Administrator

Administrator

የ2026 የሴቶች ከ17 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ሁለተኛ ዙር የመልስ ጨዋታውን ከካሜሩን አቻው ጋር ያደረገው የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን 1 ለ 0 ተሸንፏል።

የካሜሩንን የማሸነፊያ ብቸኛ ግብ ታዛኑ አንጌ በ12ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፋለች።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በጨዋታው ከካሜሩን የተሻለ እንቅስቃሴ በማሳየት ብልጫ ቢወስድም ያገኛቸውን ዕድሎች ባለመጠቀሙ ለሽንፈት ተዳርጓል ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በደርሶ መልስ ጨዋታ በአጠቃላይ 6ለ2 በመሸነፍ ማጣሪያውን ሳያልፍ ቀርቷል።

ከዕለታት አንድ ቀን አያ ጅቦ አራት ልጆቹን ማለትም መዝሩጥን፣ ማንሾለላን፣ ድብልብልንና ጣፈጦን ይዞ በሌሊት መንገድ ይሄዳሉ፡፡ እየተጓዙ ሳለ ድንገት ከቤቷ የወጣች አህያ ያገኛሉ፡፡
ይሄኔ አባት ጅብ፤
“ልጆቼ ሆይ! እንግዲህ እኔ በጣም አርጅቻለሁና፣ ይቺን አህያ እኔ ነኝ የምበላት! እናንተ ራቅ ራቅ ብላችሁ ትጠብቁኛላችሁ” አለ፡፡
ይኔ መዝሩጥ፤
“አባዬ ኧረ አንድ ብልት እንኳን አጋራን?” ይለዋል፡፡
“አይሆንም! ምንም አላቀምስህም” ይላል አባት፡፡
ይሄኔ ማንሾለላ ይነሳና፤
“ለእኔስ አባቴ?” ይላል፡፡
አያ ጅቦም፤ “እንካ ጆሮዋን ብላው” ይለዋል፡፡
ቀጥሎ ድብልብል ይመጣና፤
“ለእኔስ አባቴ?” ይለዋል፡፡
“አንተ ሽሆና ይደርስሃል” ይላል አያ ጅቦ፡፡
ቀጠለና ጣፈጦ ጠየቀ፡-
“አባዬ የእኔንስ ነገር ምን አሰብክ?” አለ፡፡
“አንተ ቆዳዋን ካገኘህ ያጠግብሃል” አለ፡፡
ልጆቹ አባታቸው አህያዋን ዘርጥጦ ጥሎ  ሲበላ ዘወር አሉ፡፡
አያ ጅቦ ዋና ዋናውን የአህያዋን ብልት እንደበላ፤ ድንገት የአህያዋ ጌታ ሲሮጥ መጣ፡፡
አያ ጅቦ ፈርጥጦ መውጫ የሌለው የጫካ ጥግ ውስጥ ገብቶ ይሰረነቅና  እየጮኸ ልጆቹን ይጠራል፡፡ ልጆቹ ቀርበው ወደ ጫካው ይጠጉና፤
“አባታችን ምነው ትጮሃለህ?” ሲሉ ይጠይቁታል፡፡
አያ ጅቦም፤
“አድነኝ ልጄ መዝሩጥ?” ይላል፡፡
መዝሩጥም፤
“አባቴ ምን ሰጥተኸኛል እንደበላህ እሩጥ!” ይለዋል፡፡
”አድነኝ ልጄ ማንሾለላ!” ይላል አያ ጅቦ፡፡
“ምን ሰጥተኸኛል ካንድ ጆሮ ሌላ!?” ይለዋል ማንሾለላ፡፡
“አድነኝ ልጄ ድብልብል?”
“አይ አባት! ሸሆና ለማን  ውለታ ይሆናል?!”
ቀጥሎ አያ ጅቦ ጣፈጦን ጠየቀ!
“አድነኝ ልጄ ጣፈጦ?!”
