Administrator

Administrator

በቅርቡ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ረቂቁ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ፣ ለሕዝብ ቀርቦ ዜጎች ውይይት እንዲያደርጉበትና  እንዲተች  የሚጠይቅ ምክረሃሳብ ለፍትህ ሚኒስቴር ቀረበ ። ”ስብስብ ለሰብዓዊ  መብቶች በኢትዮጵያ“  የተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት፣ ከሌሎች በሰብዓዊ መብቶች ላይ ከሚሠሩ አገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር በመተባበር፣ ለረቂቅ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲው  ግብዓት የሚኾኑ ሀሳቦችን የያዘ የምክር ሀሳብ ሰነድ ለፍትህ ሚኒስቴር በጽሁፍ አቅርቧል።
ይኸው ለፍትህ ሚኒስቴር የቀረበው የምክር ሃሳብ ሰነዱ፣ በቅርቡ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው  ረቂቅ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ፣ ለሕዝብ ቀርቦ እንዲተችና ሕዝቡ በጉዳዩ ላይ ሃሣብ እንዲሰጥበት የሚጠይቅ ሲሆን፤  ከሽግግር ፍትህ ፖሊሲው ትግበራ  አስቀድሞ    መንግሥት  በተለያዩ የአገሪቱ  አካባቢዎች በመካሄድ ላይ የሚገኙ  ግጭቶችን  ማስቆም እንዳለበት  እንዲሁም  በፖሊሲው ሂደት አግባብነት ያላቸው ተቋማት ሚና  መካተት እንዳለበት ይጠቁማል፡፡
 በተጨማሪም ሰነዱ የፖሊሲው የተፈጻሚነት ውሰን፣ በሰሜኑ ጦርነት ከባድ ወንጀሎችን የፈጸሙ የኤርትራ ወታደሮችን በልዩ ፍርድ ቤት ማየትን ጭምር እንዲያካትት የሚጠይቁና ሌሎች ምክረ ሃሳቦችንም ይዟል፡፡ ድርጅቱ፤ ከሌሎች በሰብዓዊ መብቶች ላይ ከሚሰሩ ተቋማት ጋር በመተባበር ለፍትህ ሚኒስቴር ባቀረበው ምክረ ሃሣብ፣ ረቂቁ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ፣ በምክር ቤቱ ከመፅደቁ በፊት ለህዝብ ውይይት ሊቀርብ እንደሚገባው  ጠቁሟል፡፡



አገኘሁ_አዳነ_ድልነሣሁ-


በቤልጅዬም የኢትዮጵያ ኤምባሲ፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለ_የሥነጥበብና_ዲዛይን_ት_ቤት ጋር በመተባበር በቤልጅዬም ከየካቲት 18 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሥዕል ትርዒት አቅርበዋል። ይህ ኤግዚቢሽን መልኩና ፈርጁ ብዙ የሆነውን የዲፕሎማሲ ዓለም በሥነጥበብና ባህል ለማዋዛት፣ ነባሩ የሥነ ጥበብ ብሂል በዘመነኛው የሥነ ሥዕል እንቅስቃሴ ላይ ያሳደረውን ክንደ ብርቱ ተፅዕኖ ለማመላከትና ት/ቤቱ ከቀረው ዓለም አቻ ተቋማት ጋር ትስስር መፍጠር እንዲችል ታስቦ የተሰናዳ ነበር።  በትርዒቱ መክፈቻ የአውሮፓ ኅብረት የውጭ ግንኙነት  ቢሮ ዋና ፀሐፊ ስቴፋኖ ሳኒኖ (Stefano Sannino)፣ የቤልጂየም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተወካይ፣ አምባሳደር  ባርት ዴ ግሩፍ፣ የአካፓድ ምክትል ዋና ፀሐፊ ዶ/ር ኖርበርት ሪቻርድ ኢብራሂም፣ በብራስልስ የሚገኙ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት የተገኙ ሲሆን፣ የሥነ ጥበብ ልሂቃንና የሥነ ጥበብ አፍቃርያን ታድመውበታል።
በቤልጅዬም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባለሙሉ ስልጣን እንደራሴ አምባሳደር ሒሩት ዘመነ፣ አምባሳደር ሞላልኝ አስፋው እና የሥራ ጓዶቻቸው ዝግጅቱ የተሳካ ይሆን ዘንድ የሚያስመካ ጥረት አድርገዋል። ጥረቱ ፍሬ አፍርቶም በቤልጅዬም የሚገኙ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ፣ የታሪክ፣ የሂስ እና የሥነጥበብ ንድፈ ሐሳብ ልሂቃን በኤምባሲው እንዲሰበሰቡ ሆነዋል።
የአንትወርፕን (Antwerpen) Royal Academy of the Arts መምህራንም በኤምባሲው ተገኝተው ፍሬ ያለው ውይይት ማድረግ ችለናል። ምሑራኑ ትርዒቱን ተመልከተው መደነቃቸውን የገለጹልን ሲሆን፣  በምንተባበርባቸው ተቋማዊ የጋራ ጉዳዮች ላይ መክረናል።  
የቀረበው የሥዕል ትርዒት ተወዳጅነቱ ከፍ በማለቱ ምክንያት ለተጨማሪ አንድ ሳምንት የተራዘመ ሲሆን፣ ለአካባቢው ማኅበረሰብ መነቃቃት መፍጠሩን በዝግጅቱ አካል የሆንነው ሙያተኞች መታዘባችንን እንመሰክራለን።
ሀገራችን ኢትዮጵያ ከሌላው ዓለም ጋር የምትነጋገርበትን የቋንቋ አማራጭ ለማስፋት ሥነጥበብን ወደ ዲፕሎማሲው ዓለም የጋበዙትን አምባሳደር ሒሩት ዘመነን፣ አምባሳደር ሞላልኝ አስፋውንና የሥራ ጓዶቻቸውን  ማመስገን ይገባል።

