Administrator

Administrator

በሃገራችን በጃዝ ሙዚቃ ዘርፍ ከ50 ዓመታት በላይ የሚታወቀው  አርቲስት ሙላቱ አስታጥቄ (የክቡር ዶ/ር)፣ ከአድናቂዎቹ ጋር የሚገናኝበትና እራት የሚበላበት ልዩ ምሽት መዘጋጀቱ ተገለጸ፡፡
የታዋቂ ኤቨንት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሳሙኤል አበራና የጃዝ ንጉስ ሙላቱ አስታጥቄ፣ የእራት ምሽቱን አስመልክቶ ባለፈው ሳምንት  ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫው ላይ እንደተብራራው፤ አርቲስት

ሙላቱ አስታጥቄ፣ የካቲት 9 ቀን 2016 ዓ.ም ምሽት፣ በግዮን ሆቴል በሚገኘው አፍሪካ ጃዝ መንደር፣ ከአድናቂዎቹ ጋር ተገናኝቶ ራት እንደሚበላና ፊርማውን እንደሚያኖር ታውቋል፡፡ የፎቶግራፍ መነሳት መርሃ

ግብር እንደሚኖርም ተነግሯል፡፡ በዝግጅቱ ላይ ተጋባዥ እንግዶችና ታዋቂ የኪነጥበብ ባለሙያዎች እንዲሁም የአርቲስቱ  አድናቂዎች ይገኛሉ ተብሏል፡፡
የተለያዩ ኹነቶችን በማዘጋጀት የሚታወቀው ታዋቂ ኤቨንት፣ ከዚህ ቀደም አርቲስት ሰላም ተስፋዬን በሸራተን አዲስ ሆቴል ከአድናቂዎቿ ጋር በማገናኘት፣ ራት የመብላትና የፎቶግራፍ መነሳት መርሃ ግብር በስኬት

ማካሄዱ ተመልክቷል፡፡  
በውጭው ዓለም ይህን መሰሉ ዝነኞችን ከአድናቂዎቻቸው ጋር የማገናኘትና አይረሴ ቅጽበቶችንና አጋጣሚዎችን የመፍጠር መርሃ ግብሮች በእጅጉ የተለመዱና የሚዘወተሩ እንደሆኑ ይታወቃል፡፡
የጃዝ ንጉሱ አርቲስት ሙላቱ አስታጥቄ በአገሩ ብቻ ሳይሆን፣ በውጭው ዓለም  የሙዚቃ መድረኮችም ከፍተኛ አድናቆትንና ዕውቅናን ያተረፈ አንጋፋ  የሙዚቃ ባለሙያ  ነው፡፡


ከማኅበራዊ ድረገፅ

 ዋስይሁን ተስፋዬ)

ይህ ናይጄሪያዊ ህጻን  ተስፋ ይባላል .. ለባእድ አምልኮ እራሳቸውን ያስገዙት ቤተሰቦቹ ለሞት አሳልፈው ሊሰጡት ከቤት አውጥተው በጭካኔ በጎዳና ላይ ሲወረውሩት ምንም አልመሰላቸውም።  ምክንያቱም

ለነሱ ከዚህ ነብስ ከማያውቅ ምስኪን ህጻን ይልቅ .. የህጻኑን “ሟርተኛ”  እና “መአት አምጭ”  .. መሆን የተነበየላቸው  ጠንቋይ ያስፈራቸዋልና፣ አውጥተው ከጎዳና ጣሉት.። (በነገራችን ላይ በባእድ

አምልኮ ምክንያት ህጻናትን አውጥቶ መጣል በናይጄሪያ የተለመደ ነው)  በዚህ ምክንያት፤ የጭካኔ ውሳኔ ተወስኖበት  ከሞቀ ቤት ወጥቶ የተጣለው ይህ ህጻን  ቤተሰቦቹ እንዳሰቡት ቶሎ የሚሞት አልሆነም

...... ከእናቱ እቅፍ ተነጥቆ እራሱን ባገኘበት  አንዲት መንደር ውስጥ በትናንሽ እግሮቹ ከወዲያ ወዲህ እየባዘነ ያገኘውን ለቃቅሞ እየበላ .. በወደቀበት ተኝቶ እየተነሳ ከሩቅ የታሰበለትን በጎ ነገር ያወቀ

ይመስል ሞትን እንቢ ብሎ ....የሌሊቱ  ውርጭና የቀኑ  ሃሩር እየተፈራረቀበት፣ በጽናት ቢቆይም  8ኛው ወር ላይ ግን ለሞት እጁን የሰጠ መሰለ ..
እነዚያ ወዳላሰበበት የመሩት ሰዎች የሚወረውሩለትን ወደ አፉ እንዲያደርግ የሚረዱት እግሮቹ ረሃብ አዛላቸው ..እናም አንድ ሌሊት ከተኛበት ሜዳ ላይ መነሳት እንዳቃተው ቀረ .........በዚህ ቅጽበት