“ማን የጎረሰውን  ማን አላምጦ?” አለ ጣፈጦ፡፡
መላወሻም አጋዥም ያጣው አያ ጅቦ፤ እዚያው ተወጋና ሞተ፡፡
*  * *
ዛሬ እኔ ነኝ ዋናው ጅብ ማለት አይሠራም! ቀድመው ያላሰቡበት  ግለኝነትና ሆዳምነት ምን ላይ እንደሚጥለን አለማሰብ የማታ ማታ ያላጋዥ  ያለመጠጊያ  ያስቀራል፡፡ ከካፒታሊዝም ምርኮኝነታችን ጀምሮ ስግብግብነት፣ በዝባዥነት፣ ዘረፋና ግፍ ይበረከታል፡፡ ያላየነው የገንዘብ ትርፍ ማህበራዊ መልካችንን  ያዥጎረጉረዋል፡፡ እንኳን ሊያተርፈን ራሳችንን ያጎልብናል፡፡ “አድነኝ ልጄ እገሌ” ቢባል ምላሽ አይኖረውም፡፡ ዛሬ ከመቼውም ጊዜ በላይ እርስ በርስ መግባባትና መስማማት ያለብን ሰዓት ነው፡፡ ስለ ሃይማኖት መግባባታችን፣ ስለ አንድነት መግባባታችን፣ ስለ ድንበር መግባባታችን፣ ስለ ዓለማቀፍ እንቅስቃሴዎች መግባባታችን--- እጅግ አስፈላጊና ብርቱ ጥረት ማድረግን የሚጠይቅም ነው፡፡ የፖለቲካ ልዩነቶችን በነፍጥ ለመፍታት መሞከር የሚያስከትለውን አሰቃቂ ጥፋትና እልቂት አሳምረን እናውቀዋለን፡፡ ከስህተታችን አሁንም የተማርን ግን አይመስልም፡፡ ለሁለት ዓመት በደም አፋሳሽ ጦርነት ውስጥ የከረመችው ትግራይ አመራሮች፣ አሁንም ለዳግም ጦርነት እየተንደረደሩ መሆኑ ያስፈራልም፤ ያስደነግጣልም፡፡ በአማራ ክልል ከታጣቂዎች ጋር እንደ ዘበት የተጀመረው ጦርነት በጊዜ በውይይት አለመቆሙ ብዙ ዋጋ እያስከፈለን ነው፡፡ በኦሮሚያም ከታጣቂ ቡድን ጋር ፍሬያማ ድርድር ማድረግ አለመቻሉ ህዝቡን ለእልቂትና ለመከራ እየዳረገው ነው፡፡
በሌላ በኩል፣ የሳሱ ድንበሮችና  መንግሥት አልባ አገራት ወደ አሰቃቂ እልቂት ሊያመሩ እንደሚችሉ ከበቂ በላይ ማሳያዎች አሉ፡፡ እነ ሶሪያ፣ አፍጋኒስታን፣ ኢራቅ፣ ሶማሊያ፣ የመን፣ ሊቢያ ወዘተ-- ለመነሻ አስረጅነት  የቆሙ ተጨባጭ ምሳሌዎቻችን ናቸው! ነገ በየአገሩ ይኸው ሁኔታ ላለመከሰቱ ምንም አስተማማኝ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዋስትና የለም፡፡ በትናንሽ የፖለቲካ አታካራ ተሞልተን፣ ትናንሽ ሙሾ በማውረድ ጊዜያችንን ከምናባክን፣ ትልቁን የዓለም አቀፍም አገር አቀፍም ስዕል (The Bigger Picture) የምናይበትን ዐይናችንን እንክፈት፡፡ ምዕራባውያን፣ ባህል፣ ሃይማኖትና ጥንታዊ ታሪክ ያላቸው አገራት (ኢራቅ፣ ኢራን፣ ሶሪያ፣ የመን፣ ግብፅ፣ ህንድ፣ ጃፓን፣ ቻይና አሁን ደግሞ የእኛው አገር ኢትዮጵያ) ላይ ያነጣጠሩት ያለ ነገር አይደለም፡፡ ባህል የሌላቸው ባለ ባህሎቹን እየገደሉ ነው፡፡ የቅርቦቹ ሶማሊያና ሊቢያ  በመንግሥት- አልባ ሁኔታ ውስጥ መሆን፣ በማን ይሁን በማን ለመጠቃታቸው ሰፊ በር ከፍቷል፡፡
ወደ ሊቢያ በጣሊያን አዛዥነት ስለዘመተው ያለዕዳው ዘማች የኤርትራ ወጣት (ደራሲው አበሻ ይለዋል) እንዲህ የሚል ሀሳብ ይገኝበታል፡፡ ስለ ሊቢያ በረሀ ነው፡-
“የመሸበር ስሜት፣ ሐዘን፣ ተስፋ ቢስነትና ፀፀት ፊታቸው ላይ ይነበባል፡፡ የበረሀው ስዕል አሰቃቂ ነው፡፡ አንዲት ዛፍ አትታይም፡፡ አንዲትም የሳር አገዳ የለችም፡፡  የውሃ ነገርማ ባይነሳ ይሻለዋል፡፡  ወደየትም አቅጣጫ መንቀሳቀስ አይታሰብም፡፡ ግራ፤ ቀኝ፤ ወደፊት፣ ወደኋላ፣ ወደየትም መሄድ  አይቻልም ምክንያቱም የትም ይሁን የት ህይወት በአሸዋ ተከባ ነው  የምትገኘው፡፡ በየትም ቢዞሩ ጠጠር ኮረት ድንጋይ፤ እና የአቧራ ክምር!
ያ በረሀ እንደባህር ሰፊ፤ ግን በጥላቻ  የተሞላ! ባህር ውስጥ ቢያንስ ዓሣ ማየትና የማዕበል ድምጽ  ማድመጥ ይቻላል፡፡ እዚህ ሊቢያ በረሃ ግን  አንዲትም ወፍ አትዘምርም፡፡ አትበርም፡፡  ያ ክፍቱ ደመና አልባ ሰማይ የጋለ ምድጃ ነው፡፡ በዚያ ጠራራ ንዳድ ውስጥ ያለ ሰው፣ ያ መሬት፣ የህይወት ይሁን የሞት  መለየት ይሳነዋል፡፡ ይህን መሬት ከአረንጓዴው፣ ከንፋሳማው እና ከለሙ የኢትዮጵያ ምድር ጋር ማነፃፀር ከንቱ ድካም ነው! የሲዖልና የገነት ነው ልዩነቱ!?”
ስለ አበሻ  የጦርነት ብቃት የሚገርም ትንተናም አለው- በሊቢያ በረሃ፡- አበሻ ፣ ጣሊያንና አረብ የውጊያ መንፈስ ምን ይመስላል?
ለአበሻ፤ ጦርነቱ ምንም ውጤት ያስከፍል ወደፊት መግፋት ነው፡፡ (ግፋ በለው እንደማለት) በጣሊያኖች፤ አዛዥህ እንዳለህ  ተዋጋ ነው፡፡ ጠላት ግንባር  ቢፋጠጥህም ካልታዘዝክ  አትተኩስም፤ ካልታዘዝክ ብትታረድም ፀጥ በል ነው!
