Administrator

Administrator

የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አመራሮች፣ ሰራተኞችና ሠልጣኝ የበጎ ፈቃድ ዲፕሎማቶች በአዲስ አበባ ከተማ የተገነቡና አሁን በመገንባት ላይ የሚገኙ የአዲስ አፍሪካ አለም አቀፍ ኤግዚቢሽንና ኮንቬንሽን ማዕከል፣ የአድዋ ድል ሙዚየምንና የኮረደር ልማት ስራዎችን ሰሞኑን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ጉብኝት ብቻም አይደለም፡፡ “በአዲስ አበባ ከተማ የተሰሩ ግዙፍ ስራዎች” በሚል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ እናትዓለም መለሰ ተሰጥቷቸዋል፡፡
የስልጠናው ዓላማ በተለይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የበጎፈቃድ ዲፕሎማቶች በመዲናዋ የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ለውጭው ዓለም በማስተዋወቅ የሃገርን ገጽታ በመገንባት ረገድ የበኩላቸውን እንዲወጡ ለማስቻል ነው፡፡ ከእነዚህ ግዙፍ ፕሮጀክቶች አንዱ ደግሞ የመጀመሪያ የሥራው ምዕራፍ በመገባደድ ላይ የሚገኘው የአዲስ አፍሪካ ዓለማቀፍ ኮንቬንሽንና ኤግዚቢሽን ማዕከል ነው፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አበቤ ስለማዕከሉ ሲናገሩ፤ አዲስ አበባ የዓለም ዓቀፍ ኤግዚቢሽኖችና ጉባኤዎች መነሃሪያነቷን የምናረጋግጥበት፣ የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማዕከልነቷን በኩራት የምንመሰክርበት ይሆናል ነው ያሉት፡፡
የዛሬ ጽሁፋችን የአዲስ አፍሪካ ዓለማቀፍ ኤግዚቢሽንና ኮንቬንሽን ማዕከል ላይ የሚያተኩር ቢሆንም፣ በቀጥታ ወደዚያ ከመሻገራችን በፊት ግን ዓለማቀፍ ተሞክሮዎችን በጥቂቱ ለማስቃኘት ወደድን - ለግንዛቤ ያህል፡፡ ከአሜሪካው ቦስተን ኮንቬንሽንና ኤግዚቢሽን ማዕከል እንጀምር፡፡
ማዕከሉ፤ በዓመት 1.6 ሚሊዮን እንግዶችንና ተሳታፊዎችን ባስተናገደበት ዓመት፣ ለሆቴል ቢዝነሶች ብቻ የ900 ሚሊዮን ዶላር ገበያ እንዳስገኘላቸው ተመዝግቦለታል። በዓመት ከ500 በላይ ዝግጅቶችን እንደሚያስተናግድ የሚነገርለት ማዕከሉ፤ እስካሁን ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ከ2.5 ቢሊዮን ዶላር በላይ አስተዋጽኦ እንዳበረከተ በ2022 የታተመው ሪፖርት ይገልጻል።
