሉ ሲያግዝ የኖረው፣ በቀውጢው ሰዓት ታጋዮችን ከክልል ክልል ሲያሳልፍ የከረመው፤ ትልቅ አድናቆት ሲቸረው የኖረ ህዝብ፤ ድንገት ድንቁር ሊል ፈፅሞ አይችልም፡፡ እንደ ሁልጊዜው የግምት ስህተት አለ!! “ይሄን ስናሰላ፣ እንዲህ እንዲህ ያለ ችግር ነበረብን” የምንለውን እንኳ ዛሬ ስለተውነው፤ ከስህተት መታረም የሚለው ቁም - ነገር ጨርሶ ጠፍቷል፡፡ ከዚህ ይሰውረን!!
ትናንሾቹን ዓሳዎች አሳዶ የሚበላቸው አይጠፋም - አቅም የላቸውምና! ትላልቆቹ ግን እርስ በርስ እስኪበላሉ መጠበቅ ነው! ከዚህም ያውጣን!!

Saturday, 29 July 2017 11:30

የአዲስ አድማስ ማሳሰቢያ

    ያለወትሮአችን ማሳሰቢያ ለመፃፍ የተገደድነው አንዲት ስማችን የተጠቀሰባት ሃሰተኛ (‹ፎርጂድ› የበለጠ ይገልፀዋል) ደብዳቤ ሰሞኑን ዝግጅት ክፍላችን በመድረሷ ነው፡፡ ደብዳቤዋ የታለመችው ለቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ ፋብሪካ ነው፡፡ ‹‹ስፖንሰር አድርጉን›› ትላለች፡፡ መታለም ብቻ ሳይሆን ለፋብሪካውም ደርሳለች፡፡ ‹‹አፍሪካ ፖስት ሚዲያ ሴንተር›› በሚል ማህተም የተከተበችው ይህች ‹‹ጉደኛ›› ደብዳቤ፤ በአጭሩ ‹‹አዲስ አድማስ ጋዜጣ የተመሰረተበትን 15ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ፣ ሐምሌ 7 ቀን 2009 ዓ.ም ከአፍሪካ ፖስት ሚዲያ ሴንተር ጋር በመተባበር፣ በአዲስ አበባ ቲያትርና ባህል አዳራሽ በታላቅ ድምቀት ይከበራል›› በሚል መግቢያ ትጀምራለች፡፡ (ልብ በሉ! ‹‹አዲስ አድማስ›› 15ኛ ዓመቱን የዛሬ ሁለት ዓመት በብሔራዊ ቴአትር ‹‹በታላቅ ድምቀት›› አክብሯል፡፡
የሆነው ሆኖ፣ የ15ኛ ዓመት በዓላችንን እንዳከበርን ያላወቁት ወይም ያልሰሙት እነዚህ ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቀ ‹‹ ቁጭ በሉዎች››፤ (‹‹ሿሿ›› ነው የሚሏቸው?!) ዝግጅቱን በርካታ ድርጅቶች ስፖንሰር እንዳደረጉ ይጠቅሱና፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራም በዓይነትም በገንዘብም ስፖንሰር እንዲያደርጋቸው ይጠይቃሉ፡፡ (የአዲስ አድማስን 15ኛ ዓመት በዓል ማለት ነው፡፡) በርግጥ የቢራውም ሆነ የገንዘቡ መጠን አልተጠቀሰም በዚህ ቢያበቃ ጥሩ ነበር፡፡ ቢራ ፋብሪካው ስፖንሰር ሲያደርግ የሚያገኘውን ጥቅማ ጥቅም ይገልፃሉ- ‹‹ድርጅታችሁን በሚታተመው ተከታታይ ሳምታዊ የጋዜጣ ዕትም ላይ በብዙ ብር ከፍለው ስፖንሰር ካደረጉን ድርጅቶች እኩል የምናስተዋውቅ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን” በማለት፡፡