..Anja Ringgren በምትባል በጎ አድራጊ ተመስለው የፈጣሪ እጆች ወደሱ ቀረቡ፤ በሆላንዳዊትዋ በጎ አድራጎት ሰራተኛ ከወደቀበት ቦታ ተገኝቶ ሲነሳ የጎድን አጥንቶቹ የሚቆጠሩ፣ ከህይወት ይልቅ ለሞት

የቀረበ በፓራሳይት የተጎዳ በረሃብ የደቀቀ ... እጅግ አሳዛኝ ህጻን ነበር፡፡ ይህች መልካም ሴት ከወደቀበት አንስታ፣ አዲስ ህይወትና አዲስ ስም ሰጠችው፡፡እናም የሞት አፋፍ ላይ ላይ ወዳለው ምስኪን ህጻን

ተጠግታም...
“ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተስፋ (HOPE) ይባላል “ .. ስትል አንሾካሾከችለት፡፡
***
አሁን ያ ሁሉ አልፏል .. HOPE በአንድ ወቅት ከሞት ጋር ፊት ለፊት ተገናኝቶ የሚያውቅ አይመስልም .... በአካሉ በርትቶ ደስ የሚል ቆንጅዬ ልጅ ሆኖ፣ በበጎ አድራጊዋ Anja Ringgren

በሚመራው የበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥ ከሚያድጉ ህጻናት ጋር እየኖረ ነው፡፡....
ከተስፋ በተጨማሪ፤ በተመሳሳይ ሌሎች ህጻናትን ከወደቁበት አንስታ ያሳደገችው በጎ አድራጊዋ Anja Ringgren፤ እነዚህ በወላጆቻቸው ተገፍተው የተጣሉ ህጻናት ከየት እንደመጡ፣ ወላጆቻቸው እነማን

እንደሆኑ ሊያውቁ ይገባል ብላ ታምናለችና. .. በቅርቡ በህጻንነት እድሜው አውጥተው የጣሉትን የተስፋን ወላጆች አፈላልጋ ነበር። በአንድነት ተስማምተው ልጃቸውን የጣሉት ባልና ሚስት ትዳራቸው ፈርሶ

በመለያየታቸው ምክንያት እናትየውን ማግኘት ባይቻልም፣ ከአባቱ ጋር እንዲገናኝና አባቱ እሱ መሆኑን እንዲያውቅ  አድርጋው ነበር። HOPE አባቱን ካገኘና አብሮ ፎቶ ከተነሳ በኋላ፣ ከወደቀበት ወዳነሳችው አሳዳጊ

እናቱ ቤት ተመልሷል።
እዚህ ላይ ግን በጭካኔ አውጥቶ የጣለው አባት፣ ያለሀፍረት ልጁን ለማግኘት መፈለጉ ለብዙዎች አስገርሟል።
***
ቅን ልብና መልካም አስተሳሰብ ካለ ተአምር መስራት ይቻላል፡፡

በግርማ ሙዚቃዎች ውስጥ ሁሉ ያለችው ሴት አንድ ናት፡፡ የሚወዳት የሚያኮርፋት፣ የሚቀርባት የሚርቃት እሷን ብቻ ነው - እጸገነትን፡፡ እጸገነት ገብረሥላሴ የልጅነቱ ናት፤ የልጁም እናት፡፡ በንጹሕ ልቡ የወደዳት፤

የምትወደው፡፡ “ሴት አላምንም” ፣ “ትወጅኝ እንደሁ”፣”ቁርጡን ንገሪኝ” እና “ፍቅር እንደክራር”ብሎ ያዜመላት፡፡ “ይበቃናል” ብሎ ያንጎራጎረውም ለእጸገነት ነው- የራቀችው ቢመስለው፡፡ ግን አይሆንለትም፡፡

“ጥሩልኝ ቶሎ” ይላል፡፡
አቃተኝ ፍፁም መለየት
እሷን ከመሰለ ወጣት
ጥሩልኝ ቶሎ በፍጥነት
ትድረስ በነፍሴ ሳልሞት
ፍፁም ፍፁም አልተዋትም
ካለሁ በሕይወት አረሳትም...
“ጥሩልኝ ቶሎ” የግርማ የአፍላነት ዜማ ነበር፡፡ ኋላ ግን የአሳዛኝ ሕይወቱ ማጀቢያ ሙዚቃ ሆነ፡፡ በፍቅራቸው ሰሞን ስትጠፋበት “ጥሩልኝ ቶሎ” ብሎ ያንጎራጎረላት እጸገነት፤ በጎልማሳነቱ ዘመን ጥላው ሔደች -

ወደ አምላኳ፡፡ ግርማ ከዚያ በኋላ ሙዚቃን ፈራ፡፡ በብዙ ጉትጎታ ተመልሶ ሲመጣም ከእጸገነት መራቅ ተሳነው፡፡ “Mistakes on purpose” ብሎ በሰየመው የሙዚቃ አልበሙ ላይም “በመልክሽ