ሌላኛው ከዓመት በፊት የተመረቀው “አቢጃን የኤግዚቢሽን ማዕከል”፣ በምዕራብ አፍሪካ ብቻ ሳይሆን ከሰሀራ በታች ትልቁ የኤግዚቢሽን ማዕከል ነው ይባልለታል። ማዕከሉ በ130 ሚሊዮን ዶላር የተገነባ ሲሆን፤ 7 ሺ ካሬ ሜትር የኤግዚቢሽን አዳራሽ አለው። የጣራው ከፍታ 15 ሜትር ነው። ማዕከሉ 5 ሺ ተሰብሳቢዎችን የሚያስተናግድ የጉባኤ አዳራሽ እንዲሁም የአስተዳደር ሕንጻዎችን ያካትታል። መድረኩና ወንበሮቹ ተገጣጣሚና ተጣጣፊ ስለሆኑ፣ አዳራሹ ኤግዚቢሽን ለማሳየትም ያገለግላል። 800 የመኪና ማቆሚያ ቦታዎችም ተዘጋጅተውለታል። በውስጡ የእንግዳ ማረፊያ ወይም ሆቴል ባይኖረውም፣ የባሕር ዳርቻ መዝናኛ አጠገብ የተገነባ በመሆኑ ጠቅሞታል። ለአካባቢው ነዋሪዎች ጥሩ ገበያ ያመጣላቸዋል። ለአገሪቱ ለአይቮሪኮስት የቱሪዝም ገቢ እያስገኘላት ይገኛል።
በአገራችን አዲስ አበባ እየተገነባ የሚገኘው ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽንና ኮንቬንሽን ማዕከል፣ ከቱሪዝም ገቢ በተጨማሪም፣ በርካታ ጥቅሞችን ያበረክታል። በዙሪያው የቢዝነስና የስራ ዕድሎችን የሚያስፋፋ፣ የእድገትና የብልጽግና ግንኙነቶችን የሚፈጥር የኢኮኖሚ መነሃሪያ (Hub) በመሆን ያገለግላል። ባሕላዊ፣ ጥበባዊና ማኅበራዊ ፋይዳዎችን የሚያበራክትም ነው - አገልግሎቶቹ በዓይነታቸው ብዙ ናቸው።
ይህም ብቻ አይደለም። የኢንዱስትሪዎች፣ የቴክኖሎጂዎች፣ የምርቶችና የአገልግሎቶች ዓለማቀፍ ኤግዚቢሽን ሲዘጋጅ፣ የዕውቀት ሽግግርን ያቀላጥፋል። የኢንቨስትመንትና የቢዝነስ አማራጮችን ይከፍታል። የንግድና የገበያ ግንኙነቶችን ለመፍጠር፣ ውል ለመፈራረም፣ ሽያጭና ግዢ ለመጀመር መልካም አጋጣሚዎችን ይፈጥራል። ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችንና ዝግጅቶችን የሚያስተናግድ አገር፣ በዓለማቀፍ የዲፕሎማሲና ኢኮኖሚ መድረክ ተሰሚነቱ ይጨምራል። የኢኮኖሚ ድርሻው እያደገ ይሄዳል።
አዲስ ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽንና ኮንቬንሽን ማዕከል 5ሺ እና 2ሺ ተሳታፊዎችን የሚያስተናግዱ ትልልቅ አዳራሾች ፣ ለኤግዚቢሽኖች እንዲሁም ለጉባኤዎች በስምንት ንዑስ አዳራሽ በርካታ ስብሰባዎችን በአንድ ጊዜ ማስተናገድ የሚያስችል ነው። በአዲስ አበባ ትልቁ ባለ 5 ኮኮብ ሆቴልም ተገንብቷል፤ 980 የእንግዳ ማረፊያዎችን መያዝ የሚችል እንዲሁም ከመስቀል አደባባይ በመቀጠል የሚጠቀስ ትልቅ አደባባይ፣ እንዲሁም ሁለት “የአምፊ ቲያትር” ስፍራዎችም እየተገነቡና እየተዘጋጁ ነው።
በዓለም የኤግዚቢሽንና የኮንፈረንስ ቱሪዝም ካርታ ላይ የኢትዮጵያ ስምና ድርሻ ጎልቶ እንዲታይ የሚያደርግ ሰፊ ፕሮጀክት ነው። ከተጓዳኝ ግንባታዎች ጋር 15 ሄክታር ይሸፍናል። በዓለም ደረጃ የመወዳደርና ተመራጭነትን የማግኘት ብቃት እንዲኖረው ታስቦ የተገነባ መሆኑ ይነገርለታል፡፡