በነገራችሁ ላይ በዚህ የጋዜጣችንን ስም ለማጭበርበርያነት ጠቅሰው በፃፉት ደብዳቤ ላይ እውነተኛ ወይም ትክክለኛ የሚመስል ነገር አለ ከተባለ፣ ፅሁፉ የሰፈረበት ነጭ ወረቀት ብቻ ነው፡፡ በደብዳቤው ላይ የሰፈሩት ሁለት ስልክ ቁጥሮች ጨርሶ አይሰሩም። ‹‹አፍሪካ ፖስት ሚዲያ ሴንተር›› የሚባል ድርጅት በተጨባጭ መኖሩን ለማረጋገጥም አልቻልንም (ሊኖር እንደማይችል ገምቱ!)፡፡
በመጨረሻም፤ ለውድ የአዲስ አድማስ ቤተሰቦች፣ አንባቢያን፣ ድርጅቶች፣ የመንግስት ተቋማትና ሌሎችም ልንገልፅ የምንወደው፣ የአዲስ አድማስ ህጋዊ ማህተም፣ ሎጎ፣ በቂ አድራሻዎች … ወዘተ በቅጡ ሳትመለከቱ (ሳታጣሩ) ለደብዳቤዎች ጥያቄ ምላሽ እንዳትሰጡ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኞችም ሆኑ ተወካዮች የድርጅቱ መታወቂያ እንዳላቸው እግረመንገዳችንን ልንገልፅ እንወዳለን፡፡ ራሳችንን እንጠብቅ!!

    በአውሮፓና በአሜሪካ ከ120 በላይ ስኬታማ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን በማቅረብ የሚታወቀው የሬጌው አቀንቃኝ ኦጄኬን ኦሊቨር ወይም በመድረክ ስሙ “ፕሮቶጄ” ዛሬ ምሽት በላፍቶ ሞል ያቀነቅናል። “The Indignation” ተብሎ በሚጠራውና በሰባት ታዋቂ የሙዚቃ ተጫዋች የተደራጀው ሙሉ ባንዱ ታጅቦ የሚያቀነቅነው  የ33 ዓመ ከታወጀ 10 ወር ገደማ ያስቆጠረው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከ5 ቀን በኋላ ይነሳ ይቀጥል የሚታወቅ ሲሆን  ሰማያዊ ፓርቲ በበኩሉ፤የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከተነሳ፣ ሐምሌ 30 እና ነሐሴ 7 ቀን 2009 ዓ.ም፣ በአዲስ አበባ ህዝባዊ ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ ለመጥራት ማቀዱን አስታውቋል፡፡
ፓርቲው ሰሞኑን ባወጣው ወቅታዊ የአቋም መግለጫው፤አስር ወራትን ያስቆጠረው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የማብቂያው ጊዜ ከ5 ቀን በኋላ፣ መሆኑን በመጠቆም፣ አዋጁ ለተጨማሪ ጊዜያት እንዳይራዘም መንግስትን ጠይቋል፡፡ አዋጁ ተጥሎ በቆየባቸው ጊዜያት፤ “የዜጎችን ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች የጣሰ፣ የፖለቲካ ምህዳሩን ከመቼውም ጊዜ ይልቅ ያጠበበ፣ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እንዲያሽቆለቁል ያደረገና የህዝብን ማህበራዊ መስተጋብሮች የገታ ነበር” ያለው ሰማያዊ፤ “መንግስት ሀገሪቱን አረጋግቻለሁ ስላለ አዋጁን ማራዘም አያስፈልግም፤ ሊነሳ ይገባዋል” ብሏል፡፡ በቅርቡ በሚኒስትሮች ም/ቤት ተወስኖ፣ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የቀረበው የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ላይ ያለው ልዩ ጥቅም ረቂቅ አዋጅ፣ የአዲስ አበባና የኦሮሚያ ህዝብ ሳይመክርበት መውጣቱን ፓርቲው ተችቷል፡፡ የግብር አጣጣል ስርዓቱም የዜጎችን ገቢ ያገናዘበ እንዲሆን የጠየቀው ፓርቲው፤ በአጠቃላይ ህዝቡ በአግባቡ ሳይመክርባቸው እየወጡ ያሉ አዋጆች፣ በዜጎች ላይ መደናገጥ እየፈጠሩ በመሆኑ ሊታረሙ  ይገባል ሲል አሳስቧል።
“ሰማያዊ” የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሊነሳ ይችላል በሚል መተማመን፣ ሐምሌ 30፣ ከጠዋቱ 4 ሰዓት እስከ ቀኑ 9 ሰዓት ሜክሲኮ አደባባይ በሚገኘው የመብራት ሃይል አዳራሽ፣ ህዝባዊ ስብሰባ እንዲሁም ነሐሴ 7፣ መነሻውን ሚኒልክ አደባባይ፣መዳረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገ፣ ሰላማዊ ሠልፍ ለመጥራት ማቀዱን አስታውቋል፡፡ የስብሰባውም ሆነ የሰልፉ አጀንዳዎች፣ በዋናነት እየወጡ ባሉ አዋጆች ላይ እንደሚያተኩር ለአዲስ አድማስ ያስረዱት የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አበበ አካሉ፤ሰልፉም ሆነ ስብሰባው የታቀደው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ሊነሣ ይችላል በሚል ግምት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ቱ ፕሮቶጄ፤ ትላንት ከቀኑ 8፡00 ላይ በአምባሳደር ሆቴል ከኮንሰርቱ አዘጋጅ EML ኤቨንት ኦርጋናይዘርስ ጋር በጋራ በሰጠው መግለጫ፤ የዛሬው የላፍቶ ሞል ኮንሰርቱ በአፍሪካ የመጀመሪያው እንደሆነ ገልጿል፡፡ ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣቱ በፊት ጣሊያን፣ ስዊድን፣ ጀርመን፣ ፈረንሳይና ስፔይን ትልልቅ ኮንሰርቶችን እንዳቀረበና እዚህ ያለውን ስራ ሲጨርስም ወደ አውሮፓ ተመልሶ ስራውን እንደሚያቀርብ ተናግሯል፡፡
ዘፋኝ ባይሆን ኖሮ ሯጭ ይሆን እንደነበር በመግለጫው የጠቆመው ዘፋኙ፤ አትሌት ሃይሌ ገ/ሥላሴን ጨምሮ ብዙ የኢትዮጵያ አትሌቶችን በስም ጭምር እንደሚያውቅ የተናገረ ሲሆን “አትሌት ጥሩነሽ ዲባባን ከልቤ አደንቃለሁ” ብሏል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ሰሞኑን ለራስ ተፈሪያን የትውልደ ኢትዮጵያዊነት መብትና ዕውቅና መስጠቱን በተመለከተ የተጠየቀው ዘፋኙ፡-