አገኘሁ_አዳነ_ድልነሣሁ-


በቤልጅዬም የኢትዮጵያ ኤምባሲ፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለ_የሥነጥበብና_ዲዛይን_ት_ቤት ጋር በመተባበር በቤልጅዬም ከየካቲት 18 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሥዕል ትርዒት አቅርበዋል። ይህ ኤግዚቢሽን መልኩና ፈርጁ ብዙ የሆነውን የዲፕሎማሲ ዓለም በሥነጥበብና ባህል ለማዋዛት፣ ነባሩ የሥነ ጥበብ ብሂል በዘመነኛው የሥነ ሥዕል እንቅስቃሴ ላይ ያሳደረውን ክንደ ብርቱ ተፅዕኖ ለማመላከትና ት/ቤቱ ከቀረው ዓለም አቻ ተቋማት ጋር ትስስር መፍጠር እንዲችል ታስቦ የተሰናዳ ነበር።  በትርዒቱ መክፈቻ የአውሮፓ ኅብረት የውጭ ግንኙነት  ቢሮ ዋና ፀሐፊ ስቴፋኖ ሳኒኖ (Stefano Sannino)፣ የቤልጂየም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተወካይ፣ አምባሳደር  ባርት ዴ ግሩፍ፣ የአካፓድ ምክትል ዋና ፀሐፊ ዶ/ር ኖርበርት ሪቻርድ ኢብራሂም፣ በብራስልስ የሚገኙ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት የተገኙ ሲሆን፣ የሥነ ጥበብ ልሂቃንና የሥነ ጥበብ አፍቃርያን ታድመውበታል።
በቤልጅዬም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባለሙሉ ስልጣን እንደራሴ አምባሳደር ሒሩት ዘመነ፣ አምባሳደር ሞላልኝ አስፋው እና የሥራ ጓዶቻቸው ዝግጅቱ የተሳካ ይሆን ዘንድ የሚያስመካ ጥረት አድርገዋል። ጥረቱ ፍሬ አፍርቶም በቤልጅዬም የሚገኙ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ፣ የታሪክ፣ የሂስ እና የሥነጥበብ ንድፈ ሐሳብ ልሂቃን በኤምባሲው እንዲሰበሰቡ ሆነዋል።
የአንትወርፕን (Antwerpen) Royal Academy of the Arts መምህራንም በኤምባሲው ተገኝተው ፍሬ ያለው ውይይት ማድረግ ችለናል። ምሑራኑ ትርዒቱን ተመልከተው መደነቃቸውን የገለጹልን ሲሆን፣  በምንተባበርባቸው ተቋማዊ የጋራ ጉዳዮች ላይ መክረናል።  
የቀረበው የሥዕል ትርዒት ተወዳጅነቱ ከፍ በማለቱ ምክንያት ለተጨማሪ አንድ ሳምንት የተራዘመ ሲሆን፣ ለአካባቢው ማኅበረሰብ መነቃቃት መፍጠሩን በዝግጅቱ አካል የሆንነው ሙያተኞች መታዘባችንን እንመሰክራለን።
ሀገራችን ኢትዮጵያ ከሌላው ዓለም ጋር የምትነጋገርበትን የቋንቋ አማራጭ ለማስፋት ሥነጥበብን ወደ ዲፕሎማሲው ዓለም የጋበዙትን አምባሳደር ሒሩት ዘመነን፣ አምባሳደር ሞላልኝ አስፋውንና የሥራ ጓዶቻቸውን  ማመስገን ይገባል።