መዲናችን አዲስ አበባ ዓለም ዓቀፍ ኤግዚቢሽኖችን፣ ጉባኤዎችንና ስብሰባዎችን በአንድ ማዕከል የማስተናገድ አቅም አልነበራትም ፣ ይህን የአገራችንን ጉድለት የሚያሟላ ማዕከል ተገንብቶ ወደ ፍጻሜው እየደረሰ ያለው ፕሮጀክት፤ ለከተማችንና ለአገራችን ተጨማሪ የስበት ማዕከል እንደሚሆን ይታመናል፡፡
ከተማችን በጣም እያደገች እየተለወጠች ነው። ተወዳዳሪነቷ እየጨመረ ነው። ግን በኮሪደር ልማት ብቻ እንዳልሆነ የአዲስ አበባ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ይናገራሉ። በእርግጥ የኮሪደር ልማቱም ሰፊ ነው። መሀል ከተማውን በስፋት ያካለለ፣ ከ130 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ርዝመትን የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ከተማዋን ከዳር ዳር እያዳረሰ ነው ማለት ይቻላል። ነገር ግን ከመሀል ከተማ ወደ ዳር ወጣ ስትሉም ብዙ አዳዲስ ግንባታዎችን ታያላችሁ። ጸዳ ያሉ መኖሪያ ቤቶች በብዛት እየተሰሩ ነው። ለኮሪደር ልማት የተነሱ ነዋሪዎች ምትክ መኖሪያ ቤት እንዲሁም የቤት መሥሪያ ምትክ ቦታ እየተሰጣቸው ነው። ነዋሪዎች በነጻ የሚገለገሉባቸው የመዝናኛና የመናፈሻ ስፍራዎች በአረንጓዴ መስክና በፏፏቴ ተውበው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።
በመሀል ከተማ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ግንባታ ከአኩሪ ታሪካችን ጋር የተያያዘ ጥሩ ነገር ፈጥረናል። የትልቅ ታሪክ መዘክር ከመሆኑም በተጨማሪ፣ በግንባታው ጥራትና ውበት፣ በጠቅላላ ይዘቱና በተሟላ አገልግሎቱ ምን ያህል ተመራጭነትን እንዳገኘ በተግባር አይተናል። የኮንፈረንስ ቱሪዝም ስበት ለመሆን ችሏል። ከመሀል ከተማ ወደ ዳር ወጣ ብለን ደግሞ ሌላ ግዙፍ ማዕከል እየጨመርንበት ነው። አዲስ አበባ የዓለም ዓቀፍ ኤግዚቢሽኖችና ጉባኤዎች መነሃሪያነቷን የምናረጋግጥበት፣ የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማዕከልነቷን በኩራት የምንመሰክርበት ይሆናል።
ኢትዮጵያ በአመቺ ጸጋዎች የታደለች አገር እንደሆነች የገለጹት የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፤ በርካታ ታሪካዊ ቅርሶችና ሀብቶች፣ የተፈጥሮ ጸጋዎችና ውበቶች አሏት። የአፍሪካ አንድነት መሥራችና የአፍሪካ ሕብረት ዋና መቀመጫ ናት። ቢያንስ ቢያንስ በዓመት አንዴ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አገራችን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መሥራችም ናት። የተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የሚገኘው በአዲስ አበባ ነው። ከዚህም ጋር ተያይዞ በርካታ የተመድ ተቋማት በአዲስ አበባ ከትመዋል። ይሄ ሌሎች አገራት የማያገኙት ዕድል ነው። የዓለም የዲፕሎማሲ ማዕከላት ተብለው የሚጠቀሱ የዓለማችን አገራት በጣት የሚቆጠሩ ናቸው። ኢትዮጵያ ከእነዚህ መካከል አንዷ ናት።
