Administrator

Administrator

ጽላቱን የሚያውቁ ካህናት በምርመራው መካተት እንዳለባቸው ተጠቁሟል
• “ጥያቄውን ለሀገረ ስብከቱ እንዳናቀርብ ሥራ አስኪያጁ ያሳስሩናል” /ምእመናኑ

በጋምቤላና ደቡብ ሱዳን አህጉረ ስብከት መንበረ ጵጵስና የምትገኘው፣ የሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ካቴድራል ዕድሜ ጠገብ ታቦት፣ የደረሰበት አለመታወቁን የከተማው ምእመናን የተናገሩ ሲሆን፤ በአቋራጭ መክበር በሚፈልጉ ስግብግቦች እጅ ሳይገባ አፋጣኝ ማጣራትና ምርመራ እንዲካሔድላቸው መንበረ ፓትርያርኩን ጠየቁ፡፡
ቤተ ክርስቲያኒቱ፣ በንጉሠ ነገሥት ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ትእዛዝ በ1941 ዓ.ም. መታነጿንና ሙሉ በሙሉ በወርቅ የተለበጠ የኪዳነ ምሕረት ታቦትም እንዲገባ ካስደረጉ በኋላ፣ ሥርዓተ እምነታቸውን ሲፈጽሙባትና ሲማፀኑባት እንደኖሩ ምእመናኑ ጠቅሰው፤ ከየካቲት 24 ቀን ጀምሮ ግን ታቦቱ በመንበሩ ላይ እንደሌለ ከካቴድራሉ ካህናት መስማታቸውን ተናግረዋል፡፡
የታቦቱ/ጽላቱ/ በመንበሩ ላይ አለመኖር በመጀመሪያ ያረጋገጡት የካቴድራሉ አስተዳዳሪ እንደነበሩና ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸውን ቄሰ ገበዙን እንደጠየቋቸው ያወሱት ምእመናኑ፣ ቄሰ ገበዙ፥ “እኔን ለምን ትጠይቁኛላችሁ? ሥራ አስኪያጁን ጠይቁ፤” የሚል ምላሽ በመስጠታቸው፣ “ሁኔታውን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎብናል፤” ብለዋል፡፡ በቀጥታ ለጋምቤላ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ እንዳያቀርቡ፣ “የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጁን ተጠቅመው ያሳስሩናል፤” ብለው እንደሚሰጉና ሁከት እንዳይቀሰቀስ ፍርሃት እንዳደረባቸው ምእመናኑ አልሸሸጉም፡፡
“ለምነን ያላፈርንባት፤ ችግራችንን ፈጥና የምትሰማን የኪዳነ ምሕረት ታቦት ጠፍታ እንዴት ዝም እንላለን፤ ብለን በአንድ ቦታ ተሰብስበን ከተመካከርን በኋላ በትዕግሥትና በሥርዓት ለሚመለከተው የበላይ አካል ማመልከትን መርጠናል፤” ያሉት ምእመናኑ፣ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት፣ ባለፈው መጋቢት 13 እና 14 ቀን፣ ጉዳዩን ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት፣ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤትና ለፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት ማቅረባቸውን አስታውቀዋል፡፡
ሙሉ በሙሉ ከወርቅ የተሠራው ታቦት፣ የሀገርም ቅርስ መሆኑን ምእመናኑ ጠቁመው፣ በአቋራጭ የመክበር ምኞት በተጠናወታቸው ስግብግቦች እጅ ሳይገባ፣ በመንበረ ፓትርያርኩ መሪነት አስቸኳይ ማጣራትና ምርምራ እንዲካሔድላቸው ተማፅነዋል፤ ጽላቱ የሚቀመጥበት መንበር ባዶ መኾኑን የሚያሳይ በወቅቱ የተቀረፀ የቪዲዮ ምስል በአባሪነት ማቅረባቸውን ገልጸው፣ ጽላቱ በመንበሩ ላይ ተገኘ ቢባል እንኳ፣ ዕድሜ ጠገቡ ጽላት መሆኑን ለይተው በሚያውቁ ካህናት ታይቶ መረጋገጥ እንደሚኖርበት ጨምረው አሳስበዋል፡፡
አህጉረ ስብከቱን በዋና ሥራ አስኪያጅነት የሚመሩት መጋቤ አእላፍ ቆሞስ አባ ተክለ ሃይማኖት፣ በክልሉ ተመድበው በሠሩበት ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት፣ 17 ብቻ የነበሩት አብያተ ክርስቲያናት ቁጥር ወደ 53 ማደጉንና በደቡብ ሱዳን ጭምር መታነፃቸው ተገልጧል፡፡ ይህም የዋና ሥራ አስኪያጁን ሐዋርያዊ ትጋት ያመለክታል ቢባልም፣ በአገልግሎታቸው ቀጣይነትና አያያዝ ረገድ፣ ከአገልጋዮችና ምእመናን በርካታ ጥያቄዎች እየተነሡ እንደሚገኙ ተጠቁሟል፡፡
ወደ ማተሚያ ቤት እስከገባንበት ሰዓት ድረስ፣ የሀገረ ስብከቱን ዋና ሥራ አስኪያጅ በእጅ ስልካቸው ላይ በመደወል አስተያየታቸውን ለማካተት ያደረግነው ተደጋጋሚ ጥረት አልተሳካም፡፡



የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ ይፃረራል፤ ያሉት የትግርኛ ቋንቋ ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ ከሥርጭት እንዲታገድላቸውና እንዲወገድላቸው፣ የመቐለ ምእመናን የጠየቁ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር በበኩሉ፣ “ትርጉሙ፣ በቤተ
ክርስቲያኗ ሊቃውንት የተሠራ ነው፤ ስሕተት አለው፤ የሚል እምነት የለንም፤” ብሏል፡፡
ከ40 በላይ የሆኑ ምእመናን የተፈራረሙበት ማመልከቻ፤ ለትግራይ አህጉረ ስብከት 4 ሊቃነ ጳጳሳት በግንቦት 2008 ዓ.ም ያቀረቡ ቢሆንም፤ ለጥያቄያቸው እስከ አሁን ምላሽ እንዳልተሰጣቸው ምዕመናኑ ለአዲስ አድማስ አስታውቀዋል፡፡
የኦርቶዶክስ፣ የካቶሊክ እና የወንጌላውያን ኅብረት አብያተ ክርስቲያናት አባል የሆኑበት የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ያሳተመው ይህ መጽሐፍ ቅዱስ፤ “ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አስተምህሮ በተፃራሪ፡- የክርስቶስን የባሕርይ አምላክነት የሚክድ፣ የቅድስት ሥላሴን አንድነትና ሦስትነት የሚያዛባ፣ ሥልጣነ ክህነትን የሚሽርና የማይቀበል፣ የቤተ ክርስቲያኗን ፊደልና ቁጥር አቆጣጠር የማይቀበል እንዲሁም፣ ቤተ ክርስቲያኗ የምትቀበላቸውን 81 መጽሐፍ ቅዱስ ወደ ጎን በመተው 66 መጻሕፍትን ብቻ ያካተተ በመሆኑ፣ እምነትን የሚያስክድ ነው፤ ይወገድልን፤” ብለዋል - ምዕመናኑ፡፡
መጽሐፍ ቅዱሱ ታትሞ በገበያ ላይ ከዋለ በኋላ፣ 92 በመቶ የሚሆነውን የክልሉን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ ግራ እያጋባ መሆኑንም ምዕመናኑ በማመልከቻቸው ጠቁመዋል፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱን ዶግማ ይፃረራል፤ የተባለው ይኸው መጽሐፍ ቅዱስ፣ ወደተለያዩ የከተማና እና የገጠር አብያተ ክርስቲያናት እንዳይሰራጭና

ዳግመኛም እንዳይታተም እንዲታዘዝላቸው ምዕመናኑ ጠይቀዋል። የትርጉሙን ስሕተት የሠሩ አካላትም ተጠያቂ እንዲሆኑና ርምጃ

እንዲወሰድባቸው ምዕመናኑ አያይዘው ጠይቀዋል።
በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ጠቅላይ ጸሐፊ፣ መምህር ይልማ ጌታሁን፣ ለመጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር በግልጽ የቀረበ