ዳሸን ባንክ ሸሪክ የተሰኘ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት የጀመረበትን 6ኛ ዓመት ባከበረበት ዕለት ከደንበኞች በበጎ አደራጎት ፈንድ በአደራ የሰበሰበውን 12.5 ሚሊዮን ብር ለ18 አገር በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ለገሰ፡፡  

ዳሸን ባንክ በሚሰጠዉ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ብቻ አሁን ላይ ከ1 ሚሊየን በላይ ደንበኞችን ማፍራት የቻለ ሲሆን፤ይህንንም በተለያዩ ስነ-ስርዓቶች አክብሯል፡፡

የዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ዓለሙ በስነ-ስርዓቱ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ ለባንኩ አመኔታቸውን ለሰጡ ደንበኞች ከፍ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበው፣ ወደፊትም ለላቀ ስኬት የሸሪዓህ መርህን በመከተል አዳዲስ የባንክ አገልግሎቶቸን እንደሚያቀርብ ገልፀዋል፡፡

አቶ አስፋው አክለውም፤ በአደራ የተሰጣቸውን ገንዘብ የተረከቡ 18 አገር በቀል በጎ አድራጎት ድርጅቶች የማህበረሰቡን ችግር ለመቅረፍ በሚያስችሉ ስራዎች ላይ እንዲያውሉት አደራ ብለዋል፡፡ በቀጣይም ባንኩ እነኚህንም ሆነ መሰል ሌሎች ተቋማትን የማህበረሰቡን ችግሮች በዘላቂነት በሚፈቱ ስራዎች ላይ በጋራ ለመስራት የሚሻ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ዳሸን ባንክ፤ የካቲት 26 ቀን 2010 ዓ.ም በአንድ መስኮት መስጠት የጀመረው አገልግሎት አድጎ ዛሬ ላይ ከ70 በላይ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በሚሰጡ ቅርንጫፎች እንዲሁም ከ800 በላይ በሆኑ ቅርንጫፎች ደግሞ በመስኮት ለደንበኞቹ የተሟላ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ ከደንበኞቹም ከ9.5 ቢሊየን ብር በላይ ማሰባሰብ የቻለ ሲሆን፤ ከዚህም ውስጥ ከ6 ቢሊየን ብር በላይ በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ ለተሰማሩ ደንበኞቹ ፋይናንስ አድርጓል፡፡

ባንኩ ከወለድ-ነፃ የባንክ አገልግሎት የሚጠይቀውን ሙያዊና ሸሪዓዊ ስነ-ምግባር ተግባራዊ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ በዚህም ረገድ እ.ኤ.አ ህዳር 28 ቀን 2023 በባህሬን ማናማ በተካሄደው 9ኛው የኢስላሚክ ሪቴል ባንክ ሽልማት ላይ ጠንካራው ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በኢትዮጵያ የሚሰጥ ባንክ (The strongest Islamik Retail Banking Window in Ethiopia 2025) በሚል ተቀማጭነቱ ሎንዶን በሚገኘውና  በፋይናንስ ዘርፍ ጥናትና ምርምር በሚሰራዉ  ኬምብሪጅ አይ ኤፍ ኤ(Cambridge IFA) የተሰኘ ተቋም ሽልማት አግኝቷል፡፡ ባንኩን ለዚህ ሽልማት ካበቁት መሰፈርቶች አንዱ  ጠንካራ የሸሪዓህ አስተዳደር ማዕቀፍ በመተግበሩ ነው፡፡