“በጣም ትልቅና ታላቅ እድል ነው፡፡ እኛ ወደ ኢትዮጵያ መጥተን መኖር የምንፈልገው ለአገሪቷ ሸክም ለመሆን አይደለም፡፡ አላማ አለን፤ ራዕይ አለን፡፡ ጓዛችንን ጠቅልለን ስንመጣ ከእውቀት፣ ከሰፊ ልምድና ሙያ ጋር ነው፡፡ ኢትዮጵያ መጥተን ልንዝናና ወይም ሳንሰራ ተቀምጠን ለመኖር አይደለም፡፡ ማንም ራስ ተፈሪያን ወደ ኢትዮጵያ ለመምጣት ሲያስብ፣ የራሱን ሀሳብ ይዞ ነው፡፡ ያንን ሀሳብ የሚፈፅመውም ኢትዮጵያን ለመጥቀም ነው” ሲል መልሷል፡፡ከዚህ በፊት ይከሰት የነበረውን ትርምስና ጭንቅንቅ ለማስቀረት ሲባል ተጨማሪ ባሮች በላፍቶ ሞል መዘጋጀታቸውን የጠቆሙት አቶ ኢዩኤል፤ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ ተመልካቾች ወደ አዳራሹ መግባት ይጀምራሉ ብለዋል፡፡ ኮንሰርቱ ቀድመው ትኬት ለገዙ 300 ብር፣ በዕለቱ ለሚገዙ በመደበኛው 500 ብር፣ በቪአይፒ 700 ብር የመግቢያ ዋጋ ተተምኖለታል፡፡


  ሜላት ተመስገን፣ የ15 ዓመት ታዳጊ ስትሆን የአንደኛ ደረጃ መልቀቂያ (8ኛ ክፍል) ፈተና ወስዳ አጥጋቢ ውጤት በማምጣት (85.5 በመቶ) ወደ 9ኛ ክፍል ተዛውራለች፡፡ ሜላት፣ ከአያቷ ጋር ነው የምትኖረው፡፡ አያቷ ደግሞ ሁለቱን ማኖር የሚያስችል ገቢ የላቸውም፡፡ በየሰው ቤቱ ልብስ እያጠቡ በሚያገኙት አነስተኛ ገቢ ነው የሚተዳደሩት፡፡ ይህ የአያቷ አቅመ ደካማነትና የገቢ ማነስ ነው በብርሃን ይሁን ኢትዮጵያ ድጋፍ እንዲደረግላት ያስመረጣት፡፡
ብርሃን ይሁን ኢትዮጵያ፤ ለሜላትና ለሌሎች የተመረጡ ተማሪዎች ምን ዓይነት ድጋፍ እያደረገ ይሆን? ሜላት እንዲህ ትገልጻለች፡- “ድርጅቱ አሪፍ ድጋፍ እያደረገልን ነው፡፡ ለምንማርበት እውቀት በኅብረት  ት/ቤት የዓመት  ይከፍልልናል። ለመማር አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁስ፣ ዩኒፎርም፣ ደብተር፣ መጻሕፍት፣ ቦርሳ፣ ልብስ ይሰጠናል። በትምህርታችን ጎብዘን፣ ውጤታማ ሆነን የተሻለ ደረጃ ላይ እንድንደርስ ከፍተኛ ድጋፍ ያደርግልናል፡፡ ድሮ የነበረንን የአጠናን ዘዴ ቀይረን፣ አዲስና ውጤታማ የጥናት ዘዴ እቅድ እንድናወጣ ረድተውናል፡፡ በዚህም ዘዴ ተሳክቶልኛል፡፡ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስጄ 85.5 በመቶ ነው ያመጣሁት” ብላለች።
ሲሳይ ኃይለየሱስ የ14 ዓመት ታዳጊ ሲሆን፣ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዶ ውጤት ስላልመጣለት ደጋሚ ነው፡፡ ሲሳይ እናቱ በህይወት ስለሌሉ የሚኖረው ከአባቱ ጋር ነው፡፡ አሁን እንኳ አነስተኛ ግሮሰሪ ስለከፈቱ ትንሽ ይሻላል እንጂ ከ3 ዓመት በፊት እሱ በብርሃን ይሁን ኢትዮጵያ ድጋፍ እንዲደረግለት ሲመረጥ የአባቱ ገቢ የሚያወላዳ አልነበረም። ዘነበወርቅ ሪፈራል ሆስፒታል (አለርት) ውስጥ ካርድ ጠሪ ስለሆኑ ገቢያቸው በጣም አነስተኛ ነበር፡፡ ሲሳይ፤ ብርሃን ይሁን ኢትዮጵያ ስለሚያደርግላቸው ድጋፍ ሲናገር፤ ሜላት ያለቻቸውን አገልግሎቶች ጠቅሶ፤ “በየቀኑ ምሳና ራታችንን ያበላናል፡፡ 9፡30 ከት/ቤት ወጥተን ወደ ግቢ ነው የምንሄደው፡፡ እዚያ በጎ ፈቃደኞች ስላሉ ያስጠኑናል፡፡ በክረምት ደግሞ አስጠኚ መምህራን ይቀጥሩልናል፡፡ ንጽህናችንን እንድንጠብቅ በየሳምንቱ የተለያዩ ሳሙናዎች ይሰጡናል፡፡ ልብሳችንን እናጥባለን፤ ገላና ፀጉራችን እንታጠባለን፡፡ ሴት ተማሪዎች ፀጉራቸውን ተጣጥበው እርስ በርስ ይሰራራሉ” በማለት ገልጿል።