አቤቱታ እንደሌለ ገልጸው፣ አቤቱታ አቅራቢዎች ለቤተ ክርስቲያኒቱ ቅሬታ አቅርበው፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ ጉዳዩን እያየችው መሆኑን መረጃ

እንዳላቸው ጠቁመዋል፡፡
ትርጉሙ፣ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን ሊቃውንት በጥንቃቄ የተሠራ መሆኑን የጠቆሙት መምህር ይልማ፣ “ሥራው ስሕተት አለው ብለን አናምንም፤

አለው ቢባል እንኳ ሊቃውንቱን ነው መጠየቅ ይችሉ የነበረው፤” ብለዋል፡፡ የትርጉም ሥራው፣ በሊቃውንት ተመርምሮ ፓትርያርኩ ባሉበት

ተመርቆ እንዲሰራጭ መደረጉንም መምህር ይልማ አስረድተዋል፡፡
“ትርጉሞች፣ በቤተ ክርስቲያን ፈቃድና ተሳትፎ የሚሠሩ ናቸው እንጂ፣ ማኅበሩ በራሱ ተነሣስቶ የሚያደርገው አይደለም፤” ያሉት መምህር ይልማ፤

እስከ አሁንም፣ የትርጉም ስሕተት አለበት፤ የሚል ጥቆማ ለማኅበሩ እንዳልቀረበ አስታውቀዋል፡፡ 

   በሚያዚያ ወር በጥቅል ‹‹ሶስታ ሃሴት›› የሚል ሰያሜ የተሰጣቸው 3 ተከታታይ ሩጫዎች ተዘጋጅተዋል

       በተባበሩት መንግስታት አብይ ስፖንሰርነት ‹‹ስለምትችል››  በሚል መርህ ከሳምንት በፊት ለ14ኛ ጊዜ የተካሄደው  የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ስኬታማ እንደነበር የውድድሩ አስተባባሪ  ዳግማዊት አማረ ለስፖርት አድማስ ገለፀች፡፡
11ሺ ተሳታፊዎች የነበሩት የጎዳና ላይ ሩጫው መነሻ እና መድረሻው በመደበኛው  አትላስ ሆቴል  መመለሱ ድምቀት ፈጥሯል ያለችው ዳግማዊት፤  ሩጫው ከመጀመሩ በፊት እና ካበቃ በኋላ የነበረው አጠቃላይ ድባብ ያማረ ነበር ብላለች፡፡ ውድድሩ ከመጀመሩ በፊት ከ150 ዓመታት በፊት ስለነበረች የኢትዮጵያ ጀግና ሴት የተሰራው የቃቄ ውርድዎት  ቲያትር አንድ የተቀነጨበ ትዕይነት ለእይታ መቅረቡ፤ በሴቶች እየተዘወተረ የመጣው ታዋቂው የዙምባ ዳንስ ደስ የሚል ትርኢቶችን በመፍጠር ውድድሩን ማሟሟቁ፤ እንዲሁም ስለምትችል የሚለው መርህን በማንገብ የሴቶችን ስኬትና ሚና ለማክበር የተደረጉት እንቅስቃሴዎች ስኬታማ እንደነበሩም አብራርታለች፡፡
በ5 ኪ.ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫው በዋናው የአዋቂ አትሌቶች ውድድር አስደናቂ ውጤት የተመዘገበ ሲሆን በመሰረት ደፋር በባለቤቷ ቴድሮስ የሚንቀሳቀሰው የአዲዳስ  ዴፕሎፕመንት ፕሮጀክት ወጣት አትሌቶች ብዙም የውድድር ልምድ ባይኖራቸውም በአንደኛ እና  ሁለተኛ ደረጃ ውድድሩን በመጨረሳቸው ነበር፡፡ በ1ኛ ደረጃ የጨረሰችው የአዲዳስ ዴቨሎፕመንት አትሌት ደጊቱ አዝመራው ስትሆን ሌላዋ አጋሯ አበባ ተፈራ በሁለተኛ ደረጃ ተከትላ ገብታለች፡፡ ምህረት ተፈራ እና ብርሃን ምህረቱ ከሱር ኮንስትራክሽን 3ኛእና አራተኛደረጃ አግኝተዋል፡፡  በሌላ በኩል ከ35 ደቂቃ በታች 5 ኪሎሜትሩን ለሚጨርሱ  ስፖርተኞች ከሜዳልያ ሽልማት ባሻገር የአትሌት መሰረት ደፋር ፊርማ ያረፈበት 2000 ሰርተፍኬቶች ለሽልማት የቀረቡ ቢሆንም፤ በውድድሩ ላይ  ከ35 ደቂቃ በታች በመጨረስ የተሸለሙት 300 ብቻ ሆነዋል፡፡ በውድድሩ መነሻ ላይ በአንድ ጎዳና ላይ እጅብ ብሎ በመሮጥ የተፈጠረው  ግርግርና መጨናነቅ ብዙ ሴቶች ከ35 ደቂቃ በታች ውድድራቸውን እንዳይጨርሱ አድርጓቸዋል ብላለች፡፡ ዳግማዊት አማረ ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ  ፡፡ ከ30 በላይ ስፖርተኞችን ባሳተፈው የሴት ተምሳሌቶች  ውድድር የግሸን ፋርማሲ ባለቤት ወይዘሮ አማከለች ሉሉ ሲያሸነፉ በሁለተኛደረጃ የጨረሰችው ድምፃዊት ቤተልሄም ጌታሁን ወይም ቤቲ ጂ ነበረች፡፡ በአምባሳደርና የውጭ ዲፕሎማቶች ምድብ ደግሞ የስውድን አምባሳደር ባለቤት ሚስሪኮ ሜንሲያ  አሸንፈዋል፡፡    
ይህ በእንዲህ እንዳለ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከሚያዚያ 15  ጀምሮ  ባሉት ተከታታይ 3 እሁዶች የተለያዩ 3 ሩጫዎችን ማዘጋጀቱን ለስፖርት አድማ በላከው መግለጫ ያመለከተ ሲሆን ሶስቱ ተከታታይ ሩጫዎች በጥቅል ሶስታ ሃሴት (Triple Crown) የሚል ስያሜ ሰጥቷቸዋል፡፡ የመጀመርያው ሚያዚያ 15 የሚካሄደውና በአጠቃላይ 4000 ተሳታፊዎችን የሚያስተናግደው የሃዋሳው 2009 ሲሲኢሲሲ ሃዋሳ ግማሽ ማራቶን ሲሆን ይህ ሩጫ በውስጡ የ21 ኪ.ሜ.፤ የ7ኪ.ሜ እንዱሁም የህፃናት ሩጫ የሚያካትት ይሆናል፡፡  ሁለተኛው ውድድር
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከኢትዮጵያ ህክምና ባለሞያዎች ማህበር ጋር በመሆን የሚያዘጋጀው አመታዊው ኤማ ሩጫ  ሚያዚያ 22 ቀን ለ2ኛ ጊዜ ሲካሄድ  5000 ተሳታፊዎች ይኖሩታል፡፡
በመጨረሻም ሚያዚያ 29 ላይ የአውሮፓ ቀንን አስመልክቶ የሚዘጋጀው የአውሮፓ ቀን የህፃናት ሩጫ ሲሆን እድሜያቸው ከ3 አመት በላይ የሆኑ 3000 ህፃናት ወንዶችና ሴቶችን  የሚሳተፉበት ይሆናል፡፡