በታሪካዊ ሀብቶችና በተፈጥሮ ጸጋዎች የታደለች ቢሆንም ግን፣ በዓለም አቀፍ ቱሪዝምና ኢኮኖሚ ውስጥ ተገቢውን ጥቅምና ድርሻ እያገኘች አይደለችም። በተመድና በአፍሪካ ሕብረት ስር የተካተቱ ብዙ ተቋማት በከተማችን አሉ። ዓለም ዓቀፍ ኤግዚቢሽኖችንና ጉባኤዎችን ማካሄድ ይፈልጋሉ። እዚሁ አገራችን ውስጥ ቢሆንላቸው ይመርጣሉ - ብዙዎቹ። ነገር ግን፣ ተስማሚ ማዕከላትና አማራጮች ፍለጋ ወደ ሌሎች አገራት ያማትራሉ።
ትልልቅ ዓለም ዓቀፍ ኤግዚቢሽኖችን በብቃት ለማስተናገድ የምንችልበት፣ ዓለም ዓቀፍ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት የሚሰጥና ዘመናዊ መሠረተ ልማቶች የተሟሉለት ማዕከል በብቃት ሳናሰናዳ ስለቆየን በየዓመቱ ብዙ ዕድሎችን ያስቀርብናል። የአገራችንን ኢኮኖሚ ሊያሳድጉ የሚችሉ የሥራና የገበያ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ዕድሎች ዓይናችን እያየ ያመልጡን ነበር። አሁን ግን በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ጥራቱን የጠበቀና የተሟላ አገልግሎት የሚሰጥ ማዕከል ተገንብቷል ፤ብለዋል የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ - አዲስ ዓለም ዓቀፍ ኤግዚቢሽንና ጉባኤ ማዕከል።
የማዕከሉ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሲሳይ ገመቹ እንደሚሉት፣ የግንባታውን ጥራትና ውበት በርካታ ባለሙያዎች አይተው መስክረውለታል። ትልቁን አዳራሽ ሁለገብ አዳራሽ ይሉታል - ለስብሰባም ለኤግዚቢሽን ማሰናጃም ይሆናል። 5 ሺ ተሳታፊዎችን ማስተናገድ ይችላል። ዲዛይኑ የሕንጻውን ንድፍ በግላጭ የሚያሳይ “ስቲል ስትራክቸር” እንደሆነ ጠቅሰው፣ በባለ ሙያዎችም ሆነ በተመልካቾች ዐይን ሲታይ ያምራል ብለዋል። ለእያንዳንዱ የስብሰባ ወይም የኤግዚቢሽን ይዘት በሚስማማ መንገድ አዳራሹን ለማስጌጥ እንዲያመች ታስቦበት የተሠራ እንደሆነም ገልጸዋል።
በርካታ ሺ ሰዎችን በአንዴ የሚያስተናግድ ሰፊ አዳራሽ ቢሆንም፣ አየር እንደልብ ስለሚያንሸራሽር፣ የጣሪያው ከፍታም 28 ሜትር ስለሆነ የሙቀት መቆጣጠሪያ አያስፈልገውም። በተፈጥሯዊ ብርሃን አዳራሹን የሚያጥለቀልቁ ረዣዥምና ሰፋፊ መስኮቶች አሉት። የፊልም ምስሎችን ለማየት ወይም የኤሌክትሪክ መብራት መጠቀም ካስፈለገም፣ መስኮቶቹን ሙሉ ለሙሉ መጋረድ ይቻላል።