ለአረቦች ወደ ጠላትህ ፈጥነህ  ሩጥ፡፡ ሁኔታው የማያዋጣ ከመሰለህ ነብስህን ለማዳን ፈርጥጥ ነው፡፡ የየተዋጊውን ባህሪ ለእኔ ብሎ መስማት የእኛ ፈንታ ነው፡፡ ጊዜው አስጊ ነው፡፡  ጎረቤቶቻችንን በቅጡ እናስተውል፡፡ ሩቅ የሚመመስሉንን ዕጣ ፈንታ ስናይ፣  “ያንተ ቤት ሲንኳኳ  ይሰማል እኔ ቤት” እንበል፡፡  “ጎረቤትህ ሲያማ ለእኔ ብለህ ስማ!” ማለት የአባት ነው!!

 

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ፤ “አሁን ከቁጥጥራችን ውጭ እየሆኑ ያሉ ሁኔታዎች በፖሊስ አቅም የሚፈቱ ነበሩ” ሲሉ ተናግረዋል። ፕሬዚዳንቱ እንደገለጹት፣ በትግራይ ክልል የሚፈጠረው ችግር ኢትዮጵያን የማተራመስ አቅም አለው።
አቶ ጌታቸው ከትላንት በስቲያ መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓ.ም. በሸራተን አዲስ ሆቴል ለጋዜጠኞች በትግራይ ክልል ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በሰጡት መግለጫ፣ በርካታ ጉዳዮችን አንስተዋል። በዚሁ መግለጫቸው፤ በትግራይ የተፈጠረውን ፖለቲካዊ ውጥረትና አለመረጋጋት ተከትሎ፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ የፌደራል መንግሥት ወደ ክልሉ እንዲገባ በይፋ አለመጠየቁን አስታውቀዋል፡፡
“የክልል መንግሥታት ‘የክልል አቅም’ የሚባለውን፣ ሁሉንም ዓይነት መንገዶች ተጠቅመው ‘አንድን ጉዳይ መቆጣጠር አቅቶናል’ በሚሉበት ሰዓት፣ ምክር ቤት ጠርተው የፌደራል መንግስትን ጣልቃ እንዲገባ ይጠይቃሉ ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ አሁን ባለንበት የትግራይ ሁኔታ በእንደዚህ አይነት መልኩ ተሰብስቦ ጥያቄ ሊያቀርብ የሚችል ምክር ቤት የለም” ሲሉ የእርሳቸው አስተዳደር የፌደራል መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ ያልጠየቀበትን ምክንያት አብራርተዋል። በተጨማሪም፣ “የሕግ ተቀባይነት ያጣ ቡድን” ሲሉ የጠሩት፣ በዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የሚመራው የህወሓት ወገን፣ የተወሰኑ ወታደራዊ መኮንኖችን በመያዝ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ተናግረዋል።
“ይህንን ሁኔታ ስርዓት ለማስያዝ በሚደረገው እንቅስቃሴ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ውስጥ ያለውን አቅም ለመጠቀም የሚያስችለውን ዕድል ነው እየተነፈገ የመጣው” ያሉት አቶ ጌታቸው፤ “አሁን ከቁጥጥራችን ውጭ እየሆኑ ያሉ ሁኔታዎች በፖሊስ አቅም የሚፈቱ ነበሩ” ብለዋል። አክለውም፤ “በዚህ ሰዓት የፌዴራል መንግሥቱ ይህንን ለማረም አግባብነት ያላቸው እርምጃዎችን መውሰድ ‘አለበት’ ስንል፣ ‘ጦር አዝምቶ፣ ጦርነት ይቀስቅስ’ እያልን አይደለም። አሁን እየተደረገ ባለው እንቅስቃሴ ወደ ጦርነት የሚያንዣብበውን ሂደት ለማስቀረት የሚያስችል ሁሉንም ዓይነት እርምጃዎች መውሰድ ‘አለበት’ ብለን እናምናለን” ሲሉ ገልጸዋል።
ከእነዚህም እርምጃዎች ውስጥ የዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ህወሓት አመራሮችን ጠ/ሚኒስትሩ ተቀብለው አለማናገር አንደኛው መሆኑን አቶ ጌታቸው ጠቅሰዋል፡፡
“የእኔ ፍላጎት ጦርነትን ማስወገድ ነው፡፡ ሌላ ጦርነት ማካሄድ ሳይሆን ጦርነትን ለማስወገድ የሚያስችሉ ሁሉም አስፈላጊ እርምጃዎች መወሰድ አለባቸው” ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ በትግራይ ክልል የሚፈጠረው ችግር ኢትዮጵያን የማተራመስ አቅም እንዳለው ያሳሰቡ ሲሆን፤ ከኤርትራ መንግሥት ጋር ግንኙነት መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን የሚናገሩ የጦር አዛዦች መኖራቸው አስደንጋጭ ነው ብለዋል፡፡ “ከኤርትራ ጋር ግንኙነት መፍጠር ካስፈለገ፣ የተፈጸሙትን ጭፍጨፋዎች በመካድ አይደለም የሚፈጠረው” ሲሉም አክለዋል፡፡