አይደለም” በተሰኘ ዜማው፤ የልጅነት ፍቅሩን ዘከረ፡፡ በካንሰር ሕመም ካለፈች 32 ዓመታት ቢሞላትም፣ ዛሬም ፎቶዋን አቅፎ እንደሚተኛ አንጎራጎረ፡፡
እስኪመሽ እናፍቃለሁ፤ እስክተኛም እጓጓለሁ፤ ምክንያቱም ጸጊን ስለማገኛት አለ፡፡ ግርማ ዕድሜውን ሙሉ የዘፈነላት ሴት አሁንም አብራው እንዳለች ያስባል፡፡ በጊዜ ቤቱ ገብቶ ከፎቶዋ ጋር ሲጫወት ያመሻል፡፡ እኔም

ተራው ደርሶኝ በድጋሚ እስካገኛት እያለ፡፡...!

የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር በ4 ዘርፍ ሽልማቶችን ይሰጣል
በጉባኤው ከ100 በላይ ድርጅቶች ይሳተፉበታል ተብሏል



60ኛው ዓመታዊ የህክምና ጉባኤና ዓለማቀፍ የጤና አውደ ርዕይ ሊካሄድ ነው
የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር በ4 ዘርፍ ሽልማቶችን ይሰጣል
በጉባኤው ከ100 በላይ ድርጅቶች ይሳተፉበታል ተብሏል

ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ማግኘት የሚችል ጤናማና የበለፀገ ማህበረሰብ የማየት ራዕይ ያነገበው የኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር፣ ዘንድሮ 60ኛውን ዓመታዊ የህክምና ጉባኤና ዓለማቀፍ አውደ ርዕይ፣ ከየካቲት

29-30 ቀን 2016 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል እንደሚያካሂድ አስታወቀ፡፡
ዓመታዊው የህክምና ኮንፈረንስ በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚኖሩ ዕውቅ የህክምና ባለሙያዎች ያላቸውን ዕውቀት፣ የምርምር ግኝቶችንና የህክምና ልምዶችን ለመለዋወጥ የሚረዳ መድረክ መሆኑን የገለፀው

ማህበሩ፤ የፓናል ውይይቶችም እንደሚካሄድበት ጠቁሟል፡፡
በህክምና ጉባኤው የሙያ ማሻሻያ ሥልጠናዎች እንደሚሰጡና የሳይንሳዊ ግኝቶች የሚቀርቡበት ክፍለ ጊዜም መዘጋጀቱ ተገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር 60ኛው ዓመታዊ የህክምና ጉባኤና ዓለማቀፍ የጤና አውደ ርዕይ ላይ ከ600 በላይ የተከበሩ የህክምና ባለሙያዎች፣ ከተለያዩ ክልሎች የሚመጡ የማህበሩ አባላት ተወካዮች፣ የተለያዩ

የጤና ባለሙያዎች ማህበራትና ስፔሻሊስቶች ማህበራት የተውጣጡ ተወካዮች እንዲሁም የህክምና ኮሌጅ ሃላፊዎች ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡
በአውደርዕዩ ከ100 በላይ ድርጅቶች እንደሚሳተፉበትና ከ2ሺ በላይ ሰዎች ይጎበኙታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ማህበሩ ጠቁሟል፡፡ በየዓመቱ የሚጠበቀው የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር የሽልማት መርሃ ግብርም በአራት

ዘርፎች እንደሚሰጥ ታውቋል፡፡ ሽልማቶቹም፤ “የኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር የዓመቱ ምርጥ የህክምና ተማሪዎች ሽልማት 2016”፣ “የኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር የህይወት ዘመን ሽልማት 2016”፣”የኢትዮጵያ

ሕክምና ማህበር ተፅዕኖ ፈጣሪና ምርጥ ወጣት ሃኪም ሽልማት 2016” እና “የኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር የ2016 የዓመቱ ምርጥ ተቋም” ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ የሕክምና ማህበር የተመሰረተው በ1954 ዓ.ም መሆኑ ይታወቃል፡፡