    በ12 ወራት 1 ቢ. ዶላር የከሰሩት ትራምፕ፣ ከአምናው ደረጃቸው በ220 ዝቅ

       ላለፉት ሶስት አመታት የአለማችን ቁጥር አንድ ቢሊየነር ሆነው የዘለቁት አሜሪካዊው የማይክሮሶፍት መስራች ቢል ጌትስ፣ ዘንድሮም የአለማችን ቁጥር አንድ ባለጸጋ መሆናቸውን ታዋቂው ፎርብስ መጽሄት በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ ይፋ ባደረገው የ2016 የፈረንጆች አመት የአለማችን ቢሊየነሮች ዝርዝር አስታውቋል፡፡
አምና በ75 ቢሊዮን ዶላር የተጣራ ሃብት የአለማችን ቀዳሚው ቢሊየነር የነበሩት ቢል ጌትስ፣ በአንድ አመት ውስጥ የሃብት መጠናቸው በ11 ቢሊዮን ዶላር በማደግ 86 ቢሊዮን ዶላር መድረሱንና ዘንድሮም በመሪነታቸው መቀጠላቸውን ያስታወቀው ፎርብስ፤ ቢል ጌትስ ካለፉት 23 አመታት በ18ቱ የአለማችን ቁጥር አንድ ቢሊየነር መሆን መቻላቸውንም አስታውሷል፡፡
አሜሪካዊው ዋረን ቡፌት በ75.6 ቢሊዮን ዶላር ሁለተኛው የአለማችን ባለጸጋ ሆነዋል ያለው መጽሄቱ፤ በአመቱ ከአለማችን ቢሊየነሮች ከፍተኛው የተባለለትን የ27.6 ቢሊዮን ዶላር የሃብት ጭማሪ በማስመዝገብ አጠቃላይ ሃብታቸው 72.8 ቢሊዮን ዶላር የደረሰላቸው የአማዞን ኩባንያ መስራች ጄፍ ቤዞስ ሶስተኛ ደረጃን መያዛቸውን አስረድቷል፡፡
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፖለቲካው የተጎናጸፉትን ድል በቢዝነሱ ለመድገም አልቻሉም ያለው ፎርብስ፤ ትራምፕ በአመቱ የሃብት መጠናቸው በ1 ቢሊዮን ዶላር ቅናሽ አሳይቶ 3.5 ቢሊዮን ዶላር በመድረሱ፣ አምና ከነበሩበት ደረጃ በ220 በማሽቆልቆል 554ኛ ደረጃ ላይ መቀመጣቸውን ገልጧል፡፡
በዘንድሮው የፎርብስ የቢሊየነሮች ዝርዝር ውስጥ በድምሩ 1 ትሪሊዮን ዶላር የተጣራ ሃብት ያላቸው 183 የቴክኖሎጂው ዘርፍ ባለጸጎች የተካተቱ ሲሆን፣ በ12 ወራት ጊዜ ውስጥ 11.4 ቢሊዮን ዶላር በማፍራት የሃብቱን መጠን 56 ቢሊዮን ዶላር ያደረሰው የፌስቡኩ መስራች ማርክ ዙክበርግ በአምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡
የአለማችን ቢሊየነሮች ብዛት አምና ከነበረበት የ13 በመቶ እድገት በማሳየት፣ 2 ሺህ 43 መድረሱን ያስታወቀው ፎርብስ፤አሜሪካ 565 ቢሊየነሮችን በዝርዝሩ ውስጥ በማካተት ቀዳሚነቱን መያዟን፣ ቻይና በበኩሏ 319 ቢሊየነሮችን በማስመዝገብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን ገልጧል፡፡
የሴት ቢሊየነሮች ቁጥር አምና ከነበረበት 202 ወደ 227 ማደጉ የተነገረ ሲሆን 39.5 ቢሊዮን ዶላር የተጣራ ሃብት ያላት ፈረንሳዊቷ ሌላኔ ቤቴንኮርት እንደ አምናው ሁሉ ዘንድሮም የአለማችን ቁጥር አንድ ሴት ቢሊየነር ሆናለች፡፡
በአመቱ ወደ ፎርብስ የቢሊየነሮች ዝርዝር የገቡ አዳዲስ ባለጸጎች ቁጥር 195 ሲሆን፣ አብዛኞቹ ቻይናውያን መሆናቸው ተነግሯል፡፡ በአንጻሩ ደግሞ፣ የሃብት መጠናቸው በማሽቆልቆሉና ከዚህ አለም በሞት በመለየታቸው ሳቢያ ከዝርዝሩ ውስጥ የተወገዱ ባለጸጎች ቁጥር 78 ነው ተብሏል፡፡
በዘንድሮው  የአለማችን ቢሊየነሮች ዝርዝር ውስጥ የተካተቱት 2 ሺህ 43 ቢሊየነሮች አጠቃላይ ድምር የተጣራ ሃብት 7.67 ትሪሊዮን ዶላር እንደሚደርስም ፎርብስ መጽሄት ሰኞ ዕለት ባወጣው መረጃ አስታውቋል፡፡

የሰሜን ኮርያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፣ አሜሪካ በሰሜን ኮርያ ላይ ወታደራዊ እርምጃ ልወስድ እችላለሁ  በሚል በይፋ ማስጠንቀቋ፣ አገራቸውን ፍርሃት ውስጥ እንደማይከታትና የኒውክሌርና የሚሳየል ፕሮግራሞቿን ከማካሄድ እንደማይገታት ማስታወቃቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰን ባለፈው አርብ በሰጡት መግለጫ፣ አገራቸው በሰሜን ኮርያ ላይ ጠበቅ ያለ ማዕቀብ እንደምትጥልና ወታደራዊ እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል ማስጠንቀቃቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ የሰሜን ኮርያው ቃል አቀባይ በበኩላቸው ለአገራቸው የዜና ወኪል በኩል በሰጡት ምላሽ፣ አገራቸው በአሜሪካ ዛቻ እንደማትደናገጥ መግለጻቸውን አስታውቋል፡፡
የሰሜን ኮርያ ኒውክሌር አገሪቱንና ህዝቦቿን ከጥፋት የሚታደግ ሁነኛ መሳሪያ ነው ያሉት ቃል አቀባዩ፤ ሰሜን ኮርያ ከአሜሪካ ሊቃጣባት የሚችልን ወታደራዊ ጥቃት በብቃት ለመመከት በሚያስችል ሁኔታ ኒውክሌር የታጠቀች አገር መሆኗን መሪዎቿ ሊገነዘቡ ይገባል ማለታቸውንም ዘገባው ገልጧል፡፡
ከንግድ ወደ ፖለቲካ ፊታቸውን ያዞሩት የአሜሪካ ባለስልጣናት፣ ሰሜን ኮርያን በዛቻና በማስፈራሪያ ትሸማቀቃለች ብለው የሚያስቡ ከሆነ ተሳስተዋል፤ መሳሳታቸውንም በቅርቡ ይገነዘባሉ ሲሉም አክለዋል፡፡
ምንም አይነት የኒውክሌርም ሆነ የሚሳኤል ሙከራ እንዳታደርግ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ክልከላ የተደረገባትና በኒውክሌር ፕሮግራሟ ሳቢያ ከአሜሪካ ጋር ግጭት ውስጥ የገባቺው ሰሜን ኮርያ፤ ባለፈው የፈረንጆች አመት ብቻ ለሁለት ጊዚያት የኒውክሌር ሙከራ ፍንዳታዎችን፣ ለ24 ጊዚያት ያህል ደግሞ የባለስቲክ ሚሳኤል ሙከራዎችን ማድረጓን ዘገባው አስታውሷል፡፡