በትግራይ ለጦርነት መከሰት ምክንያት የሆኑ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ በመሆናቸው፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ተጨማሪ ተፈናቃይ ዜጎችን ለማስተናገድ መገደዱን ፕሬዚዳንቱ በመግለጫቸው ተናግረዋል። በዶ/ር ደብረጽዮን የሚመራው ህወሓት፣ ተፈናቃዮችን ለፖለቲካ ዓላማው እየተጠቀመባቸው ስለሆነ፣ ወደ ቀድሞ ቀያቸው እንዳይመለሱ፣ ብሎም የጤናና የእርዳታ ግልጋሎቶችን እንዳያገኙ እያደረገ ነው ሲሉም ወቅሰዋል።
“የፌደራል መንግሥትን እስካሁን የወቅስኩት ይበቃኛል” ያሉት አቶ ጌታቸው፤ “የፌደራል መንግሥት የሰራቸውን ጥሩ ስራዎች መናገር ተቀባይነት እንድናጣ የሚያደርገን ስለሆነ ወቀሳው ላይ እናተኩራለን” ብለዋል።
በትግራይ ክልል ሕገ ወጥ የወርቅ ንግድ፣ የሰዎች ዝውውርና መሰል ተግባራት በከፍተኛ ደረጃ ማሻቀባቸውንና በእነዚህ ድርጊቶች ውስጥ ተሳታፊ የሆኑ ሰዎች አሁን ላይ ያለውን ያልተረጋጋ ሁኔታ ከተጠያቂነት የማምለጫ መንገድ አድርገው እየተጠቀሙበት መሆናቸውን ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።
“90 በመቶው ሕዝብ ሰላምን ስለሚፈልግ ይደግፈኛል” የሚሉት አቶ ጌታቸው፤ ወጣቱ የሕብረተሰብ ክፍል ምርጫው ሰላም መሆኑንና ወደ ጦርነት መግባት እንደማይፈልግ አንስተዋል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም፤ “70 በመቶ ሕዝብ ‘ወጣት ነው’ ስንል፣ ‘ሽማግሌ አይደግፍም’ ማለት አይደለም። ሰላም ወዳድ ሁሉ ግን ጊዜያዊ አስተዳደሩን ይደግፈዋል” ብለዋል።
“ሕጋዊው አስተዳደር የእኔ ነው። የፌደራል መንግሥቱ የሚያውቀው የእኔን አስተዳደር ነው” ያሉት አቶ ጌታቸው፤ በተለያዩ የትግራይ አካባቢዎች ስለሚስተዋለው የማሕተም እሰጣ ገባ ሲናገሩ፤ “ሕዝቡ ማሕተም የያዘ ‘ይምራኝ’ አላለም” ብለዋል፡፡ በህወሓት አመራሮች መካከል ሥልጣን ለመያዝ የሚደረገውን ሽኩቻ የነቀፉት ፕሬዚዳንቱ፤ “እኔን ጨምሮ ሌሎችም ለያዝነው ስልጣን የሚመጥን ስራ አልሰራንም” ሲሉ ተናግረዋል።
ከሰሞኑ ከማሕተም እሰጥ አገባና ከወረዳ ምክር ቤት ጋር በተያያዘ በዓዲጉደም እና ዓዲግራት ከተሞች የተፈጠረውን ውዝግብግና ግጭት አስመልክቶ፣“የወረዳ ምክር ቤቶች ሕጋዊነት እንደምን ይታያል? ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ ምክር ቤት ጋር በተገናኘ የሚነሳውን የሕጋዊ ቅቡልነት ጥያቄ እርስዎ እንዴት ይገመግሙታል?” በሚል ከአዲስ አድማስ ጥያቄ የቀረበላቸው አቶ ጌታቸው ሲመልሱ፤ “በ2012 ዓ.ም. ያደረግነውን ምርጫ በፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ‘ሕገ ወጥ ነው’ ብለን ተስማምተናል። ምክር ቤቶቹ ከተቋቋሙ 12 ዓመት ያህል የሆናቸው ናቸው።” ብለዋል። አክለውም፤ “አንዳንድ ወገኖች ‘የፌደራል መንግስት ምርጫ ስላላደረገ፣ እነዚህ ምክር ቤቶች አይፈርሱም’ ሲሉ ይሟገታሉ። ፌደራል መንግሥቱ የምክር ቤቶቹን ደንብ አውጥቶ ይሆናል፤ የማውቀው ነገር የለም። አብዛኛዎቹ ምክር ቤቶች ከነበራቸው 150 አባል፣ አሁን ላይ 20 ሰው ነው ያላቸው።” በማለት አስረድተዋል።
ለአብነት ያህል ታሕታይ ማይጨው አካባቢን ያነሱት አቶ ጌታቸው፤ “ሰው አጥተው፣ አፈ ጉባዔው ስለጠፋ ከቀበሌ አንድ አፈ ጉባዔ ተጠርቶ የምክር ቤት ስብሰባ ተጠርቶ፣ ‘የወረዳ አስተዳዳሪውን አንስተናል፣ የወረዳ አስተዳዳሪ ሾመናል’ ይላሉ። እንደዚህ ዓይነት ድራማ ዕድሜ ልክ ሲሰራበት የኖረ ነው።” ብለዋል። የእርሳቸው አስተዳደር አላግባብ ከስልጣን መውረድና መሾም እንዳይኖር ደንብ ማውጣቱን አውስተው፣ ይሁንና “ጠመንጃ የያዙ ሰዎችን የሚመሩ” ያሏቸው ወታደራዊ መኮንኖች፣ ሕገ መንግስት መተንተን መጀመራቸውን አመልክተዋል።
“20 ሰው ያለው ምክር ቤት፣ ምክር ቤት አይደለም። ካቢኔው በወሰነው መሰረት ለማስተካከል ተሞክሯል። አንድ ሰው አርጩሜ ይዞ ሄዶ ‘አንተ በሕገ መንግስቱ መሰረት ተመርጠሃል፣ አልተመረጥክም’ ለማለት ማን ነው መብት የሰጠው?” ሲሉ የጠየቁት አቶ ጌታቸው፤ “ይህ ትርምስ ነው የምናየውን የውጥረት ሁኔታ የፈጠረው። ጥይት እየተተኮሰ ሰዎች እየተጎዱና እየተገደሉ ያለውም በዚህም ምክንያት ነው።” ብለዋል። አያይዘውም፣ “የተወሰኑ የሰራዊት አመራሮችና በአብዛኛው ‘ጉባዔ አድርጌያለሁ’ እያለ የሚያምታታ ከፍተኛ የስልጣን አባዜ ያለው ቡድን የፈጠረው ሁኔታ ነው። ሕዝቡን እያሸበሩት ነው። ሕዝቡም እየተቃወማቸው ነው።” ሲሉ ገልጸዋል።