ባንኩ በአለም አቀፍ ደረጃ የእስላማዊ ፋይናንስ ተቋማትን የሂሳብ፣ ኦዲትና ሸሪዓህ መስፈርቶችን የሚያወጣው ተቋም (AAOIFI) ቋሚ አባል የሆነ፣ በኢትዮጳያ ብቸኛው የፋይናንስ ተቋም መሆኑ ይታወቃል፡፡

በሙዚቃው ኢንዱስትሪ ውስጥ ከሚገኙ አለም አቀፍ ተቋማት ጋር  በጋራ እየሰራ የሚገኘው ሰዋሰው መልቲሚዲያ፣ በትውልደ ኢትዮጵያውያን በተመሰረተውና በተለያዩ የአሜሪካን ግዛቶች በስፋት በዲጂታል ማስታወቂያው ዘርፍ ላይ እየሰራ ከሚገኘው አድ ቴክ ሶሉሽን ጋር  በጋራ ለመስራት በዛሬው ዕለት ከስምምነት ላይ ደረሱ፡፡

የዛሬው ስምምነት ኢትዮጵያውያን አርቲስቶችን ወደ ዓለም አቀፉ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ እንዲሁም በሙዚቃው ዘርፍ የተሰማሩ ግዙፍ አለም አቀፍ ተቋማትን ደግሞ ወደ ሀገራችን የኪነ-ጥበብ ዘርፍ ለማስገባት አልሞ ለሚሰራው  ሰዋሰው መልቲሚዲያ ወሳኝ ምዕራፍ ነው ተብሏል፡፡

በተለያዩ የአሜሪካን ግዛቶች በኢትዮጵያውያን በሚዘጋጁ ትልልቅ ፕሮግራሞች፣ በአብዛኞቹ የሀገሪቱ ግዛቶች በሚገኙ ሞሎች፣ አደባባዮች፣ ሆቴሎችና በርካታ ሰዎች በሚሰበሰቡባቸው ጎዳናዎች ላይ የዲጂታል ማስታወቂያ ስራን የሚሰራው አድ ቴክ ሶሉሽን፣ በሰዋሰው በኩል የሚወጡ አልበሞችን፣ የተለያዩ አርቲስቶችን ስራዎች እንዲሁም ከሰዋሰው ጋር በጋራ የሚሰሩ ተቋማትን አገልግሎቶች የሚያስተዋውቅ ይሆናል፡፡

የሰዋሰው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሀብቱ ነጋሽ፤ በመላው አለም የሰዋሰው አርቲስቶችንና ስራዎችን ለማስተዋወቅና ለማስፋፋት ከምናደርጋቸው ስራዎች መካከል ይህ አንደኛው መሆኑን ጠቅሰው፣ በስምምነቱም ደስተኛ መሆናቸውን ገልፃዋል፡፡

በኢትዮጵያ የአድ ቴክ ሶሉሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አማኑኤል ኪዳኔ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያን የሙዚቃ ኢንዱስትሪ በተለየ መልክ ለማሻሻልና ለመለወጥ ከሚሰራው ሰዋሰው ጋር በጋራ ለመስራት በመስማማታችን ከፍተኛ ደስታ ተሰምቶናል ብለዋል፡፡

ሁለቱ ድርጅቶች በቀጣይ በአውሮፓ የተለያዩ ሀገራት በጋራ የመስራት ውጥን እንዳላቸውም ተጠቁሟል፡፡

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ፕሮጀክት አፈፃፀም 95 በመቶ መድረሱን የሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ገለጸ።

ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤቱ  በዛሬው ዕለት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተነገረው፤ የሲቪል ሥራው 98 በመቶ እንዲሁም የኤሌክትሮሜካኒካል ሥራው 78 በመቶ ደርሷል፡፡

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታው አሁን ላይ 95 በመቶ የደረሰ ሲሆን፤ ሀይል የማመንጨት ምዕራፍ ላይም ይገኛል።

መላ የኢትዮጵያ ህዝብ ካለው ላይ በማዋጣት ግድቡን  ለዚህ እንዳደረሰው ያመለከተው ጽ/ቤቱ፤ በ13 አመታት ውስጥም ከ18.9 ቢሊዮን ብር በላይ ማሰባሰብ ተችሏል ብሏል።
 