ሃዳስ ዘሩ አባቷን በሞት ስለተነጠቀች ከእናቷ ጋር ነው የምትኖረው፡፡ ወደፊት ሐኪም  የመሆን ህልም እንዳላት የጠቀሰችው ሃዳስ፣ የ16 ዓመት ታዳጊ ስትሆን  በ1ኛ ሴሚስተር 2ኛ፣ በ2ኛ ሴሚስተር ደግሞ 3ኛ ደረጃ አግኝታ በአማካይ ውጤት 86 በማምጣት፣ ወደ 10ኛ ክፍል ተዛውራለች፡፡ እናቷ ምንም ገቢ የላቸውም፡፡ “ገቢያችን የሰው እጅ ማየት ነው” ብላለች ሃዳስ፡፡ ከአምስት ዓመት በፊት ጥሩ ውጤት እያላቸው በድጋፍ እጦት ትምህርታቸውን ማቋረጥ የለባቸውም ተብሎ፣ ጥሩ ውጤት ስለነበራት መመረጧን ተናግራለች፡፡ ብርሃን ይሁን ኢትዮጵያ የሚያደርግላቸውን ድጋፍ፣ ቀደም ሲል ሁለቱ ተማሪዎች እንዳሉት በማድነቅ ዘርዝራ፣ ለጥናት ከፍተኛ ትኩረት እንደሚሰጡ ገልጻለች፡፡ ‹‹ክረምት ላይ አስጠኚ መምህራን ይቀጠራሉ፤ከመስከረም-ሰኔ ድረስ ግዙበራ ሳህና በበጎ ፈቃደኞች ድጋፍ እንድታጠና ይደረጋል›› ብላለች፡፡
ተማሪዎቹን አግኝተን ያነጋገርነው በደቡብ አፍሪካ ኤምባሲ ነው፡፡ ባለፈው ማክሰኞ ኔልሰን ማንዴላ በሕይወት ቆይተው ቢሆን ኖሮ 99ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን ያከብሩ ነበር፡፡ በሕይወት ባይኖሩም፤ የተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባኤ፣ በ2001 ዓ.ም ኔልሰን ማንዴላ ለደቡብ አፍሪካና ለመላው ዓለም ላበረከቱት አስተዋጽኦ፣ የልደታቸው ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲከበር በወሰነው መሠረት፣ የደቡብ አፍሪካ ኤምባሲም ዕለቱን፣ እንደ ኔልሰን ማንዴላ ጥሩ ተግባር እየፈፀመ የሚገኘው ብርሃን ይሁን ኢትዮጵያ ድጋፍ ከሚያደርግላቸውና ከ12-16 ዓመት ዕድሜ ካላቸው 39 ህፃናት ጋር አሳልፏል፡፡
የመንግሥታቱ ድርጅት፣ የኔልሰን ማንዴላ የልደት ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ እያንዳንዱ አገር እንዲያከብረው ከመወሰኑ አንድ ዓመት በፊት፣ ማንዴላ ለድርጅቱ ስልክ ደውለው፤ ‹‹እያንዳንዱ የዓለም ዜጋ ዓለምን ወደ ተሻለ ደረጃ ለመለወጥ በተለይም ለሕፃናት፣ ቢያንስ የ67 ደቂቃ መስዋዕትነት መክፈል ይጠበቅበታል›› ብለው ባሳሰቡት መሠረት፣ የኤምባሲው አባላት ጊዜአቸውንና ከግል ገንዘባቸው 85 ሺህ ብር በማውጣት ለተጠቀሱት ሕፃናት ስጦታ (የተለያዩ ልብሶችና ጫማዎች) ገዝተው ማበርከታቸውን አስታውቀዋል፡፡