የክልሉን ጊዜያዊ ምክር ቤት በተመለከተ፣ በጊዜያዊ አስተዳደሩ በወጣ ደንብ መሰረት መቋቋሙን አስታውቀው፣ “አማካሪ ምክር ቤት ነው። ምክር ቤቱ ‘ስራ ለመስራት የሚያስችሉ ተቋማትን ማቋቋም ይችላል’ የሚል በመቋቋሚያ ደንቡ ውስጥ የተካተተ ሃላፊነት አለ። የጊዜያዊ ምክር ቤቱ ሕጋዊነት ሳይሆን አሁን እየተደረገ ያለው ዕንቅስቃሴ ጊዜያዊ አስተዳደሩ የፌደራል መንግስት ‘አጋር ነው’ በማለት ለማፍረስ በመሞከር፣ ከፌደራል መንግሥቱ ሕጋዊነት የሚፈልግ አካል አለ።” በማለት ወቅሰዋል።
በክልሉ እርሳቸው የሚመሩትን ጊዜያዊ አስተዳደርና የፕሪቶሪያ ስምምነትን ለማፍረስ “እየተደረገ ነው” ያሉት እንቅስቃሴ በፍጥነት እንዲገታም ጥሪ አቅርበዋል። የፌዴራል መንግሥቱም ይህንን ለማረም አግባብነት ያላቸው እርምጃዎች መውሰድ እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

በዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት፣ “በትግራይ መፈንቅለ መንግሥት ‘ተካሂዷል’ የሚባለው ውሸት ነው” ሲል ገለጸ። ህወሓት ከኤርትራ መንግሥት ጋር ግንኙነት እንደሌለውም ቡድኑ አመልክቷል።
ከትላንት በስቲያ ሐሙስ መቐለ ከተማ በሚገኘው የህወሓት ጽሕፈት ቤት ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት የፓርቲው ምክትል ሊቀ መንበር አቶ አማኑኤል አሰፋ፤ “ሕዝቡን በተዛባ ወሬ ወደ አላስፈላጊ ውዥንብር በማስገባት፣ መሬት ላይ በሌለ ግጭት ውጥረት ውስጥ መክተት ሃላፊነት ከሚሰማው ፖለቲከኛ የሚጠበቅ አይደለም “ በማለት ተናግረዋል። አክለውም፤ “ሕዝቡን የሚያሰጋ ነገር በሌለበት ሁኔታ ገንዘብ ከባንክ ለማውጣትና አስቤዛ ለመግዛት መሯሯጥ አይገባውም” ብለዋል።
“ህወሓት በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት ለፌደራሉ መንግሥት የሰጠውን እውቅና በማጠናከር በመመካከር መስራቱን ይቀጥላል” ያሉት አቶ አማኑኤል፤ ከፌደራል መንግሥቱ ጋር በቀጣይ “እናደርገዋል” ስላሉት ተግባር አብራርተዋል። ፓርቲው ከሥልጣን ባነሳቸው የጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ምትክ፣ ከፌደራል መንግሥት ጋር በመተማመን አዲስ ፕሬዚዳንት እንደሚመርጡም ጠቁመዋል፡፡
የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር “የቀድሞ ፕሬዚዳንት” ሲሉ የጠሯቸው አቶ ጌታቸው ረዳ፤ ከሰሞኑ በከፍተኛ የሰራዊቱ አመራሮች ላይ የወሰዱት የእግድ ዕርምጃ “በሌላቸው ስልጣን የተደረገና ተቀባይነት የሌለው ነው” ሲሉም አጣጥለውታል።
አቶ አማኑኤል፤ “’በትግራይ መፈንቅለ መንግሥት ተካሂዷል’ የሚባለው ፍጹም ውሸት ነው፤ ህወሓት በጊዜያዊ አስተዳደሩ ያለውን የሥልጣን ድርሻ ከማስተካከል የዘለለ አንዳችም የወሰደው እርምጃ የለም” ቢሉም፣ ከትላንት በስቲያ ሐሙስ አቶ ጌታቸው ረዳ በሸራተን አዲስ በሰጡት መግለጫ፤ በጊዜያዊ አስተዳደሩ ላይ የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
“በዶ/ር ደብረጽዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን ከኤርትራ መንግሥት ጋር ግንኙነት አለው” ስለተባለው ጉዳይ ያነሱት አቶ አማኑኤል፤ ነገሩ ውሸት ነው” ሲሉ አስተባብለዋል። “ከኢትዮጵያ መንግሥት ዕውቅና ውጪ ከኤርትራ ጋር የሚካሄድ ግንኙነት የለም” ሲሉም አክለዋል።
በተያያዘ ዜና፣ የኤርትራ መንግሥት የማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል በትዊተር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ፤ መንግሥታቸው የህወሓት ክፍፍል እንደማይመለከተው ጠቅሰዋል። “የህወሓት መከፋፈል ኤርትራን አይመለከትም” ያሉት ባለሥልጣኑ፤ “የትግራይ ሕዝብ የውስጥ ሰላም እንዲበጠበጥ ኤርትራ ምንም ዓይነት ፍላጎት የላትም” ብለዋል።
“የተለያየ የፖለቲካ እሳቤ ያላቸው የኢትዮጵያ ፖለቲከኞች የቀይ ባህርን አጀንዳ እንደ አዲስ በማቀጣጠል የአፍሪካ ቀንድን ወደ ሌላ ተጨማሪ ውጥረት ከማስገባት ይቆጠቡ” ሲሉም አሳሰበዋል፤ አቶ የማነ።

የኬሌ - ቶሬ - ጨለለቅቱ - ዲላ መንገድ በመዘጋቱ ምክንያት ለችግር መዳረጋቸውን የኮሬ ዞን ነዋሪዎች ተናግረዋል። ነዋሪዎቹ እንደገለጹት፣ ለመንግስት አካላት ስሞታ ቢያቀርቡም፣ ሰሚ አላገኙም።