በቅርቡ 16 እህት ኩባንያዎችን እንደሚከፍት ተጠቁሟል
* በቀጣዮቹ ወራት 24 የቴክኖሎጂ ፕላትፎርሞችን ተደራሽ ያደርጋል

ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ፤ ከገበሬው ቴክኖሎጂ ሶሉሽን የተሰኘ እህት ኩባንያ በመመሥረት ስድስት የቴክኖሎጂ መተግበሪያዎችን አስተዋወቀ፡፡ TርTዝ ብላክ፤ የቴክኖሎጂ መተግበሪያዎቹን ያስተዋወቀው ከትላንት በስቲያ ሐሙስ ሰንጋተራ በሚገኘው የኩባንያው ዋና መ/ቤት ውስጥ በተዘጋጀው ከገበሬው ቴክኖሎጂ ሶሉሽን  የምረቃ ሥነስርዓት ላይ ነው፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ መሥራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ፣ ኩባንያው ያበለፀጋቸውን ስድስት የቴክኖሎጂ መተግበሪያዎችን ያስተዋወቁ ሲሆን፤ ፐርፐዝ ብላክ በቀጣይ ወራት 24 የቴክኖሎጂ ፕላትፎርሞችን ተደራሽ እንደሚያደርግም አብስረዋል፡፡
ኩባንያው ትኩረቱን ቴክኖሎጂ ላይ ያደረገበትን ምክንያት ያስረዱት ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ፤ የTርTዝ ብላክ ኢትዮጵያ ትልቁ ዓላማው፣ የጥቁር ህዝቦች ኢኮኖሚ ልህቀትን መፍጠር በመሆኑ ነው ብለዋል፡፡
“TርTዝ ብላክ ኢትዮጵያ የንግድ አክሲዮን ማህበር፣ በዓለማቀፍ ደረጃ በጥቁር ህዝቦች ላይ ለዘመናት የቀጠለውን አድሎአዊ ሥርዓት በቢዝነስ ሞዴል በሚረጋገጥ የኢኮኖሚ የበላይነት ለማመዛዘን የተቋቋመ ኩባንያ ነው፡፡” ተብሏል፡፡
ባለፈው ሐሙስ በተካሄደው የከገበሬው ቴክኖሎጂ የምረቃ ስነስርዓት ላይ ስድስት የቴክኖሎጂ መተግበሪያዎች የተዋወቁ ሲሆን፤ ኩባንያው ከዚህ ቀደም ኢ-ኮሜርስ ማስተዋወቁ ይታወሳል፡፡በከገበሬው ቴክኖሎጂ ሶሉሽን አማካኝነት ከተዋወቁት መተግበሪያዎች ውስጥ “የከገበሬው የግብርና ምርቶች አቅርቦት” መተግበሪያ አንዱ ሲሆን፤ ገበሬው ከሸማቹ ጋር የሚገናኝበት መድረክ ነው ተብሏል፡፡“ገበሬዎች ምርታቸውን ከሸማቹ ጋር ማገናኘት አለመቻላቸው ነው ድሃ አድርጎ ያስቀራቸው” ያሉት ዶ/ር ፍስሃ፤ ይሄ የቴክኖሎጂ መተግበሪያ  ገበሬውን ከሸማቹ ጋር ያገናኘዋል ብለዋል፡፡
ሌላኛው መተግበሪያ “የከገበሬው ኮንስዩመር ብድር ማኔጅመንት” በሚል የሚታወቅ ሲሆን፤ ይህም ሸማቹ የብድር አገልግሎት የሚያገኝበት መድረክ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ሦስተኛው የቴክኖሎጂ መተግበሪያ የኢ-ለርኒንግ አስተዳደር ሥርዓት ነው ተብሏል፡፡ ከገበሬው ቴክኖሎጂ ሶሉሽን ምረቃን አስመልክቶ የተሰራጨው መረጃ እንደሚገልፀው ይህ መተግበሪያ፤ “በተለያዩ የትምህርት መስኮችና ከ77 በላይ የሚሆኑ ልዩ ልዩ የክህሎት ማበልፀጊያ ሥልጠናዎችን በበይነ መረብ አማካኝነት ባሉበት ሆነው መከታተልና አቅምን ማጎልበት የሚቻልበት ሲሆን፤ በሌላ በኩል ደግሞ በተለያየ መስክ እውቀትና ችሎታ ያላቸው ግለሰቦችም ዕውቀታቸውን የሚያጋሩበት ድረ ገፅ ነው፡፡” ከእነዚህ በተጨማሪ “የከገበሬው ቴሌቪዥን መረጃ ማሰራጫ”፣ እንዲሁም “የከገበሬው ኦርደር እና ዴሊቨሪ መቆጣጠሪያ” እና ሌሎች መተግበሪያዎች በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ ተዋውቀዋል፡፡
ኩባንያው በጥቂት ወራት ውስጥ የቴክኖሎጂ ፕላትፎርሞቹን ቁጥር 24 እንደሚያደርስ ያስታውቁት የፐርፐዝ ብላክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ፤ የኛ ዓላማ እነዚህን ፕላትፎርሞች የሁሉም የመገልገያ መድረክ ማድረግ ነው ብለዋል፡፡
TርTዝ ብላክ ኢትዮጵያ በሁለት ዓመት ውስጥ አድጎና አዋቂ ሆኖ ልጅ ለመውለድ በቅቷል ያሉት ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ፤ በቅርቡም 16 እህት ኩባንያዎችን እንደሚከፍት አስታውቀዋል፡፡
 ራዕዩ በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ተቀዳሚ የግብርና ምርት አቅራቢ መሆን እንደሆነ የሚገልፀው TርTዝ ብላክ፤ ተልዕኮው ደግሞ በኢትዮጵያ የኑሮ ውድነትን ታሪክ ማድረግ እንዲሁም ኢትዮጵያ ለሌሎች የአፍሪካ አገራትና ጥቁር ማህበረሰብ ለሚገኝባቸው አገራት የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የተነሳሽነት ምንጭና አርአያ መሆን ነው ይላል፡፡ 