 ከሰሞኑ ይፋ የተደረገው የ2017 የአለማችን አገራት የደስተኛነት ደረጃ ሪፖርት፣ ኖርዌይን ከ155 የአለማችን አገራት በቀዳሚነት ሲያስቀምጥ፣ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ደግሞ በመጨረሻ ደረጃ ላይ ትገኛለች ማለቱን ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል፡፡ ስድስት ያህል የአገራትን ማህበረ-ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ መመዘኛ መስፈርቶችን በመጠቀም በየአመቱ የአገራትን የደስተኛነት ደረጃ ይፋ የሚያደርገው ሰስቴኔብል ዲቨሎፕመንት ሶሊዩሽንስ ኔትወርክ የተባለው አለማቀፍ ተቋም፣ በ2017 ሪፖርቱ ዴንማርክን በሁለተኛ፣ አይስላንድን በሶስተኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧቸዋል፡፡
ስዊዘርላንድ፣ ፊላንድ፣ ኒዘርላንድስ፣ ካናዳ፣ ኒውዚላንድ፣ አውስትራሊያ እና ስዊድን ተከታዮቹን ደረጃዎች መያዛቸው የተነገረ ሲሆን፣ ዴንማርክ ለአራት አመታት የአለማችን ቁጥር አንድ ደስተኛ አገር ሆና መመዝገቧንም አስታውሷል፡፡
የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ዜጎች ጥናቱ ከተሰራባቸው 155 የአለማችን አገራት ህዝቦች ሁሉ በኑሯቸው የማይደሰቱ ህዝቦች ናቸው፤ አገሪቱም በአመቱ የአለማችን አገራት የደስተኛነት ዝርዝር ውስጥ የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች ያለው ሪፖርቱ፤ ብሩንዲና ታንዛኒያ እንደ ቅደም ተከተላቸው ከመጨረሻ ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጣቸውን አመልክቷል፡፡
የአገር ውስጥ ጠቅላላ ምርትና የነፍስ ወከፍ ገቢ፣ አማካይ በህይወት የመኖር ጣራ፣ የህይወት ምርጫን የማድረግ ነጻነትና የመሳሰሉት ጉዳዮች የአገራቱን የደስተኛነት ደረጃ ለመገምገም በጥቅም ላይ ከዋሉ መስፈርቶች መካከል ይጠቀሳሉ ያለው ሪፖርቱ፤ ደስተኛነት ገንዘብ የመያዝና ያለመያዝ ጉዳይ አይደለም፤ ለዚህም አንዳንድ ሀብታም አገራት ዝቅ ያለ የደስተኝነት ደረጃ ይዘው መገኘታቸው ማረጋገጫ ነው ብሏል፡፡

 ድንገተኛ እሳት በሚፈጥረው ኖት 7 ምርቱ የከፋ ቀውስ ውስጥ ገብቶ የከረመው ሳምሰንግ ኩባንያ፣ አዲሱን ስማርት ፎን ምርቱን ጋላክሲ ኤስ 8ን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ይፋ በማድረግ ለገበያ ያበቃል መባሉን ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግቧል፡፡
ሳምሰንግ ኩባንያ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውንና ከዚህ ቀደም ለገበያ ከቀረቡት የጋላክሲ ስማርት ፎኖች የተለየ ይዞታና ገጽታ ይኖረዋል የተባለውን አዲሱን ምርቱን ጋላክሲ 8ን እስከ ሚያዝያ ወር መጨረሻ ለገበያ እንደሚያበቃ የሚጠቁሙ መረጃዎች መውጣታቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ የመሸጫ ዋጋውም 799 ፓውንድ ይሆናል ተብሎ መገመቱን ገልጧል፡፡
ሳምሰንግ በጥቁር፣ በብርማ እና በሃምራዊ ቀለም እንደሚመረትና በካሜራ፣ በባትሪና በሌሎች ከዚህ ቀደም ከነበሩት ምርቶች የተለየ እንደሚሆን የተነገረለትን ይህን አዲስ የስማርት ፎን ምርቱን ለገበያ ለማብቃት ያቀደው ቀደም ብሎ ቢሆንም፣ በኖት 7 ምርቱ ሳቢያ የገባበት ቀውስ ዕቅዱን እንዲያራዝም እንዳስገደደው ዘገባው አስታውሷል፡፡
ኩባንያው ከጋላክሲ 8 በተጨማሪ ጋላክሲ 8 ፕላስ በሚል ስያሜ ያመረተውን አዲስ የስማርት ፎን ምርቱን ለገበያ ያበቃል መባሉን ያስታወቀው ዘ ኢንዲፔንደንት፤ የጋላክሲ 8 ፕላስ የመሸጫ ዋጋ ደግሞ 899 ፓውንድ ይደርሳል ተብሎ እንደሚገመት አብራርቷል፡፡

 የትንሳኤን በዓል ምክንያት በማድረግ በኢዮሃ አዲስ ኢንተርቴይመንትና ኤቨንት የተዘጋጀው  “ኢዮሃ ፋሲካ” ኤክስፖ ዛሬ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ይከፈታል፡፡
ኤክስፖው ሻጭና ገዢን ከማገናኘት ባለፈ ለ22 ቀናት የሙዚቃ ኮንሰርቶችን በወጣትና አንጋፋ ድምፃዊያን በማቅረብ የመዝናኛና የፌስቲቫል ድባብ እንዲኖረው መደረጉን የኢዮሃ አዲስ ኢንተርቴይመንትና ኤቨንት ዋና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ አዩ አለሙ ገልፀዋል፡፡
ከ400 በላይ የውጭ፣ 8 የአገር ውስጥ የንግድ ድርጅቶች ይሳተፉበታል የተባለው ይሄው ኤክስፖ፤አራት እውቅ ባንዶች የሚሳተፉበትና ከ100 በላይ ታዋቂ ዘፋኞች የሚያቀነቅኑበት የሙዚቃ ኮንሰርት፣ በዝነኛ ዲጄዎች የሚቀርብ ሙዚቃ፣ ከ80 በላይ ወጣቶችን የሚያሳትፍ  ዘመናዊና ባህላዊ የዳንስ ውድድር እንደሚቀርብበት ተጠቁሟል፡፡  
የፋሲካ ኤክስፖውን በየቀኑ ከ30 ሺህ በላይ፣ በጠቅላላ ግማሽ ሚሊዮን ህዝብ ይጎበኘዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ዋና ሥራ አስኪያጁዋ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡  
 ኢዮሃ አዲስ ኢንተርቴይመንትና ኤቨንት፤ በየቀኑ ወደ ኤክስፖው የሚመጡ ጎብኚዎች የሚገቡበትን ትኬት ቁጥር ለሽልማት ወደ 86 በአጭር መልዕክት በመላክ መኪና፣ ሞተር ሳይክልና ሌሎች ሽልማቶችን የሚያገኙበትን ዘመናዊ አሰራር ማመቻቸቱም ተነግሯል፡፡ የዚህን ዓመት የገና ኤክስፖ ጨምሮ ያለፈውን ዓመት የገናና የፋሲካ ኤክስፖዎች ያዘጋጀው ኢዮሃ፤ የዘንድሮን የፋሲካ ኤክስፖ ጨረታ በ13.6 ሚሊዮን ብር ማሸነፉ ታውቋል፡፡