ነዋሪዎች ለአዲስ አድማስ እንደተናገሩት፤ ከ2009 ዓ.ም. አንስቶ ከምዕራብ ጉጂ የሚነሱ ታጣቂዎች የሚፈጽሟቸው ጥቃቶች እያገረሹ መምጣታቸውን ተናግረዋል። በኮሬ ዞን፣ ጎርካ ወረዳ፣ ጄሎ ቀበሌ ቅዳሜ የካቲት 29 ቀን 2017 ዓ.ም. እና በማግስቱ፣ ከኦሮሚያ ክልል፣ ምዕራብ ጉጂ ዞን፣ ገላና ወረዳ የተነሱ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት፣ ሁለት ሰዎች እንደተገደሉ ጨምረው ገልጸዋል።
አቶ ሱልጣን አብድራህማን የተባሉ የጄሎ ቀበሌ ነዋሪ ሲናገሩ፤ “ከረፋዱ 4፡30 እስከ 5፡00 ባለው ሰዓት ነው ጥቃቱ የተፈጸመው። የአካባቢው ነዋሪዎች ከብቶቻቸውን ውሃ እያጠጡ ነበር።” ብለዋል። የእርሳቸው የቤተሰብ አባል የሆኑት አርሶአደር ሽኩር ዩሱፍ በታጣቂዎቹ ጥይት ተመትተው ከቆሰሉ በኋላ፣ ወደ ኬሌ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተወስደው እንደነበር አቶ ሱልጣን አውስተው፣ ወደ አርባምንጭ ሆስፒታል ሪፈር ተብለው እየተጓዙ ሳለ፣ አርባምንጭ ከተማ ሊደርሱ 30 ኪሎሜትር ሲቀራቸው ሕይወታቸው ማለፉን አመልክተዋል።
ጥቃት አድራሾቹ ከምዕራብ ጉጂ የሚነሱ ታጣቂዎች መሆናቸውን ያስረዱት አቶ ሱልጣን፤ ጥቃቱ ለስምንት ተከታታይ ዓመታት በተደጋጋሚ መቀጠሉን ገልጸዋል። በተጨማሪም፣ ከስምንት ዓመት አንስቶ የሁለት ቀበሌዎች ነዋሪዎች ተፈናቅለው በድንኳን ውስጥ እየኖሩ እንደሚገኙና ወደ ቀድሞ ቀያቸው እንዳልተመለሱ አስታውቀዋል።
ከሐምሌ 16 ቀን 2009 ዓ.ም. ጀምሮ መንገድ በመዘጋቱ ሕዝቡ ወደ አዲስ አበባ ለመጓዝ 900 ኪሎሜትሮችን ያህል አቆራርጦ መሄድ ግዴታ እንደሆነበት የሚናገሩት አቶ ሱልጣን፤ “በኢኮኖሚ ረገድ የአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ጉዳት እየደረሰ ነው” ብለዋል። በተለይም፣ በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነዳጅ ዕጥረትና የጥቁር ገበያ የነዳጅ ሽያጭ ተጽዕኖ መፍጠሩን አስረድተዋል።
ሌላኛው ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ነዋሪ በበኩላቸው፣ የጄሎ ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ወጣት ቡጥሳ ጉይባ በታጠቁ ሃይሎች መገደሉን ገልጸዋል። ታጣቂዎቹ የሚነሱት ከምዕራብ ጉጂ ዞን፣ ገላና ወረዳ መሆኑንም ጨምረው ጠቅሰዋል።
ታቅዶበት የሚፈጸም ጥቃት መሆኑን የሚያነሱት እኚሁ ነዋሪ፤ “ከተጠያቂነት ለመሸሽ የሚፈጸም ጥቃት ይመስላል” ብለዋል። ይሁንና ከተጠያቂነት “ይሸሻል” ስላሉት ሃይል በውል የገለጹት ነገር የለም። ነዋሪው የክልሉ መንግስት ጥቃት አድራሹን ሃይል ሊቆጣጠረው አለመቻሉንና ከመንግስት በኩል ቸልተኝነት እንደሚስተዋል ጠቁመዋል። አክለውም፤ “ጥረት ቢደረግ ኖሮ፣ ለዘጠኝ ዓመታት አንድ ማሕበረሰብ ከቀዬው ተፈናቅሎ አይኖርም ነበር” ብለዋል።
“በኮሬ ዞን ይቅርና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አቅም የሚፈታ ችግር አይደለም” የሚሉት ደግሞ አቶ ሱልጣን ናቸው። አቶ ሱልጣን ጨምረው እንደተናገሩት፤ ጉዳዩ የፌደራል መንግስትን የሚመለከት ነው። የመከላከያ ሰራዊት በኮሬና በምዕራብ ጉጂ ዞኖች አዋሳኝ ላይ በምትገኘው ኮምቦልቻ ከተማ ላይ ሰፍሮ እንደሚገኝና በጥቃት አድራሾቹ ሃይሎች ላይ እርምጃ እየወሰደ አለመሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የኬሌ - ቶሬ - ጨለለቅቱ - ዲላ መንገድ በመዘጋቱ የሕዝብ መመላለሻ መኪናዎች እንደማይጓዙና ለጥቂት ቀናት ብቻ አምቡላንሶች እንዲሄዱ ክፍት ቢሆንም፣ ታጣቂዎች በሚፈጽሙት ጥቃት ተመልሶ መዘጋቱን ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉት ነዋሪ ጠቁመዋል። “ከጌዲኦ እስከ ኮንሶ ድረስ የሚያደርስ መንገድ ነበር። ይሁንና በተደጋጋሚ ሾፌሮች ስለሚገደሉ፣ ንብረት ስለሚዘረፍና ተጓዦች ስለሚታገቱ መንገዱ ዝግ ሆኗል።” ብለዋል።
ከተለያዩ አካባቢዎች ወደ ዞኑ ሸቀጦችን ለማምጣት ችግር በመፍጠሩ ምክንያት የኑሮ ውድነት ተባብሶ መቀጠሉን የተናገሩት ነዋሪው፤ በደረጃቸው ከፍ ያሉ የሕክምና አገልግሎቶችን ማግኘት ፈተና እንደሆነም አስረድተዋል።