ሁለት የምግብ አቅርቦት ማስተናበሪያ ስፍራ፣ እንዲሁም የእረፍት ሰዓት የሻይ የቡና መስተናገጃ ሰፊ ቦታ አለው። ከአዳራሹ ሥር በታችኛው ፎቅ ወደ ተዘጋጁት በርካታ የመጸዳጃ ቤቶች የሚያደርስ መተላለፊያ የሚገኘውም በዚሁ አቅጣጫ ነው። በአዳራሹ ሌላኛው ጎን የክብር እንግዶች መቆያ ቦታና ተጨማሪ የመጸዳጃ አገልግሎት ስፍራዎች ተሰርተውለታል።
የኤግዚቢሽን አዳራሽ - በ5 ሺ ካሬ ሜትር ስፋት
ከሁለገብ አዳራሽ ቀጥሎ ከላይ የምናገኘው ትልቅ አዳራሽ ዋና አገልግሎቱ ለኤግዚቢሽን ነው። መካከለኛ አዳራሽ ነው ይሉታል - ዋና ስራ አስፈጻሚው ሲሳይ ገመቹ። አንድ ሺ ሰዎችን ያስተናግዳል። ዘና ያለ መንፈስ እንዲኖረው፣ አየር በደንብ እንዲንሸራሸር፣ የተፈጥሮ ብርሃን በሰፊው እንዲያስገባ ታስቦበት የተሰራው አዳራሽ፣ ጣሪያው 28 ሜትር ቁመት አለው።
ከአንድ አቅጣጫ በኩል፣ ከአዳራሹ አጠገብ የመጋዘን ክፍሎች አሉት። በሌላኛው አቅጣጫ ደግሞ ቢሮዎችን ይዟል። በአጠቃላይ ከኤግዚቢሽን ዝግጅት ጋር የተዛመዱ አገልግሎቶችን ሁሉ እንዲያሟላ ተድርጎ ነው የተሠራው።
ሰፊ የትዕይንት አዳራሽ - በተገጣጣሚ ግድግዳም ሲከፋፍሉት ደግሞ ሰባት ንዑስ አዳራሾች፡፡ አራተኛ ፎቅ ላይ የምናገኘው ሰፊ አዳራሽ፣ 2 ሺ ሰዎችን ማስተናገድ ይችላል። ለትልቅ ጉባኤ ሊያገለግል ይችላል። ስዕሎችን ለማሳየት ወይም ሌላ ለእይታ የሚቀርቡ ድግሶችን ለማዘጋጀትም የአዳራሹ ቅርጽ ይመቻል። ተመልካቾች በአንዱ ጫፍ ገብተው፣ በእይታ ድግሶችን ተስተናግደው ዓይናቸውን ረክቶ በሌላኛው ጥግ ይወጣሉ። ካስፈለገ ደግሞ ረዥሙ አዳራሽ ውስጥ ተገጣጣሚ ግድግዳዎች ተዘርግተው፣ ለንዑስ ስብሰባዎች የሚያገለግሉ 7 መካከለኛና አነስተኛ አዳራሾች ይወጣዋል። ግድግዳዎቹ ተጣጣፊ ተገጣጣሚ ቢሆኑም፣ ከመደበኛ ግድግዳ አይተናነሱም። ድምጽ አያሳልፉም፤ ሲታዩም ያምራሉ ብለዋል - የማዕከሉ ዋና ስራ አስፈጻሚ።
አዳራሹ አራተኛ ፎቅ ላይ ቢሆንም፣ ከበቂ በላይ መተላለፊያዎች አሉት። በየአቅጣጫው በተሠሩ በርካታ ሰፋፊ ደረጃዎች አማካኝነት መግባትና መውጣት ይቻላል። ከደረጃዎች ጎን “ስካሌተሮች” አሉ። ከእነዚህ በተጨማሪም አሳንሰሮች (ሊፍቶችን) መጠቀም ይቻላል።
የአዳራሾቹን አገልግሎት በትክክል ለማከናወንና ለመቆጣጠር የሚያገለግሉ የቴክኒክና የቴክኖሎጂ ክፍሎችን ጨምሮ፣ የጥበቃና የክትትል ስራውም በሚገባ እንደታሰበበት ስራ አስፈጻሚው ያስረዳሉ። የጥበቃ ስራዎችን በምሳሌነት አንስተው ሲናገሩ፣ ዋናዎቹ ቁልፍ ነገሮች የባለሙያ ስልጠናና ቴክኖሎጂ ናቸው ይላሉ። ኤግዚቢሽኖችና ጉባኤዎች በተቃና ሁኔታ እንዲካሄዱ ነው - የጥበቃ አስፈላጊነት። አዘጋጆች፣ ተሳታፊዎችና ተመልካቾች የተሟላ ምቹ አገልግሎት እንዲያገኙም ነው - የጥበቃ አላማው።