ሩሲያ ካፈራቻቸው ታላላቅ የሥነ ጽሑፍ ሰዎች ውስጥ ገጣሚና ተርጓሚ የሆነችው ማሪና ኢቫኖቫ ስቬታየቫ አንደኛዋ ናት፡፡ ማሪና ኢቫኖቫ ሳይንስና የኪነ ጥበብ ዕውቀት ከአላቸው ቤተሰቦች ሞስኮ ውስጥ የተወለደቺው እ.ኤ.አ መስከረም 26 ቀን 1892 ዓ.ም ነው፡፡
ያረፈችው ደግሞ እ.ኤ.አ በ1941 ዓ.ም ላይ ነው። አባቷ ኢቫን ብላዲሚሮቪች ስቬታየብ የሞስኮ ዩኒቨርስቲ ፕሮፌሰር፣ የታወቀ ፈላስፋ፣ ዲሬክተርና የኪነ ጥበብ ሙዚየም መሥራች (በአሁኑ ሰዓት በፑሽኪን ስም በሚጠራው ከተማ የሚገኘው ሙዚየም) ነበር፡፡
ወላጅ እናቷ እመት ማሪያ ኔ ሜንም የተለየ ዕውቀት የነበራትና የኮንሰርት ፒያኖ ተጫዋች ነበረች፡፡
ማሪና ሞስኮ ውስጥ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን የተማረቺው በግል ት/ቤት ነው። በልጅነቷ ቤተሰቧ የተለያየ ጉብኝት ለማድረግ ወደ ጀርመን፣ ስዊዘርላንድነሰ ወደ ሶርቦን ፓሪስ በሚሄድበት ወቅት አብራ በመሄድ ትምህርቷን ትከታተልና ቋንቋም ታጠና ነበር፡፡ እ.ኤ.አ በ1908 ደግሞ በራስዋ ፍላጎት ወደ ፈረንሳይ (ፓሪስ) ሄዳ ሶርቦን ውስጥ የጥንት ፈረንሳይኛ ሥነ ጽሑፍ ኮርስ መከታተል ጀመረች፡፡ በ16 ዓመቷ ግጥም መግጠም የጀመረቺው ስቤታየቫ፤ 18 ዓመት ሲሞላት ወደ ሩሲያ ተመልሳ የመጀመሪያዋ የሆነ የሥነ ግጥም ስብስብ መጽሐፍ ‹‹ የምሽት አልበም›› (EVENING ALBUM) በሚል ርዕስ አሳተመች። በኋላም ማለት እ.ኤ.አ በ1912፣በ1913፣በ1916 ዓ.ም የተጋጋለ ውስጣዊ ስሜቷንና የሩሲያን ነባራዊ ሁኔታ የሚያንፀባርቁ ሌሎች ሥራዎቿን ለህትት አበቃች፡፡ በተለይም “ከፍታ” የተሰኘው ግጥሟ ለሩሲያና ለሩሲያ ገጣሚዎች የተበረከተ ሲሆን ኩራትን፣ ጀግንነትን፣ የበለፀገ እውቀትንና ፍፃሜ የሌለው ስሜትን ያመለክታል፡፡
‹‹የምሽት አልበም›› የሚለው ግጥም ስለ ልጅነቷና ስለ ወጣትነቷ ዘመን ያትታል፡፡ ማስታወሻ አድርጋ ያበረከተችውም ለዚሁ ዘመኗ ነው፡፡
እ.ኤ.አ በ1912 ዓ.ም ማሪና ሰርጌይ ኢፎርን የተባለና የዛሩ መንግሥት ወታደር የነበረ ሰው አግብታ ሁለት ሴቶችንና አንድ ወንድ ልጅ ወልዳለች፡፡ የማሪና ሰቬተየቫ ሕይወት ከሩሲያ አብዮት ጋር የያያዘ ነበር፡፡ ባለቤቷ ኢፎርን ነጩ ጦር (the white guard) እየተባለ ከሚታወቀው የዛሩ መንግሥት ጦር ሰራዊት ጋር ተሰልፎ አብዮተኞችን/ ሶቭየቶችን ወይም ቦልሸቪኮችን/ ሲወጋ ነበር፡፡
ማሪና ‹‹ገርልፍሬንድ›› በሚለው ግጥሟ ተደንቃና ተመስጣ ገጣሚና የኦፔራ ቲአትር ባለሙያ ከሆነችው ከሶፍያ ፓሞክ ጋር ተዋወቀች። ምክንያቱም ሶፍያ ፓሞክ በወቅቱ በዚህ ግጥሟ ዝናን አትርፋ ነበር፡፡ ቀጥላም በዛሩ ዘመነ መንግሥት የቀይ ጦር ሽምቅ ታዋጊ ወታደር ከነበረና ኮንስታንቲን ፎዜቪች ከተባለ ገጣሚ ጋር ትውውቅ አደረገች፡፡ ኮንስታንቲን ‹‹የተራራ ግጥሞች›› እና ‹‹ የመጨረሻ ግጥሞች›› የተሰኙ ሥራዎች ስለነበሩት እነዚህን አንብባ አድናቆቷን ገለጸለችለት፡፡
እ.ኤ.አ በ1917 የኦክቶቨር ሪቮሉሽን ወቅት ተይዛ ለ5 ዓመት ታሥራለች፡፡ ከአብዮቱ ጋር በተያያዘ በተከታታዮቹ ዓመታት ድርቅና ረሀብ በሩሲያ በተከሰተበት ወቅት አንደኛዋ ሴት ልጇ በረሀብ ምክንያት ሞታበታለች፡፡
እ.ኤ.አ በ1922 ዓ.ም ማሪና ባለቤቷንና ቤተሰቧን ይዛ ወደ በርሊን፣ ከዚያም ወደ ፕራግ፣ ቀጥላ በ1925 ወደ ፓሪስ ተሰደደች፡፡ በፓሪስ የሩሲያ ማኅበረሰብ አባላት ጋርም መኖር ጀመረች። ነገር ግን አብዛኞቹ ስደተኞች የቀድሞው የዛር መንግሥት ወታደሮች ስለነበሩ የማሪና ባለቤት ሰርጌይ ኢፎርን የቦልሸቪኮች ሰላይ ሳይሆን አይቀርም ብለው ስለገመቱ እርሱን መፍራት ጀመሩ፡፡ በኋላም ነገሩ እውነት ሆኖ ተገኘ፡፡ ከጊዜ በኋላ ሰርጌይ ኢፎርን ወደ ሩሲያ ተመለሰ፡፡ ሞስኮ እንደደረሰም ታሥሮ ከቆየ በኋላ ተገደለ፡፡ ማሪና በስደት ዘመኗ ወጎችንና የትረካ ሥራዎችን ደርሳ ለማሳተም ችላለች፡፡ የአብዛኞቹ ግጥሞቿ ጭብጥ የሚነሳው ከአፈ-ታሪክና ከኅብረ ዝማሬ ሲሆን የአገጣጠም ስልቱ ደግሞ በታላቁ ሩሲያዊ ገጣሚ በአሌክሳንደር ብሎክና በታላቂቱ የኪነ ጥበብ ሰው በአና አህማቶቫ የአጻጻፍ ቴክኒክ የተቃኘ ነው፡፡ በሥራዎቿ ውስጥ የሩሲያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖትና ጸሎተኞች፣ የእምነት ዕሴቶች ከዘመናዊ አስተሳሰብ ጋር ተቃኝተው ይታያሉ፡፡
ማሪና ከብዙ ነገር ተገልላና ብቸኛ ሆኖ በስደት ብትቀመጥም የነፍስ ጥሪዋን ግን አልረሳችም። በከፍተኛ ስሜት ተነሳስታ ብዙ የጻፈችው በስደት ጊዜዋ ነው፡፡ ‹‹መለያየት››፣ ‹‹ንግድ››፣ ‹‹ሥነ ልቡና››፣ ‹‹ከሩሲያ በኋላ››፣ ‹‹ይድረስ ለልጄ››፣ ‹‹የአገር ናፍቆት››፣ ‹‹ቼቺያ›› /በወቅቱ ፖለቲካ ላይ የሚያተኩር ሥራ / የተባሉትን ሥራዎች ደርሳ ያሳተመቻቸው በስደት ዘመኗ ነው፡፡ ከማሪና ታላላቅ የግጥምና የልቦለድ ሥራዎች ውስጥ
በፖሪስ ውስጥ፣ ጸሎተኛው፣ ለእናቴ፣ ስብሰባ፣ ኒና ይቅርታ አድርጊልኝ … የሚሉት ይጠቀሳሉ፡፡
ማሪና እ.ኤ.አ ከ1939 ዓ.ም ጀምራ ወደ ሀገሯ በመመለስ ሞስኮ ውስጥ ለመኖር ብትፈልግም በፖለቲካ አመለካከቷ ምክንያት የሥነ ጽሑፍ አፍቃርያንና በማኅበረሰቡ ዘንድ የተገለለች ሆነች። ከዚህም የተነሣ እ.ኤ.አ በ1941 ዓ.ም ራስዋን አጥፍታለች፡፡
ታላቁ ገጣሚ ቦሪስ ፖስተርናህ አሟሟቷን አስመልክቶ ሲናገር፡-
‹‹ማሪናን ቀደም ብሎ የሥነ ጽሑፍ ቢሮክራቶች ልበቢስ በሆነ መንገድ ባይቀርቧት ኖር ራስዋን አታጠፋም ነበር›› ብሏል፡፡
የጽሑፍ ሥራዎቿ የሰላ አእምሮ፣ በጥልቀት የሚያይ ዐይንና አስተዋይ ልቡና የነበራት ታላቅ ሴት የነበረች መሆኗን አስመስክረዋል፡፡
በ20ኛው ክፍለ ዘመን በወጥነት ከቀረቡት የግጥም ሥራዎች ውስጥ የማሪና ስቤታየቫ በዋነኛነት ይጠቀሳል፡፡ የእርስዋ የሥነ ግጥም ምንጭ የፈለቀው ተቃርኖ ከበዛበት የግል ሕይወቷ ነው፡፡ የቋንቋ አጠቃቀሟ የተመጠነ፣ በጥቂት ቃላት ብዙ የምትናገርነ ገጣሚ ናት፡፡ በጭብጥ ረገድ ካነሳቻቸው በርካታ ርእሰ ጉዳዮች ውስጥ የሚበዛው ሴታዊነት፣ ወሲብ፣ የሴቶች ግላዊ ሕይወትና በማኅበራዊ ኑሮ ስለአላቸው ሚና ነው፡፡
ለማሪና ስቬታየቫ በአሁኑ ሰዓት የሩሲያ መንግሥት በመኖሪያዋ አካባቢ በሚገኘውና ቦሪስግሌቭስኪ ተብሎ በሚጠራው ሠፈር ሐውልት አቁሞላታል፡፡