”ይህን ሳያዩ ቤት እንዳይገዙ” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ አርኪ የሪል እስቴት ኤክስፖ፤ ከየካቲት 15- 17 ቀን 2016 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ  እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡ በዚህ ኤክስፖ ላይ ሪል እስቴት

አልሚዎች ቤት በማቅረብ ሲሳተፉ፣ ባንኮች ደግሞ ፋይናንስ በማቅረብ እንደሚሳተፉ አዘጋጆቹ ጠቁመዋል፡፡በኢንቴርየር ዲዛይን (ቤት የማስዋብ አገልግሎት) የተሰማሩ እንዲሁም የእንጨት ሥራ ውጤቶችን የሚያቀርቡ

ፈርኒቸር ቤቶችም በኤክስፖው ላይ እንደሚሳተፉ ታውቋል፡፡ ዘርፉ በቴክኖሎጂ እንዲታገዝም በዚህ ሥራ ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች ሌሎች የኤክስፖው ድምቀት ናቸው ተብሏል፡፡ በዚህ ኤክስፖ አቅምን ታሳቢ በማድረግ

ታላቅ ቅናሽ ያደረጉ ሪል እስቴቶችም እንደሚሳተፉ የኤክስፖው አዘጋጆች ጠቁመዋል፡፡ኤክስፖው ይህን ሁሉ በአንድ ቦታ በማካተት የቤት ፈላጊውን ራስ ምታት ያቀላል የሚሉት አዘጋጆቹ፤ ቤት መግዛት የሚፈልግ

ዋጋንና ጥራትን እንዲሁም ሌሎች መረጃዎችን ለማሰባሰብ የሚያባክነውን ጊዜና ጉልበትም ይቆጥባል ባይ ናቸው፡፡  ከ70 በላይ ድርጅቶች የሚሳተፉበትን ይሄን ኤክስፖ እስከ 10ሺ የሚደርሱ ሰዎች እንደሚጎበኙት

ይጠበቃል ብለዋል፤ አዘጋጆቹ አርኪ ኤቨንት ኦርጋናይዘር፡፡ አርኪ ኤቨንት ኦርጋናይዘር ”አርኪ ሆምስ“ ኤክስፖን ሲያዘጋጁ፣ የዘንድሮው ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑ ታውቋል፡

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ፣ መንግስት ከኢትዮጵያ ህዝብ የሃይማኖትና የባህል እሴቶች ጋር የሚፃረር ፅንሰ ሃሳቦችና ትርጓሜዎች ያላቸውን ይዘቶች ያካተተውን መንግስት ስምምነት መፈረሙን በጥብቅ

እንደሚቃወም አስታወቀ፡፡ በአውሮፓ ህብረትና በአፍሪካ፣ በካረቢያንና በፓስፊክ አገራት ለቀጣዮቹ 20 ዓመታት እንዲዘልቅ ታሳቢ ተደርጎ የተከናወነው የንግድና ኢኮኖሚ ትብብር በሚል ሽፋን የቀረበውና ሰሞኑን

የተፈረመው ስምምነት፣ ከግብረ ሰዶማዊነት መብቶች፣ ከፆታ መቀየር፣ ከውርጃና ሁሉን አቀፍ ግልሙትናዎችን ህጋዊ ማድረግ ይገኝበታል ተብሏል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም እጅግ አደገኛ ይዘት ያለው ለአህጉሪቱ ልጆችና

ታዳጊዎች ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርት አስገዳጅ ትምህርት ሆኖ እንዲሰጥ የሚያደርግ እንደሆነም ተገልጿል፡፡በኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ የበላይ ጠባቂ አባቶች ሰሞኑን የተሰጠው ይኸው መግለጫ፣

መንግሰት ከሰሞኑ የፈፀመውን ይህንኑ ስምምነት በጥብቅ እንደሚቃወሙትና እንደማይቀበሉት በመጥቀስ፣ ጉዳዩን መንግስት በአንክሮ እንዲመለከተው ጠይቀዋል፡፡