ለዚህም የጥበቃ ካሜራዎችና መከታተያ ቴክኖሎጂዎችን አሟልተናል ይላሉ - አቶ ሲሳይ። የጥበቃ ባለሙያዎች የተሰብሳቢዎችን ትኩረት በማይረብሽ ሁኔታ ስራቸውን እንዲያከናውኑም በቂ ስልጠና ይኖራቸዋል።
ከኤግዚቢሽንና ከጉባኤ አዳራሾች በተጨማሪ፣ ማዕከሉ ሌሎች በርካታ ግንባታዎችንንና አገልግሎቶችን ያካትታል። ባለ 5 ኮከብ ሆቴል - 980 የእንግዶች ማረፊያ ያለው። ከአዳራሾቹ አጠገብ የተገነባው ሆቴል፣ ስራው አልቋል ማለት ይቻላል። ተቀብቶ አጊጦ አምሯል። በሆቴል አገልግሎት በከተማችን በትልቅነቱ ቀዳሚነትን የያዘ ሆቴል እንደሚሆን የተናገሩት ከንቲባ አዳነች አበቤ፤ 980 የእንግዳ ማረፊያዎችን መያዝ ይችላል ብለዋል። የአገልግሎቱ ጥራት ከስካይ ላይት ጋር በእኩል ደረጃ የሚቀመጥ ነው ብለዋል። ነገር ግን የአዳራሾችና የሆቴል ግንባታ ጉዳይ ብቻ አይደለም።
ሰፊ የስበት መናኸሪያ
እዚህ አካባቢ ምንም ሆቴል አልነበረም ይላሉ - ከንቲባ አዳነች። አሁን ሦስት ሆቴሎች ተሰርተዋል። አራተኛው ከማዶ በኩል አለ። ተደማምረው 1400 የእንግዳ ማረፊያ አገልግሎት የማቅረብ አቅም አላቸው። ምርጥ ምርጥ አፓርትመንቶች በአካባቢው ተሰርተዋል። ለሕዝብ አገልግሎት ክፍት የሚሆኑ አረንጓዴ ስፍራዎችና ተቋማትም እየተዘጋጁ ነው። ፊት ለፊት ለሚ ፓርክ አለ። ሰፊ ነው። ከመስቀል አደባባይ በመቀጠል የሚጠቀስ የከተማችን ትልቅ አደባባይ ነው። ከኤግዚቢሽንና ከጉባኤ ማዕከሉ ጋር ተያይዞ ነው ስራው የሚከናወነው።
ይህም ብቻ አይደለም። የአዳራሾችና የሆቴል ግንባታዎችን ጨምሮ፣ በተጓዳኝ የሚካሄዱ የፓርክና የተለያዩ አገልግሎቶች ግንባታዎች ብዙ ናቸው። ከአዳራሾቹ አጠገብ በሁለት አቅጣጫ፣ ሰፋፊ አምፊቴአትሮች እየተገነቡና እየተዘጋጁ ነው።

 

ከዚህ ሥር በአጭሩ ስለ አሁናዊ ሁኔታችን የተሰማኝን አወጋለሁ…
…ከምንኖረው ይልቅ የምንሰማው የሚያሳስበን ሕዝቦች ሆነናል፤ ከላመው፣ ከጣመው፣ ካጣጣምነው፣ ከቀመስነው በላይ የተነገረንን አስቀድመን እናስሰልፋለን፤ በአመክኒዮ የትምህርት ዘርፍ ‹‹The problem of proof›› ይሉት ጉዳይ አለ፤ ትክክል መሆንን የማረጋገጥ ክፍተት እንበለው መሰለኝ፤ መድረሻችን፣ ወይም ድምዳሜያችን መነሻን መሠረት ያደረገ መሆን እንዳለበት የሚተነትን ሲሆን፣ ድምዳሜ ላይ ለመድረስ ሁነኛ፣ ወይም ትክክለኛ መነሻ ሊኖረን እንደሚገባ ያትታል።