Monday, 27 March 2017 00:00

አንብባችሁ እንድትስቁ!!

  አባት ሰዎች ሲዋሹ በጥፊ የሚማታ ውሸት የሚለይ ሮቦት ይገዛል፡፡
አንድ ማታ እራት ላይም ሮቦቱን ሊሞክረው ይወስናል፡፡.
አባት ልጁ ከሰዓት በኋላ ምን ሲሰራ እንደነበር ይጠይቀዋል፡፡
ልጅም “የቤት ሥራ ስሰራ ነበር” ይላል፡፡
ሮቦቱ ልጁን ጥፊ ያቀምሰዋል፡፡
ዋሽቷል ማለት ነው፡፡
“እሺ--እሺ--ጓደኛዬ ቤት ፊልም ስመለከት ነበር” ብሎ ንግግሩን ያርማል፡፡
“ምን ዓይነት ፊልም ነው ስትመለከቱ የነበረው?” አባት ይጠይቃል፡፡
ልጅም፡- “የካርቱን ፊልም”
ሮቦቱ ልጁን በጥፊ ይመታዋል፡፡
“በቃ የወሲብ ፊልም ነው” ይላል ልጅ፡፡
አባትም፡- “ምን አልክ?
እኔ እኮ ባንተ ዕድሜ ወሲብ ምን እንደሆነ እንኳን አላውቅም”
ሮቦት ቀልድ አያውቅም፤ አባትየውን በጥፊ፡፡
እናት ሳቀችና፡- “የአባቱ ልጅ! በራስህ ነው የወጣው” አለች፤ ሳይቸግራት፡፡
ሮቦቱ እናትየውንም በጥፊ አቀመሳት፡፡
ወዲያው ሮቦቱ እንዲሸጥ ተፈረደበት፡፡
***
አንድ ቀን ፈጣሪ ወደ አዳም ዘንድ ብቅ ብሎ፤
“ጥቂት መልካም ዜናና ጥቂት መጥፎ ዜና ልነግርህ ነው የመጣሁት” ይለዋል፡፡
አዳምም ፈጣሪውን ትክ ብሎ ተመለከተና፤ “እንግዲያውስ መልካሙን ዜና አስቀድምልኝ” አለው፡፡
ፈጣሪም ፈገግ አለና ጉዳዩን ማብራራት ጀመረ፡-
“ሁለት አዳዲስ የአካል ክፍሎችን (ኦርጋን) ይዤህልህ መጥቼአለሁ፡፡
 አንደኛው አዕምሮ ይባላል፡፡
በጣም ብልህ እንድትሆን ያደርግሃል፤ አዳዲስ ነገሮችን ለመፍጠርና ከሄዋን ጋርም በአስተውሎት እንድታወጋ ይረዳሃል፡፡
ሌላኛው ያመጣሁልህ የአካል ክፍል ደግሞ ብልት ይባላል፡፡
እንደ ራስህ ብልህ የሆነ አዲስ ህይወት ለመፍጠርና እቺን ፕላኔት በዘርህ ለመሙላት ያስችልሃል፡፡
ለሄዋንም ልጆች ስለምታፈራላት ደስታዋ ይጨምራል፡፡”
አዳምም በደስታ ተጥለቅልቆ የሚሰራው የሚያደርገው ጠፋው፡፡
“በጣም ድንቅ ስጦታዎችን ነው ያበረከትክልኝ፤ ከዚህ ዕጹብ ድንቅ ገጸ በረከት በኋላ ምን ዓይነት መጥፎ ዜና ልትነግረኝ እንደምትችል አይቼ?” አለው ፈጣሪን፡፡
ፈጣሪም፤ “መጥፎው ዜና ምን መሰለህ፣ ስፈጥርህ የሰጠሁህ የደም መጠን እነዚህን ሁለት አካላት (ኦርጋንስ) በአንድ ጊዜ ማሰራት የሚችል አይደለም፤ተራ በተራ እንጂ” አለው በሃዘን ስሜት ተውጦ፡፡
(አንዱ ኦርጋን ሲሰራ አንዱ ሥራ ያቆማል)
*   *   *
ቀኑን ሙሉ የቢራ አምራቾች ጉባኤ ሲካሄድ ይውላል፡፡
ጉባኤው ሲጠናቀቅ የሁሉም ኩባንያዎች ፕሬዚዳንቶች ወደ አንድ መጠጥ ቤት ጎራ ብለው ቢራ ለመጎንጨት ይስማማሉ፡፡
የበድዋይዘር ቢራ ፕሬዚዳንት በድዋይዘር ያዝዛል፡፡ የሚለር ቢራ ፕሬዚዳንትም ሚለር ያዝዛል።
የኩርስ ቢራ ፕሬዚዳንት እንዲሁ ኩርስ ቢራ ያዝዛል፡፡
በመጨረሻም አስተናጋጇ የጊነስ ቢራ ባለቤትና ፕሬዚዳንት የሆነውን አርተር ጊነስን ምን እንደሚጠጣ ትጠይቀዋለች፡፡ ሚስተር ጊነስም፤ “ኮካኮላ” በማለት ሁሉንም አስገረማቸው፡፡
“ጊነስ ቢራ ለምን አላዘዝክም?” ሲሉ ጠየቁት ባልደረቦቹ፡፡
እሱም፡- “እናንተ ቢራ ካልጠጣችሁ እኔም አልጠጣም” ሲል መለሰላቸው፡፡
(ቀላል ነገራቸው!)
*   *   *
አንድ አዲስ አስተማሪ ወደ ክፍል እየገባች ሳለ፣በሳይኮሎጂ ኮርስ የተማረችውን በጥቅም ላይ ለማዋል አሰበች፡፡
እናም የዕለቱን የትምህርት ክፍለ ጊዜ እንዲህ በማለት ጀመረች፡-
“በዚህ ክፍል ውስጥ ደደብ ነኝ ብሎ የሚያስብ ሁሉ ተነስቶ ይቁም”
ከጥቂት ሰከንዶች በኋላ ህጻኑ ጆኒ ተነስቶ ይቆማል፡፡
አስተማሪዋም፡- “ጆኒ፤ ደደብ ነኝ ብለህ ታስባለህ?; ጠየቀችው፡፡
“በጭራሽ፤ እርስዎ ብቻዎን መቆምዎ አናዶኝ ነው”
*   *   *
ችግሩ ያለው ማ ጋ ነው?
ሰውየው ሃኪሙ ዘንድ ይሄድና፡-
“የሚስቴ የመስማት አቅም የደከመ ይመስለኛል፤ እንደ ድሮው አይደለም፤ ምን ባደርግ ይሻለኛል?” ሲል ምክር ይጠይቀዋል፡፡
ሃኪሙም፡- “እርግጠኛ ለመሆን ይህን ሞክር፤ ሚስትህ ወጥ ቤት ሆና ምግብ ስታሰናዳ ከኋላዋ 15 ጫማ ርቀት ላይ ሆነህ የሆነ ነገር ጠይቃት፡፡ መልስ ካልሰጠችህ እየቀረብካት መልስ እስክትሰጥህ ድረስ መጠየቅህን ቀጥል” አለው፡፡
ሰውየው ወደ ቤቱ ተመለሰና ሚስቱ እራት ማዘጋጀት ስትጀምር የተባለውን ይሞክር ገባ፡፡
ከኋላዋ 15 ጫማ ርቀት ላይ ቆሞ፤ “ማሬ፤ ዛሬ እራታችን ምንድን ነው?” ሲል ጠየቃት፡፡ ነገር ግን ከሷ ምላሽ አላገኘም፡፡ 10 ጫማ ተጠግቶ በድጋሚ ሚስቱን ጠየቃት፡፡