‹‹የብዙ ልጆች ወላጆች አካል ጉዳተኞች ናቸው። የአምስት ልጆች ወላጆች ማየት አይችሉም፡፡ ሌሎች ደግሞ የተለያየ የአካል ጉዳት፣ ሥጋ ደዌ፣ ኤችአይቪ/ ኤድስ ያለባቸው ናቸው፡፡ ተስፋቸው ልመና ብቻ ነው፡፡ ልጆቻቸው ካልደረሱላቸው ሕይወታቸው አይለወጥም፡፡ እነዚህ ልጆች ድጋፍ አግኝተው፣ ተምረው፣ ሕይወታቸው ተለውጦና ውጤታማ ሆነው ለቤተሰቦቻቸው ሲደርሱ ማየት ነው ግባችን፡፡ ልጆቹ ተምረው ራሳቸውን ከቻሉ የቤተሰቦቻቸው ህይወት ይለወጣል የሚል እምነት አለን፡፡ ለአካባቢውም ሞዴል ይሆናሉ፡፡ ቆሬ አካባቢ የተማረ ኅብረተሰብ ማየት ነው ዓላማችን›› ያሉት ደግሞ የብርሃን ይሁን ኢትዮጵያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ወ/ሮ መንበረ በቀለ ናቸው፡፡
“ዋናው ትኩረታችን፣ ተማሪዎች የትምህርት እገዛ አግኝተውና  የተሻለ ውጤት አምጥተው አካባቢውን የሚለውጡ ዜጎችን መፍጠር ነው፡፡ ቆሬ አካባቢ ያለ ሰው አብዛኛው ድሃ ነው፡፡ የምንረዳቸው ልጆች ወላጆች አብዛኞቹ በልመናና ቆሻሻ በመልቀም የሚተዳደሩ ናቸው፡፡ ተማሪዎች በቂ ምግብ አያገኙም፡፡ ተምረውና ሕይወታቸው ተለውጦ የተሻለ ሰው እንዲሆኑ እገዛ እናደርጋለን ያሉት ወ/ሮ መንበረ፤ ለሰው ልጅ  ዋነኛው አስፈላጊ ነገር ምግብ ስለሆነ በየቀኑ ምሳና እራት ይመገባሉ፡፡ ደብተርና መጻሕፍት መያዣ ቦርሳን ጨምሮ የትምህርት መሳሪያ ወጪያቸው ይሸፈናል፡፡ ለሚማሩበት ት/ቤት ዓመታዊ ወጪ ይከፈላል፡፡ ዩኒፎም፣ ልብስና ጫማ ይገዛላቸዋል፡፡ ጤናቸውን እንከታተላለን፡፡ የታመመ ልጅ ካጋጠመን እናሳክማለን፡፡ ፈቃደኛ በጎ አድራጊ ሐኪም ሲገኝ ደግሞ ሁሉም የጤና ምርመራ ይደረግላቸዋል፡፡ የጥናት ፕሮግራምም ቀርፀው እንዲያጠኑ እናደርጋለን፣ በጥብቅ እንከታተላለንም›› ብለዋል ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ፡፡
ብርሃን ይሁን ኢትዮጵያ የራሱ ገቢ የለውም። ኢትዮጵያውያን ወዳጆቻችንን፣ ጓደኞቻችንንና ቤተሰቦቻችንን ድጋፍ እንዲያደርጉልን እንጠይቃለን። የአንድ ወይም የሁለት ልጅ የወር ወጪ የሚያግዙን ሰዎች አሉ፡፡ ከውጭ የምናገኘው ድጋፍ በጣም ትንሽ ስለሆነ እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡ በዚህ አጋጣሚ ጅምራችን እንደተገለፀው ነው፡፡ መጨረሻችንም ያማረና ስኬታማ፣ ልጆቹም ተለውጠው፣ የወላጆቻቸውን ሕይወት የሚለውጡና ጥሩ አገር ተረካቢ ዜጋ እንዲሆኑ፣ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን የተቻላችሁን ድጋፍ እንድታደርጉልን እጠይቃለሁ›› ብለዋል ወ/ሮ መንበረ በቀለ፡፡