ግድቡ አሁንም ከፍጻሜው እስኪደርስ ህዝቡ የሚያደርገውን ርብርብ እንዲያጠናከር ጽ/ቤቱ ጥሪ ቀርቧል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ  የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ ግድብ የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠበትን 13ኛ ዓመት በተለያዩ ዝግጅቶች ለማክበር መዘጋጀቱን የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡


   የቴሌግራም ቻናልችንን  በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

• ቅዱሳት መጻሕፍት በቅናሽ ዋጋ ለምእመናን ይቀርባሉ ተብሏል
“መጽሐፍ ቅዱሳዊ እሴቶችን በሕዝባችን ሕይወት እናሥርጽ!” በሚል መሪ ቃል፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ሳምንትና የቅዱሳት መጻሕፍት ዐውደ ርዕይ ከመጋቢት 16 እስከ መጋቢት 21 ቀን 2016 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡
የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኀበር በዛሬው ዕለት ጠዋት በስካይ ላይት ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፤ የመጽሐፍ ቅዱስ ሳምንት ለአምስት ቀናት እንደሚካሄድ አስታውቋል።
በዚህ መርሐ ግብር ላይ የኢትዮጵያ አርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ፣ የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ፣ ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ተቋማትና በርካታ ቁጥር ያላቸው ምእመናን በስፋት እንደሚሳተፉበት ተነግሯል፡፡
98 ዓመት እድሜ ያስቆጠረው የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኀበር ሰብሳቢ ዶ/ር ተስፋጽዮን ደለለው እንደገለጹት፤ ማኀበሩ 22 በሚደርሱ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች መጽሐፍ ቅዱስ በማስተርጎም ላይ ሲሆን በቀጣይ ከ20 በላይ በሚደርሱ ተጨማሪ ቋንቋዎች አስተርጉሞ ለማቅረብ በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በአውደ ርዕዩ ላይ ቅዱሳት መጻሕፍት በቅናሽ ዋጋ ለምእመናን እንደሚቀርቡ የተገለጸ ሲሆን፤ ምዕመናን በተጠቀሱት ቀናት ያለምንም ክፍያ ወደ ስካይ ላይት ሆቴል በመምጣት በስጋም በነፍስም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማህበሩ ጥሪ አቅርቧል።
በመርሐ ግብሩ ማጠናቀቂያ መጋቢት 21 ቀን 2016 ዓ.ም የመጽሐፍ ቅዱስ ቀን በሚል የእውቅና እና የምስጋና ፕሮግራም መዘጋጀቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡

   የቴሌግራም ቻናልችንን  በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህል ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ዘንድሮ ባዘጋጀው የ"ዝክረ ኪነጥበብ" መርሃ ግብር፣ የበርካታ ቴአትሮች ደራሲ የሆነው ፀሐፌ ተውኔት ውድነህ ክፍሌ የክብር ዲፕሎማና እውቅና ዛሬ የካቲት 26 ቀን 2016 ዓ.ም በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተበርክቶለታል።

ጸሃፌ ተውኔት ውድነህ ክፍሌ፤  ግማሽ ጨረቃ፣ የደፈረሱ አይኖች፣ ባቢሎን በሳሎን ፣ ቅጥልጥል ኮከቦች፣ የሌሊት ሙሽሮች፣ ንጋት ፣ የሌሊት ጧፍ፣ ሦስቱ ሰዎች፣ የቼዝ አለም ፣ ቤርሙዳ እና ሌሎች የመድረክና የስክሪን ድራማዎች ደራሲ መሆኑ ይታወቃል፡፡

በእውቅናው ሥነሥርዓት ላይም በፀሐፌ ተውኔት ውድነህ ክፍሌ ላይ የሚያጠነጥን  ዘጋቢ ፊልም፣ በተውኔቶቹ ላይ የባለሞያ ዳሰሳና ከ“የደፈረሱ ዓይኖች” ቴአትር ላይ ቅንጫቢ ተውኔት ቀርቧል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህል ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ በየዓመቱ በሚያዘጋጀው "ዝክረ ኪነጥበብ" ልዩ መርሃ ግብር፣ ለሀገራቸው ኪነጥበብ በሙያቸው የላቀ አስተዋጽኦ ካበረከቱ ጠቢባን  አንዱን በመምረጥ የክብር ዲፕሎማና እውቅና ሲሰጥ ቆይቷል::