አሁንም መልስ የለም፡፡
5 ጫማ ቀረበና ጥያቄውን አቀረበ፡፡
ግን ምላሽ አላገኘም፡፡
በመጨረሻ ከኋላዋ ቆሞ፤
“ማሬ÷ዛሬ እራታችን ምንድን ነው?” አላት፡፡
ሚስትም ፡-
“ለአራተኛ  ጊዜ   እነግርሃለሁ፤  
ዶሮ ነው!” አለችው፡፡
ችግሩ ያለው ማ ጋ ነው ? ከእሱ ወይስ ከእሷ?
*   *   *
አንዲት በመካከለኛ ዕድሜዋ ላይ የምትገኝ ሴት በድንገተኛ የልብ ህመም ራሷን ስታ ሆስፒታል ትገባለች፡፡
የቀዶ ህክምና እየተደረገላት ሳለም ነፍሷ ከስጋዋ ተለይታ ሰማይ ቤት ትሄዳለች፡፡
እዚያም እግዚአብሄርን ታገኘውና፤ “ቀኔ ደርሷል እንዴ?” ስትል ትጠይቀዋለች፡፡
እግዚአብሄርም፡- “አልደረሰም ገና 40 ዓመት ከ4 ወር ይቀርሻል” ይላታል፡፡
ከህመሟ ስታገግም ታዲያ እዚያው ለመቆየት ትወስንና የፕላስቲክ ቀዶ ህክምና እንዲሰራላት ትጠይቃለች፡፡
ብዙ ዕድሜ ስለሚቀራት ዓለሟን ልታይ ተመኝታለች፡፡
እናም ፊቷን አስቀየረች፣ ቦርጯን አስቀነሰች፣ ዳሌዋን ማራኪ እንዲሆን አድርጋ አሰራች፡፡
የጸጉሯንም ቀለም አስቀየረች፡፡
የማታ ማታም አንድ ፍሬ ኮረዳ መስላ ቁጭ አለች፡፡
የምትሻውን መልክና ገጽታ ከተጎናጸፈች በኋላ በደስታ ተጥለቅልቃ ከሆስፒታሉ ወጣች፡፡
ነገር ግን ወደ ቤቷ እየሄደች ሳለ መንገድ ስትሻገር አምቡላንስ ገጭቷት ትሞታለች፡፡
ለሁለተኛ ጊዜ ከእግዚአብሄር ጋር ስትገናኝም፡-
“ሌላ 40 ዓመት ይቀርሻል ብለኸኝ አልነበር፤ ለምን ከአምቡላንሱ አደጋ አላተረፍከኝም?” ስትል ተቆጥታ ጠየቀችው፡፡
እግዚአብሄርም መለሰላት፡-
“አዝናለሁ፤ አንቺ መሆንሽን አላወቅሁም ነበር”
*   *   *
ሰውየው የቅርብ ጓደኛው ሚስት ሞታ ሊያስተዛዝነው ወደ ቤቱ ይሄዳል፡፡
በሩን ቢቆረቁር ግን የሚከፍትለት ያጣል፡፡ ምን ተፈጠረ በሚል ስጋት በሩን ገፋ አድርጎ ይገባል፡፡
ጓደኛውን ያገኘው ግን ከሌላ ሴት ጋር ሲሳሳም ነበር፡፡
“ጃክ” አለ ሰውየው በመገረም ተሞልቶ÷ “ሚስትህ እኮ ከሞተች ገና 24 ሰዓት አልሞላትም”
ጓደኝየው ቀና ብሎ ተመለከተውና፤ “በዚህ ሃዘን ውስጥ ሆኜ የምሰራውን የማውቅ ይመስልሃል?” አለው፡፡
*   *   *
ባል፡- ሎተሪ ቢደርሰኝ ምን ታደርጊያለሽ?
ሚስት፡- ግማሹን ወስጄ የራሴን ህይወት ለብቻዬ እጀምራለሁ
ባል፡- ይኸውልሽ 100 ዶላር ደርሶኛል፤እባክሽን 50 ዶላርሽን ውሰጂና አሁኑኑ ሂጂልኝ!
*   *   *
የሰላዮች ፈተና -----
የጀርመን፣ የጣሊያንና የሩሲያ ሰላዮች በሥራ ላይ ሳሉ በቁጥጥር ስር ይውሉና ምርመራ ይደረግባቸዋል፡፡
የታሰሩት መስኮት በሌለው ጠባብ ወህኒ ቤት ውስጥ ሲሆን ምግብ የሚሰጣቸው ነፍሳቸውን ለማቆየት ያህል ብቻ ነበር፡፡
መጀመሪያ ለምርመራ የተጠራው የጀርመኑ ሰላይ ነው፡፡
እጆቹ ታስረውና ወንበር ላይ ተቀምጦ ነበር የተመረመረው፡፡
ለሁለት ሰዓት ያህል ድብደባና ስቃዩን ችሎ ለማን እንደሚሰራ ሳይናገር ከቆየ በኋላ የማታ ማታ ተረታ፡፡
ወደ እስር ክፍሉ ሲመለስ ግን ሌሎቹ ሰላዮች ይሄን ያህል ሰዓት መከራውን ችሎ በመቆየቱ አደነቁት፡፡
በመቀጠል የሄደው የሩሲያው ሰላይ ነበር፡፡ እሱ ደግሞ ለ12 ሰዓታት ከፍተኛ ድብደባና ስቃይ ከደረሰበት በኋላ ለማን እንደሚሰራ ተናገረ፡፡ ወደ እስር ክፍሉ ሲመለስም ለዚያ ሁሉ ሰዓታት በጽናት በመቆየቱ ሌሎቹ ሰላዮች በእጅጉ ተደመሙበት፡፡
በመጨረሻም ጣሊያናዊው ሰላይ ወደ ምርመራ ክፍሉ ተላከ፡፡ እጁን ታስሮ ለ4 ቀናት እየተደበደበ ቢሰቃይም ለማን እንደሚሰራ ትንፍሽ ሳይል ወደ እስር ክፍሉ ተመለሰ፡፡ ሌሎቹ ሰላዮች እንዴት ለ4 ቀናት ሳይናገር መቆየት እንደቻለ ጠየቁት፡፡
እሱም፤ “ለመናገር እኮ ሞክሬ ነበር፤ነገር ግን እጆቼን ማንቀሳቀስ አልቻልኩም; አላቸው፡፡
(ጣልያን እጆቹን ካላንቀሳቀሰ ማውራት አይችልም ይባል የለ!)
*   *   *
አባት፡-እኔ የመረጥኩልህን ሴት እንድታገባ እፈልጋለሁ
ልጅ፡- አላደርገውም!
አባት፡- የቢል ጌትስ ልጅ እኮ ናት
ልጅ፡- እንደሱ ከሆነ እሺ
አባት ወደ ቢል ጌትስ ዘንድ ይሄዳሉ፡፡
.አባት፡- ልጅህ ልጄን እንድታገባው እፈልጋለሁ
ቢል ጌትስ፡- ፈጽሞ አይሆንም!
አባት፡- ልጄ እኮ የዓለም ባንክ ዋና ሃላፊ ነው
ቢል ጌትስ፡- እንዲያ ከሆነ እሺ
አባት የዓለም ባንኩ ፕሬዚዳንት ዘንድ ይሄዳሉ፡፡
አባት፡- ልጄን የባንኩ ዋና ሃላፊ አድርገህ ሹምልኝ
ፕሬዚዳንቱ፡- የማይሞከረውን!
አባት፡- ልጄ እኮ ያገባው የቢል ጌትስን ልጅ ነው