ነዋሪዎቹ ለመንግሥት ተደጋጋሚ አቤቱታ ቢያቀርቡም፣ ሰሚ ባለማገኘቱ በጥቃቶቹና ተያያዥ ችግሮች ምክንያት እየተሰቃዩ እንደሚገኙ አብራርተዋል። የመንግስት አካላት ስሞታቸውን አዳምጠው መፍትሔ እንዲሰጧቸውም ተማጽነዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ የዞኑን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ሃላፊ አቶ ተፈራ ቦንዶሮ ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ወላይታ ዞን ዳሞት ወይዴ ወረዳ፣ ባዴሳ ከተማ አካባቢ በዛሬው ዕለት በደረሰ የመኪና አደጋ የ15 ሰዎች ህይወት ማለፉን የዞኑ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
መኪናው በአጠቃላይ 46 ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረ ሲሆን፤ 5 ሰዎች ያለምንም ጉዳት ከአደጋው መትረፋቸው ታውቋል፡፡
ከአርባ ምንጭ ወደ ሻሸመኔ ይጓዝ የነበረ መኪና፣ ባዴሳ ከተማ አካባቢ ሲደርስ ፍሬን በመበጠስ ወንዝ ውስጥ ተገልብጦ በመግባት ገብቶ አደጋው መድረሱ ተነግሯል፡፡
አደጋው የደረሰባቸው ወደ አርባ ምንጭ ዚጊቲ ደብረ ሠላም አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ጉዞ አድርገው ሲመለሱ በነበሩ ወጣት ምዕመናን ላይ መሆኑ ታውቋል፡፡
ዛሬ ጠዋት 11 ሰዓት ገደማ በደረሰው በዚህ የትራፊክ አደጋ፣ ሹፌሩንና ረዳቱን ጨምሮ የ15 ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ ሲያልፍ፤ በ21 ሰዎች ላይ ከባድ፣ በ6 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል ጉዳት መድረሱን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ንጋቱ ጌታቸው ገልፀዋል። ከባድና ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው ተጎጂዎች ወደ ሆስፒታል ተወስደው ሕክምና እየተደረገላቸው መሆኑንም አክለዋል፡፡
አሸናፊዎቹ በጄኔቫ በሚካሄደው ውድድር ላይ ይሳተፋሉ
ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከሲያትል አካዳሚ ጋር በመተባበር፣ ‘’AI for Good Youth Challege Ethiopia’’ በሚል መሪ ቃል፣ በቴክኖሎጂ ፈጠራ ተሰጥኦ ያላቸው ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ዩኒቨርሲቲ ድረስ በመማር ላይ የሚገኙ ሕፃናትና ወጣቶችን ያካተተ ውድድር ተካሂዷል።
በውድድሩ ከተለያዩ ክልሎች የተውጣጡ ተማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን፤ ተወዳዳሪዎቹ በሰው ሠራሽ አስተውሎት ኢንጂነሪንግና ዲዛይን የሠሯቸውን ፕሮጀክቶች አቅርበዋል።
በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የኢኖቬሽን ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሰላምይሁን አደፍርስ ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽ ትግበራ እውን እንዲሆን፣ ለኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ሥራዎች ዕድገትና ቀጣይነት የሚሠሩና አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ አካላትን በቀዳሚነት እንደግፋለን ብለዋል።
የSTEM Power ካንትሪ ዳይሬክተር ዶክተር ስሜነው ቀስክስ በበኩላቸው፤ ከሰው ሰራሽ አስተውሎት ጋር በማያያዝ ሕፃናትና ወጣቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂዎች ማሳተፍ፣ ብዙ ሳይንቲስቶችና ሥራ ፈጣሪዎች እንዲወጡ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
የውድድሩ አሸናፊዎች ሽልማት የሚበረከትላቸው ሲሆን፤ ከሃምሌ 8 – 11 ቀን 2017 ዓ.ም ጄኔቫ ላይ በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና ባህል ድርጅት በሚያካሄደው የሰው ሠራሽ አስተውሎት ኢንጂነሪንግ ውድድር ላይ ኢትዮጵያን ወክለው እንደሚሳተፉ ታውቋል፡፡
(ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር)