በቢጂአይ ኢትዮጵያ እና በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ መካከል ሲካሄድ የቆየው ሜክሲኮ የሚገኘው የቢጂአይ ኢትዮጵያ ዋና መሥሪያ ቤት ህንፃ ሽያጭ ድርድር፣ ውል ለማሰር ባለመቻሉ ሂደቱ መቋረጡ ተገልጧል፡፡

ቢጂአይ ኢትዮጵያ ትላንት ባሰራጨው መግለጫ፣  የሽያጩ ውል የተቋረጠው ፤ በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ  በኩል ግብይቱን ለማጠናቀቅና የሽያጭ ውሉን ለመፈረም ፍላጎትና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ነው፤ ብሏል።

ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ግን በዚህ አይስማማም፡፡ ኩባንያው ዛሬ ጠዋት ሠንጋ ተራ በሚገኘው የዋና መ/ቤቱ አዳራሽ በሰጠው መግለጫ፤ ”ቢጂአይ ኢትዮጵያ የመንግሥት ግዴታዎችን ባለመወጣቱ በውልና ማስረጃ ለመፈራረም አልተቻለም“ ብሏል፡፡

ለቢጂአይ 1ቢ. 150 ሚሊዮን ብር ክፍያ መፈጸሙን ያስታወሰው ፐርፐዝ ብላክ፤ ቀሪውን ክፍያ በህጉ መሰረት  በውልና ማስረጃ ስንፈራረም ለመክፈል ዝግጁ ነን ብሏል፡፡

”ከታክስ ነጻ የሆኑበት ወረቀት ከቀረበ በውልና ማስረጃ እንፈራረማለን፤ እኛ ተገቢውን ሰነድ ካሟሉ በሁለተኛው ዙር የሚጠበቅብንን 2.5 ቢሊዮን ብር ለመክፈል ዝግጁ ነን፡፡“ ብሏል፤ ፐርፐዝ ብላክ በሰጠው መግለጫ፡፡

ቢጂአይ ኢትዮጵያ የታክስ ክሊራንስ አቅርቦ በውልና ማስረጃ የማይፈራረም ከሆነ ግን ጉዳዩን ወደ ፍ/ቤት ለመውሰድ እንገደዳለን ብሏል - ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ፡፡

ቢጂአይ እና ፐርፐዝ ብላክ ሜክሲኮ የሚገኘውን የቢጂአይ ኢትዮጵያ ዋና መ/ቤት ህንጻ ለመገበያየት የተዋዋሉት በ5 ቢሊዮን ብር ሲሆን፤ 1 ቢሊዮን ብር የቅድምያ ክፍያ መፈጸሙ ታውቋል፡፡ ከፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ የሚጠበቀው ሁለተኛ ክፍያ 2.5 ቢሊዮን ብር ሲሆን፤ ይህ ክፍያ የሚፈጸመው በውልና ማስረጃ ስንፈራረም ነው ብሏል - ፐርፐዝ ብላክ በመግለጫው፡፡

የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ መሥራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ ለሥራ ጉዳይ በአሜሪካ እንደሚገኙና ከነገ ወዲያ ሐሙስ እንደሚመለሱ የተጠቆመ ሲሆን፤ አርብ ጠዋት በጉዳዩ ዙሪያ ዝርዝር መግለጫ ይሰጣሉ ተብሏል፡፡

ዝግጅት ክፍሉ በሁለቱም ወገን ያለውን ዝርዝር ጉዳይ እየተከታተለ ያደርሳችኋል፡፡

እየተገለማመጠ ሀኪሙን ተጠጋው። እምባ ያቆሩ አይኖቹን ጨመቅ፣ጨመቅ እያደረገ ወደ ጆሮው ጠጋ አለና፤ “ዶክተር የማሳክምበት አቅሙ የለኝም። እሱም አይድንም። ለስቃይና ለጭንቀት ከምንዳረግ እባክህ ሞቱን አፍጥንልኝ! ግደልልኝ!”
ዶክተሩ ጭንቅላቱን የተመታ ያህል ክው ብሎ በቆመበት ደርቆ ቀረ።
***
(ው.ክ)
ማስታወሻ፦ አንድ የህክምና ዶክተር የገጠመውን ከነገረኝ ተነስቼ ነው።

Page 3 of 695