የደቡብ አፍሪካ ኤምባሲ ሠራተኞች ገንዘብ አዋጥተው የገዙትን ልብስ፣ ጫማ፣ የትምህርት ቁሳቁስ፣ የንጽህና መጠበቂያ፤…. ስጦታ ለተማሪዎቹ የሰጡት በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር፣ በአፍሪካ ኅብረትና በመንግሥቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቋሚ ተወካይ፣ ሚ/ር አዱሚዶ ኒሺንጋ ሲሆኑ አንድ ተማሪ የሠራው ሥዕልም ተበርክቶላቸዋል፡፡

  በደራሲ ተስፋዬ አለነ የተሰናዳው “የሚስት ምርቃት” ልብ ወለድ መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ መፅሐፉ በጥቅሉ በፍቅር፣ በማህበራዊና በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ
የሚያጠነጥኑ 20 አጫጭር ልብ ወለድ ታሪኮችን ያካተተ ሲሆን ከዚያ ውስጥ “ስደተኛው ፍቅር” የተሰኘው ታሪክ ግን በእውነተኛ ታሪክ ላይ ያተኮረ መሆኑን ደራሲው ተናግሯል፡፡ በ216 ገፅ የተመጠነው መፅሐፉ በ61 ብር ከ20 ሳንቲም ለገበያ የቀረበ ነው፡፡ አምስተኛ ስራውን ሰሞኑን ለአንባቢ ጀባ ያለው ደራሲ ተስፋዬ አለነ በተለያዩ ጋዜጦችና መፅሄቶች አዝናኝ ወጎችን በመፃፍ የሚታወቅ ሲሆን ከዚህ ቀደምም “የመንጌ ውሽሚት”፣ “እንክልካይ”፣ “ዘላለማዊ ጓደኝነት” እና “Effective English” የተሰኙ መፅሐፍትን ለንባብ ማብቃቱ ይታወቃል፡፡

ሚዳቆ የመጻሕፍት አሳታሚዎች ደርጅት ትላንት ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ጀምሮ “የኮሪያ ዘመቻ”፣ “የአድዋ ድል” “የእነ ሳራ ዛፍ” እና “የሳራ ጥያቄ” የተባሉትን የህፃናት መፅሐፍ መስቀል አደባባይ ከቀይ ሽብር ሰማዕታት ሙዚየም ጀርባ በሚገኘው አዲስ አበበ ሙዚየም ውስጥ አስመረቀ፡፡ በዕለቱ የምረቃ ስነ ስርዓቱን መድረክ ደራሲ፣ ዳይሬክተርና ተዋናይት አዜብ ወርቁ የመራች ሲሆን ደራሲ እንዳለጌታ ከበደም በእንግድነት ተገኝቶ መፅሐፍቱን መመረቁ ታውቋል፡፡ በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ፀሐፍት፣ ሰዓሊዎች፣ አርታኢዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመው እንደነበር ሚዳቆ አሳታሚዎች ለአዲስ አድማስ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡

 በአርቲስት ዓለምፀሐይ ወዳጆና በሙያ ባልደረቦቿ የሚመራውና መቀመጫውን አሜሪካ ያደረገው ዓመታዊ የኪነ ጥበብ ምሽት የፊታችን ሐሙስ ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ በአክሱም ሆቴል ይካሄዳል፡፡
በዕለቱ የተለያዩ ግጥሞችች፣ ወጎች፣ መነባንብ፣ በአርቲስት ታምሩ ንጉሴ የሚቀርብ የክራር ሙዚቃና ሌሎችም የኪነ ጥበብ ድግሶች ይቀርባሉ፡፡