ይኸውም ነገ መጋቢት 7 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 5:00 ሠዓት ጀምሮ በመስቀል አደባባይ የሚከናወነውን የኢፍጣር ፕሮግራም ምክንያት በማድረግ፦
???? ከኦሎምፒያ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ )
???? ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ መብራት (ጥላሁን አደባባይ ሲሆን ከባድ ተሽከርካሪ አጎና ላይ )
???? ከለገሃር መብራት ወደ መሰቀል አደባባይ (ለገሃር መብራት)
???? ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድየም (ቴሌ ማቋረጫ ላይ)
???? ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ (ሀራምቤ መብራት ላይ )
???? ከብሔራዊ ቤተ መንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ (ብሔራዊ ቤተመንግሥት ላይ )
???? ከቅዱስ ዑራኤል አደባባይ ወደ መስቀል (ባምቢስ መቅረዝ ሆስፒታል መታጠፊያ ድረስ የሚዘጋ መሆኑን በመገንዘብ አሽከርካሪዎች አማራጭ እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ያሳስባል።

"ወታደራዊ ሃይልን ወደ ስልጣን የማምጣት ጉዳይ አይታሰብም"
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ፤ ከፌደራል መንግስትም ጋር ይሁን ከሌላ አካል ጋር ወደ ግጭት የሚያስገባ ነገር እንደሌለ አስታወቁ፡፡
“በምንም መልኩ በውስጣችን የሚፈጠር ግጭትና ጦርነት አይኖርም፣ የውስጥ ግጭት ይፈጠራል የሚለው ጉዳይ ዝግ ነው” ያሉት ጄነራሉ፤ “ግጭቱና ጦርነቱ በውስጣችን ይሆናል ወይም ደግሞ ከውጭ በሚኖር ግፊት ይጀመራል የሚለው ጉዳይ ሊያሳስብ አይገባም፣ አይኖርም” ብለዋል።
ባለፉት ቀናት በክልሉ የተካሄዱት ሁነቶች በምንም መልኩ ከወታደራዊ ድርጊት ጋር የሚያያዙ አይደለም ያሉት ጄነራል ታደሰ፤ “በምንም መልኩ ወታደራዊ ሃይልን ወደ ስልጣን የማምጣት ጉዳይ አይደለም፤ ይህ ፈጽሞ የማይሆን ነገር ነው” ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በህወሓት አመራሮች መካከል የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት የሀይማኖት አባቶችን ጨምሮ በተለያዩ አካላት የተለያዩ ጥረቶች ቢደረጉም ሊሳካ አልቻለም፤ ችግሩ ከአደራዳሪዎቹ ሳይሆን ከተዳራዳሪ አካላት የመነጨ ነበር ያሉት ጄነራሉ፤ ዋና ተግዳሮት የሆነው “አለመቀበልና እንቅፋት መፍጠር፣ አንዱ ወገን አንዱን ወገን አሸንፎ ለመውጣት ፍላጎት መኖሩ” እንደነበር አስረድተዋል፡፡
ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ታደሰ ይህን ይበሉ እንጂ፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት ጌታቸው ረዳ ከትላንት በስቲያ በአዲስ አበባ በሰጡት መግለጫ፤ ህገወጥ ያሉት የህወሓት ቡድን አመራሮች ሥልጣን በሃይል ለመንጠቅ እያደረጉት ያለው እንቅስቃሴ ወደ ጦርነትና ግጭት እንደሚያመራ ማስጠንቀቃቸው ይታወቃል፡፡ የፌደራል መንግሥትም ድርጊቱን ለመግታት አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡

በትግራይ የሕወሓት አንደኛው አንጃ ለራሱ ጥቅም ሲል እየፈጠራቸው ያሉ ድርጊቶች ተገቢነት የሌላቸውና ህዝብን ችግር ውስጥ የሚከቱ በመሆናቸው በጊዜ መቆም እንዳለባቸው የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር አረጋዊ በርሔ አሳስበዋል፡፡

በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ሁሉንም አካታች የሆነ አስተዳደር በክልሉ መተግበር እንዳለበት የገለጹት ሊቀመንበሩ፤ የትግራይ ህዝብ ከመጠን በላይ በጦርነት ተጎድቷል ብለዋል፡፡
ከፕሪቶሪያው ስምምነት ወዲህ በክልሉ የተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር በህወሓት አንጃ እንዲጨናገፍ መደረጉን የጠቆሙት ዶ/ር አረጋዊ፤ የፌደራል መንግስት በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ሁሉንም ያካተተ አስተዳደር ተመስርቶ፣ ህዝቡን ከዳግም መከራ ሊታደገው ይገባል ሲሉ ገልፀዋል።

Page 2 of 760