Saturday, 10 February 2024 09:49

ጥል ያጣ ጠጅ ያድላል

በፈረንሳይ አገር፤ የውበት እንብርት በምትባለው በፓሪስ በጣም ተደናቂ ከሚባሉት እይታዎች መካከል የ”ኤፍል ታወር” (የኤይፍል ሰማይ-ጠቀስ ሀውልት እንደማለት  ነው) አንዱ ነው፡፡ ይህ ልዩ ቅርፅ ያለው የብረት አፅመ - ሀውልት የተሰራው ለ1889 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) የፓሪስ ኤግዚቢሽን እንዲሆን ተብሎ ነበር፡፡ ቁመቱ 320 ሜትር ነው፡፡ ዋነኛው መሀንዲስና መሰረታዊው የዲዛይን ነዳፊ ኤይፍል ጁስታቭ (1832-1923) ይባላል፡፡ “ኤይፍል ታወር” የሚለው ስያሜ እንግዲህ ከሰውዬው ስም የመነጨ ነው ማለት ነው፡፡ አሜሪካን አገር በኒውዮርክ የሚገኘውን የነፃነት ሐውልት (Statue of Liberty) ዲዛይን የነደፈውም ይሄው መሀንዲስ ነው፡፡
የ”ኤፍል ታወር”ን ሐውልት ዲዛይን ለማውጣት መጀመሪያ በፓሪስ ያሉ ዲዛይን አውጪዎች በሙሉ እንዲወዳደሩ ማስታወቂያ ወጥቶ ነበር፡፡ ከተወዳደሩት መካከል በወቅቱ ታላቅ ነው የሚባለው አንድ ሰዓሊም ይገኝበታል፡፡ ይህ ሰዓሊ ማንም የሚበልጠኝ የለምና የማሸንፈው እኔ ነኝ ብሎ በእርግጠኝነት ኮርቶ የተቀመጠ ነበር፡፡
ውጤቱ ግን እንደጠበቀው አልሆነም፡፡ ያልገመተው ዲዛይነር አሸነፈ፡፡ ሰዓሊው በጣም ተበሳጨ፡፡ ከቤቱ መውጣት ሁሉ አስጠላው፡፡ ከቀን ቀን የኤፍል ታወር በፓሪስ ሰማይ ግዙፉን ቅርፁን ሽቅብ መዝዞ እየተንጠራራ ይታይ ጀመር፡፡ በመጨረሻም ሀውልቱ እጅግ አምሮ ከየአቅጣጫው ጎልቶ እንደሚታይ ሆኖ ቆመ፡፡
ታዲያ ሁሌ ጠዋት ጠዋት፣ ያ ተሸናፊ ሰዓሊ ከቤቱ ሲወጣ “ኤፍል ታወር” ገዝፎ ቆሞ ያየዋል፡፡ ይናደዳል፡፡ ስለዚህ አቅጣጫ ይቀይራል፡፡ ያ የብረት ኃውልት ግን ከተቀየረው አቅጣጫም ሆኖ ሲያየው በዚያም በኩል አፍጥጦ ያየዋል፡፡ በቆመበት አቅጣጫ ሁሉ የ”ኤፍል ታወር” ይታየዋል፡፡ “ይህንን ሐውልት የማላይበት የት ልድረስ?” ይላል፡፡ በድፍን ፓሪስ በተለያየ አቅጣጫ ለመዝናናት በሄደ ቁጥር “ኤፍል ታወር” ብቅ ይላል፡፡ ሰዓሊው ጨነቀው፡፡ በየትም አቅጣጫ ቢዞር ሀውልቱን ያየዋል፡፡ ስለሆነም የመሸነፍ ህመሙን ያስታውሰዋል፡፡ ለህሊናው ሁከት ይሆንበታል፡፡ ቡና እንኳን ለመጠጣት ወጥቶ የ”ኤፍል ታወር”ን ሳያይ ቡና ቤት መቀመጥ አልቻለም፡፡
አንድ ቀን አንድ ሀሳብ መጣለት፡፡ “ለምን ከሰማይ - ጠቀሱ ሀውልት ስር ያለው ካፌ ሄጄ ቡና አልጠጣም?” አለ፡፡ ፈጥኖ ወደዚያች ካፌ ሄደ፡፡ ቡናውን አዝዞ እየጠጣ ሳለ፣ በሁሉም አቅጣጫ ቢመለከት የ”ኤፍል ታወር” ጨርሶ የለም፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ እፎይ ብሎ ደስ እያለው ቡናውን ጠጣ! እነሆ በመጨረሻ ከጠላው እውነት ሥር መቀመጡ የተሻለ ሆኖ አገኘው፡፡
***
መሸነፍን አለመቀበል ለህሊና ውጋት ይዳርጋል፡፡ አንድ ወቅት ትልቅ ነበርኩና የሚበልጠኝ አይፈጠርም ብሎ ማሰብም ከፍተኛ ችግር ላይ ይጥላል፡፡ ያፈጠጠውን እውነት አልቀበልም ማለትና ከእውነት ለመሸሽ መሞከር፤ መከራ ማየትን ያስከትላል፡፡ ላያመልጡ ነገር ቁም-ስቅል ማየትን ያመጣል!
በተደጋጋሚ የሚሰሩ ስህተቶች ከአንዴ ከሁለቴ በላይ እርምት ይደረግባቸዋል ተብሎ ተመልሰው እዚያው የሚገኙ ከሆነ ወይ ከአራሚ፤ ወይ ከታራሚው፣ አሊያም ከስርዓቱ አንዳች መሰረታዊ ጉድለት አለ ማለት ነው፡፡ ይሄን ያልመረመረ እስከ ፍፃሜ ውድቀቱ ድረስ ከችግር ወደ ችግር ሲሸጋገር እንዲኖር ይገደዳል፡፡ ዕጣ-ፈንታው የሽግግር ዘመን ብቻ ይሆናል፡፡ አንዳንድ የሹመት ወንበሮች በተደጋጋሚ ሰው ተመድቦባቸው በተደጋጋሚ ፈጣን ሽረት ይደርስባቸዋል፡፡ ወንበሮቹም የሽግግር ወንበር ይመስላሉ ለማለት ይቻላል፡፡ ለመፍትሄው ሌላ ሰው የመመደብን ችግር እንጂ የአሰራሩን አሊያም የስርዓቱን እንከን የማየት ባህል ገና አልተለመደም፡፡ ይሄ የግድ መለመድ አለበት፡፡
ስብሰባ በተባለ ቁጥር “የመኖር ወይም አለመኖር” ጥያቄ የሚደቀንባቸው አያሌ ሹማምንት ናቸው! እንደ እውነቱ ከሆነ ለጊዜው ነው እንጂ እውነቱ የታወቀ እለት እርቃን መቅረት አለ- “የአይጥ ጧፍ ድመት ሲገባ ይጠፋል” ነዋ ነገሩ!