ፕሬዚዳንት፡- እንደሱ ከሆነ ይቻላል!
ይሄ ነው እንግዲህ ቢዝነስ ማለት!
*   *   *
አንድ ሩሲያዊ አሜሪካ ኤርፖርት ውስጥ ከቀረጥ ነጻ (duty free shop) መደብር ጎራ ይላል፡፡
የመደብሩን አስተናጋጅም፤ “የሩሲያ ቋንቋ ትችያለሽ?” ሲል ይጠይቃታል፡፡
“አዎ፤ ትንሽ ትንሽ እችላለሁ” መለሰችለት፡፡
ሩሲያዊው “እፎይ” አለና “ማርልቦሮ” አላት፡፡
(ለዚሁ ነው በሬዬን ያረድኩት አለ አበሻ!)
*   *   *
በሩሲያ የት/ቤት ክፍል ውስጥ ነው አሉ፡፡
አስተማሪ፡- ጎበዝ ልጆች ያሉት የት ነው?
ተማሪዎች፡- በሩሲያ!
አስተማሪ፡- ጣፋጭ ከረሜላዎች የት ነው የሚመረቱት?
ተማሪዎች፡- በሩሲያ!
አስተማሪ፡- ምርጥ ከተሞች የት ነው ያሉት?
ተማሪዎች፡- በሩሲያ!
ድንገት በክፍሉ ውስጥ ካሉት ተማሪዎች ትንሷ ናድያ ማልቀስ ጀመረች፡፡
አስተማሪው፡- ናድያ፤ ለምንድን ነው የምታለቅሺው?
ናድያ፡- ሩሲያ የምትባለው አገር መኖር እፈልጋለሁ!
(እኔም ሁሌ የኢቢሲ ጦቢያ ትናፍቀኛለች!)
*   *   *
ወህኒ ቤት ወይስ ት/ቤት?
ቻይና ውስጥ ነው አሉ፡፡ የሆነ ፕሮጀክት ተሰርቶ ከተጠናቀቀ በኋላ በዛ ያለ ገንዘብ ይተርፋል፡፡ የአካባቢው ቋሚ ኮሚቴ ተሰብስቦ የተረፈው ገንዘብ የአንደኛ ደረጃ ት/ቤትን ለማደስ ይዋል ወይስ ወህኒ ቤት ይታደስበት በሚለው ላይ ይወያያል፡፡ ነገር ግን ወደ አንድ ውሳኔ ለመምጣት አልተቻለም፡፡
በመጨረሻ ግን አንድ በቋሚ ኮሚቴው ውስጥ ለረዥም ጊዜ በአባልነት የቆዩ ሰው ሁሉንም ያስገረመ አስተያየት ሰነዘሩ፡- “በዚህ ዕድሜያችን የአንደኛ ደረጃ ትምህርት የመከታተል ዕድል እናገኛለን እንዴ?”
ለአፍታ ዝምታ ነገሰ፡፡
ከፊሉ ሻይ መጠጣት፣ ከፊሉ ደግሞ ከቅንድቡ ላይ ላቡን መጠራረግ ያዘ፡፡ ከዚያም ሁሉም አባላት “ወህኒ ቤት ይታደስበት” በሚለው ተስማሙ፡፡
(ከዕለታት አንድ ቀን ሁሉም ወህኒ ቤት መግባታቸው አይቀርማ!)
*   *   *
ብላክሜይል!
ትንሹ ሳሚ ለገና ቢስክሌት እንዲገዛለት ለእናቱ ጥያቄ ያቀርባል፡፡ እናቱም ለአባ ገና ደብዳቤ ቢጽፍላቸው እንደሚሻል ትነግረዋለች፡፡ ሳሚ ግን ደብዳቤውን ለህጻኑ ኢየሱስ ብጽፍ እመርጣለሁ አለ፡፡
እናቱም በዚሁ ሃሳብ ተስማማች፡፡
ሳሚ ወደ ክፍሉ በመግባትም እንዲህ ሲል
ጻፈ፡- “ውድ ኢየሱስ፤ በጣም ጥሩ ልጅ ስለሆንኩ ለገና ቢስክሌት እፈልጋለሁ፡፡”
ሆኖም የጻፈውን ደግሞ ሲያነበው ብዙም ሳያስደስተው ቀረ፡፡ ስለዚህም እንደገና ለመጻፍ ሞከረ፡- “ውድ ኢየሱስ፤ አብዛኛውን ጊዜ ጥሩ ልጅ ነኝ፤ እናም ለገና ቢስክሌት እፈልጋለሁ፡፡”
አሁንም ግን ሲያነበው አላስደሰተውም፡፡
ለሦስተኛ ጊዜ ለመጻፍ ሙከራ
አደረገ፡- “ውድ ኢየሱስ፤ አዲስ ቢስክሌት ካገኘሁ ጥሩ ልጅ ለመሆን እሞክራለሁ”
ይሄኛውም የልቡን አላደረሰለትም፡፡
በመጨረሻ የተሻለ ሃሳብ ለማመንጨት በማሰብ፣ ከቤቱ ወጥቶ በእግሩ መጓዝ ይጀምራል፡፡ ጥቂት እንደተጓዘም አንድ መኖሪያ ቤት በረንዳ ላይ በነሀስ የተሰራ ትንሽዬ የድንግል ማርያም ምስል (ቅርጽ) ተሰቅሎ ይመለከታል፡፡ አንድ ሃሳብ ከመቅጽበት ብልጭ አለለት፡፡ ሳሚ በቀጥታ ወደ ቤቱ ያመራና የማርያምን ምስል ከተሰቀለበት አውርዶ ኮቱ ውስጥ በመሸሸግ በጥድፊያ ወደ ቤቱ ያመራል፡፡ እክፍሉ ውስጥ ገብቶም አልጋው ስር ይደብቀዋል፡፡
ከዚያም የሚከተለውን ደብዳቤ ጻፈ፡- ”“ውድ ኢየሱስ፤ እናትህን ዳግም ማየት የምትፈልግ ከሆነ አዲስ ቢስክሌት ላክልኝ”
*   *   *
ቀናተኛዋ ሚስት!
ሚስት በሥራ ላይ ለሚገኘው ባሏ ስልክ ለመደወል ትሞክርና ሞባይሏ ሂሳብ እንደሌለው ትረዳለች፡፡
ወዲያው ትንሹ ልጃቸው በራሱ ሞባይል አባቱ ጋ ደውሎ የፈለገችውን አስቸኳይ መልዕክት እንዲያደርስ ታዘዋለች፡
ከጥቂት ደቂቃ በኋላ ልጅ ለእናቱ እንዲህ ይላታል፤ “ሶስት ጊዜ ደውዬ ሴት ነው ያነሳችው”
ሚስት ባሏ እስኪመጣ መታገስ አቅቷት በንዴት ስትንቆራጠጥ ትቆይና የመኪናውን ድምጽ ስትሰማ ከቤት ዘላ ትወጣለች፡፡ ከመኪናው ሲወርድ ጠብቃም ምንም ሳትናገር ጥፊ ታቀምሰዋለች፡፡
ባል ተደናግጦ ምክንያቱን ሊጠይቃት ሲል ሌላ ጥፊ ትደግመዋለች፡፡
በዚህም ጠብ ይነሳና ጎረቤት ይሰባሰባል፡፡
ይሄኔ ወደ ልጇ ዞር ትልና አባቱ ጋ ሲደውል ያነሳችው ሴትዮ ምን እንዳለችው ለተሰበሰበው ሰው እንዲናገር ትጠይቀዋለች፡-
ልጁም እንዲህ አለ፡-
“የደወሉላቸው ደንበኛ ከአገልግሎት ጥሪ ውጭ ስለሆኑ እባክዎ ትንሽ ቆይተው ይሞክሩ”
(ሚስት እንዴት ታፍር!