የኢትዮጵያን ኪነ ጥበብ ለማሳደግና ለወጣት የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች መድረክ ለመፍጠር ታልሞ በየዓመቱ በሚዘጋጀው በዚህ ምሽት ላይ ምልዕቲ ኪሮስ፣ ወሰን ሰገድ ገ/ኪዳን፣ በላይ በቀለ ወያ፣ ሰለሞን ሞገስና ሌሎችም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ የተባለ ሲሆን በአገራችን የቅኔ ባህል ዙሪያ ባለ ቅኔው ዶ/ር ታደለ ገድሌ የቅኔ ዲስኩር ያቀርባሉም ተብሏል፡፡
በዕለቱ የኪነ ጥበብ አፍቃሪ በነፃ ምሽቱን እንዲታደም ግብዣ ቀርቧል፡፡

     70 ሺህ ሄክታር እርሻ እና ከ100 በላይ የአልማዝና ወርቅ ማምረቻ ፈቃድ አላቸው

      የኮንጎው ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ካቢላ እና ቤተሰባቸው በአገር ውስጥና በውጭ አገራት በሚንቀሳቀሱ መሪ ከ80 በላይ ታላላቅ የንግድ ኩባንያዎች ውስጥ ጠቀም ያለ የባለቤትነት ድርሻ እንዳላቸውና አጠቃላይ ሃብታቸው በአስር ሚሊዮኖች ዶላር እንደሚቆጠር ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
ተቀማጭነቱ በአሜሪካ የሆነው ኮንጎ ሪሰርች ግሩፕ የተባለው የጥናት ተቋም ያወጣውን የጥናት ውጤት ጠቅሶ ሮይተርስ ከትናንት በስቲያ ባወጣው ዘገባ እንዳለው፣ ጆሴፍ ካቢላ እና ቤተሰባቸው በኩባንያዎቹ ውስጥ ካላቸው የባለቤትነት ድርሻ በተጨማሪ፣ 70 ሺህ ሄክታር የእርሻ መሬትና አልማዝና ወርቅ ማምረት የሚያስችሉ ከ100 በላይ የማዕድን ፍለጋ ንግድ ፈቃዶች አሏቸው፡፡
በ2001 አባታቸውን ተክተው ወደ ስልጣን መምጣታቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ ምንም እንኳን የስልጣን ዘመናቸው ያበቃው ባለፈው ታህሳስ ወር ላይ ቢሆንም፣ ስልጣኔን አልለቅም ብለው በመሪነታቸው መቀጠላቸውን አመልክቷል፡፡
በተያያዘ ዜናም በሙስና ከፍተኛ የህዝብ ገንዘብ መዝብረዋል በሚል ክስ የተመሰረተባቸውን የናይጀሪያ የቀድሞ የነዳጅ ሚኒስትር ዲዛኒ አሊሰን ማዱኬ ጉዳይ ሲመረምር የቆየው ፍርድ ቤት፣ የግለሰቧን 37 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ንብረት እንዳይንቀሳቀስ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ያስተላለፈበት እጅግ ዘመናዊ ቤት ሲሆን፣ ለንደን ውስጥ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ በዋስ ተፈትተው በዚያው የሚገኙት የቀድሞዋ ሚኒስትር ቤቱን የገዙት ከመንግስት ካዘና ያለአግባብ በመዘበሩት 37.5 ዶላር ነው መባሉን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል፡፡