አንዳንዱ የራሱ ሳያንስ የሩቅና የቅርብ የስጋም፣ የድርጅትም ዘመዶቹን በዙሪያው ሰብስቦ ሌላ የሙስና፣ የኢ-ዲሞክራሲያዊነት፣ የኢ-ፍትሀዊነት፣ የአስተዳደር ደካማነት ማዕከል ለመፍጠር የሚውተረተር ይመስላል፡፡ እንዲህ መሰሉን ጉልበተኛ ተጠልሎ በማን አለብኝነት ዘራፍ ሲል ይውላል፡፡ “የጠገበ ሌባ ቃጭል ያንጠለጥላል” እንዲሉ ቀኑ ደርሶ “ከተከበረ” መንበሩ እስኪወርድ በአደባባይ ግነን በሉኝ ማለት የሙጥኝ ይላል፡፡ የማታ ማታ ከነዘመድ አዝማዱ የወረደ እለት ጉዳዮች ሁሉ ወደ መጀመሪያው እርከን ይመለሳሉ፡፡ (Back to Square one) ነገራችን ሁሉ የእንቧይ ካብ የእንቧይ ካብ ማለት እንግዲህ ይሄ ነው፡፡ሌላም ብርቱ ችግር አለ፡፡ እንደ ቅዱስ መፅሐፍ ቃል የሚደረደሩ ቃላት የስብሰባ አሸንክታብ ሆነው እንዳይቀሩ ልብ ብሎ ማየት ያስፈልጋል፡፡ የተሳሳተ የእድገት ስዕል ይሰጣልና መጠንቀቅ ይበጃል፡፡ ጧት ማታ የሚነበነቡት ቃላት የወረት ፀሎት እንዳይሆኑ ተግባራዊነታቸውን ማጤን ያስፈልጋል፡፡ አለበለዚያ የገዛ ራስን ጥላ እስከመሸሽ፣ ደረቁን እውነት የማላይበት የት ልድረስ እስከማለት የደረሰ ጥፋት ውስጥ መዘፈቅ ይከተላል፡፡ በየቢሮው ስብሰባ ተካፍሎ መመለስ፣ ልዩ ማዕረግ ያስገኘላቸው የሚያስመስሉ አያሌ አለቆች አሉ፡፡ የስብሰባዎቹን ቃላት መደጋገምን እንደ እውቀት መለኪያ መውሰድም እጅግ አደገኛ ህፀፅ አለው፡፡ መተግበር ዋና ነገር ነው፡፡ እንዴት መተግበር እንዳለበት ማውጠንጠንም ቁልፍ ጉዳይ ነው፡፡ በተከታታይ በታዩ ኢትዮጵያዊ ለውጦች ውስጥ ሁሉ የቃል-ጥናት ዋና መሳሪያ ሆኖ ታይቷል፡፡ የካድሬ ደቀ - መዛሙርትና የቢሮ ንቃት-ሃዋርያት ድግምት እስኪመስሉ ድረስ እንዲያንገፈግፉ መደረጋቸው አሌ አይባልም፡፡  የቢሮክራሲው ቁንጮ ቢሮክራሲውን እየረገመ ለሌላ አገር ቢሮክራሲ የቆመ ያስመስላል፡፡ አንዳንዴ ከናካቴው የሚወቀስ የጠፋበት ጊዜም ይፈጠራል፡፡ ነብሱን ይማረውና ሌኒን “ጠላቶቻችን ቋንቋችንን ወስደውብናል፣ ቅያሬ ቋንቋ ሊኖረን ይገባል” ያለው እንዲሁ ተቸግሮ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ዛሬም ያንኑ ፈለግ የያዘ ይመስላል፡፡
የሚገርመው ግን ዋናው ትኩረት የሚደረገው የወቅቱ አንገብጋቢ ጉዳዮች ማለትም-የማያቋርጠው ድርቅ ላይ፣ የተፈጥሮአዊና ሰው ሰራሽ ጥፋቶች ላይ፣ ዞሮ-ገጠም የዕዳ ጣጣ ላይ፣ ስራ አጥነት፣ በሽታና ርሀብ ላይ አይደለም፡፡ ወደፊት እነሱን የሚፈቱ የሚመስሉ ነባቤያዊ ልፈፋዎች (theoretical rhetorics) የጥንትና ያሁኖቹ፣ የሩቅ ያሁኖችና የቅርብ ያሁኖች፣ ያደባባይ ቃላት ሽመናዎች (coinages) አስገራሚ ነው፡፡ አንዱ “ሂስና ግለሂስ” ሲል ሌላው “ግምገማ፤” አንዱ “ኅብረት” ሲል፣ ሌላው “ውህደት”፣ አንዱ “ግንባር” ሲል ሌላው “ቅንጅት” ወዘተ… መድብለ ፓርቲና የብዙሃን ፓርቲ፣ ኮንፈረንስና ጉባዔ፣ ውጤት - ተኮርና አመርቂ ውጤት፣ ዕሳቤና ግንዛቤ፣ አንጃና ውሁዳን፣ ማንቃትና ማስረጽ፣ በመዋቅር ማውረድና መመደብ፣ ሰብሳቢና ጠርናፊ፣ ምዝበራና ሙስና፣ ታክቲክና ስትራቴጂ፣ ሚሽንና ቪዥን፣ ፓርቲሲፔሽንና ህብረ-ሱታፌ፣… እነዚህን መሰል ቃላት እንደየአመራሩ ይፈበረካሉ፣ ይፈለፈላሉ፡፡ መረሳት የሌለበት ግን ይሄን ሁሉ ለመረዳት የሚችልና በተግባርም ማራመድ ያለበት ህዝብ ወሳኝ መሆኑን ነው፡፡ ህዝብ ያልተረዳው ነገር የፖለቲከኞች መሻኮቻ እንጂ መሬት - የያዘ (terre a terre) እና ረብ-ያለው ጉዳይ አይሆንም፡፡ የፒራሚዱ አናት ላይ ያሉ ኅሩያን ህዳጣን (ጥቂቶች ምርጦች) ብቻ ለውጥን የትም አያራምዱትም፡፡
እያንዳንዱ ድርጅት ወይም ፓርቲ በህዝብ አኗኗርና በሀገር እድገት ላይ ምን ያስከትላል ሳይል “ወቅታዊው መፈክር ያታግላል አያታግልም”፣ “ሀሳቡ ባይተገበርም ሰውን ካነጋገረ ተሳትፎን ያጎለብት የለም ወይ?” “በጉዳዩ ላይ አባላት ይተጋገላሉ አይተጋገሉም፣…” በሚል አይነት የራስን መንገድ ብቻ ባማከለ አካሄድ መጓዝ፣ ዞሮ ዞሮ ለግራ-መጋባትና ለአተካሮ ሊዳርግ፣ ኋላም ጥላቻን ሊፈጥር እንደሚችል መገንዘብ ከብዙ ውዝግብ ያድናል፡፡ አለበለዚያ ግን “ጥል ያጣ ጠጅ ያድላል” እንደተባለው ወቅታዊ አቧራ በማስነሳት ብቻ ላያቆም ይችላልና መጠንቀቅ ደግ ነው!! እንደ ሰዓሊው እውነቱ ስር ለመደበቅም ቢሆን ጊዜው መርፈድ እንደሌለበት አለመዘንጋት ነው!

የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ታሪክ ተመራማሪው የታሪክ ምሁሩ እና በቅርቡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለመጀመሪያ ጊዜ ያሳተመው''  የዘመናዊት ኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት እና ዲፕሎማሲ ከ1900-2015 ዓ.ም.'' መጽሐፍ ላይ አስተያየት በመስጠት ሞያዊ ድጋፍ ያበረከቱት ዶ/ር በለጠ በላቸው በሳይንስ ሙዚየም በመገኘት የዲፕሎማሲ ሳምንት አውደ ርዕይን ጎብኝተዋል።



የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ለሀገር አቀፍና ክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባና የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት መስጠቱን አስታወቀ።
ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምዝገባና የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት የሰጠው ለወሎ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲና ለብሔራዊ ባይቶ ዓባይ ትግራይ ለተሰኙ ሀገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዲሁም ለኩሽ ህዝቦች ብሔራዊ ንቅናቄ ለተሰኘ ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገጹ ያሰፈረው መረጃ ያመለክታል።
ቦርዱ ጥር 21 ቀን 2016 ዓ.ም ያከናወነው የምዝገባና የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ በኢትዮጵያ የምርጫ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011  በተሰጠው ሥልጣን መሠረት መሆኑ ተገልጿል።

Page 8 of 695