ኢትዮጵያ ውስጥ ሐይማኖቶች (በርካቶቹ) ከመጡ/ከተዋወቁ ረጅም ጊዜን አስቆጥረዋል፤ ሕዝቡም በተለያዩ ሐይማኖቶች ሥር ተቻችሎ ረጅም ዓመታትን ኖሯል፤ ብሔርም ቢሆን የቆየ ጉዳይ ነው፤ ነገር ግን አልፎ፣ አልፎ በተወሰኑ ግለሰቦች ዘንድ በሐይማኖትና በብሔር ጎራ ከፍሎ መናቸፍ አለ፤ ሐይማኖት የሚያጣላን፣ ብሔር የሚያናክሰን ከሆነ፣ ‹እስከዛሬ ለምን ሳያናክስ ቆየ?› ብሎ መጠየቅ የሕዝቡ ጉዳይ ነው፤ እስከዛሬ በሠላም የኖርን ሰዎች ደርሰን የምንጣላ ከሆነ፣ ሐይማኖት ወይም ብሔር ሳይሆኑ ጥፋተኞቹ እኛው ነን።
ይኼን ሁሉ ዘመን ኖረን፣ ኖረን አሁን ላይ የምንናቸፍበት ምንም ምክንያት ሊኖር አይገባም በማለት መለስ ብሎ የኖርነውን ዘመን ማሰብ መልካም ነው፤ ስህተቶቹ ሕዝቦች ነን፤ በሶስዮሎጂ መስክ ደግሞ ‹‹Noble Lies›› የሚባል ነገር አለ፤ ዋሽቶ ማስታረቅ ዓይነት ጉዳይ ነው፤ ዋሽቼ ላስታርቃችሁ አይደለም፤ ሕጸጻችሁን አምናችሁ መነቃቅራችሁ እንድትጥሉት ለመናገር ያህል ነው። ከመስማት መኖር፣ ከመቅዳት ማጣጣም ይቀድማሉና ኑሯችሁን እመኑ።
ኑሯችንን ስለማናምን ጠንካራ ሐይማኖተኛ፣ ጠንካራ ዜጋ፣ ተቆርቋሪ ትውልድ ከማፍራት አፈግፍገናል፤ ስለ ሀገሩ የሚጮኽ እንጂ ስለ ሀገሩ የሚተጋ ማግኘት ዘበት እየሆነ መጥቷል፤ ሰሚዎች፣ ጢያራ ጋላቢዎች፣ አጉል ተስፈኞች፣ ተነጂዎች ስለሆንን እውንና ሕልማችን ተባርዘዋል፤ ጠንካራ ሕዝብና መንግሥት እንዳይኖረን ከሚያደርጉ ጉዳዮች መካከል አንዱ ይኼው አመላችን ነው።
ሕዝብን የሚቀርጸው ሕዝብ ነው፤ መንግሥትንም ቢሆን በአብዛኛው የሚቀርጸው ሕዝብ ነው፤ ሕዝቡ መንግሥትን ሥራህን ሥራ ሊለው ይገባል፤ መንግሥትን ሊመከርና ሊዘክር ይጠበቃል፤ መንግሥትን መደገፍ አንድ ነገር ነው፤ ለሀገር ዋስትና ሀገርን የሚያስቀድም መንግሥት ሊደገፍ ይገባል፤ ነገር ግን በእኛ ዘመን መንግሥትን ማበረታታት፣ መደገፍ፣ ከጎኑ መሆን… ሳይሆን እየተደረገ ያለው የመንግሥት አክቲቪስት የመሆን ዳርዳርታ ነው።
ቢቻል መንግሥትን ደግፎ፣ መንግሥትን አበርትቶ ለሕዝብ ነው አክቲቪስት መሆን የሚገባው፤ የሕዝባዊ ግዴታን መወጣት፣ መብትና ግዴታን አውቆ በሕግና ሥርዐት መተዳደር፣ ልማትን በንቃት መተግበር… መንግሥትን ከመደገፍ የሚመደቡ እና የዜግነት ግዴታ ተብለው ከሚታሰቡ ጉዳዮች መካከል ዋንኞቹ ናቸው፤ ነገር ግን ለመንግሥት ማጎብደድ፣ ለሕዝቡ ጠብ የማይል ሥራን እየሠራ ሕዝቡን የሚያንገሸግሸውን መንግሥት ሙጥኝ ማለት የአመክኒዮ ክፍተት ነው።
አሁን፣ አሁን ላይ አብዛኛው ሕዝብ በአንቂ ንግግሮች፣ በተራ ተስፋ ሰጪ ወሬዎች፣ ሐሳዊ በሆኑ አብቂ አባባሎች ታጅሎ ኑሮውን በመግፋት ላይ እንዳለ መገመት ከባድ አይደለም፤ በሚሰማው የተቀነባበረ አንቂ ንግግር ነገውን ይጠባበቃል፤ አንገሽጋሽ ኑሮው የሚነግረውን ከማመን ባለፈ የመንግሥትንና የሚዲያዎችን ተረታ፣ ተረት እየቀረደደ ይባትላል።
ማነው መባተል ዕጣ-ፈንታችሁ ነው ያለን? ማነው ጢያራ ስትጋልቡ፣ ነፋስ ስትከተሉ ከርማችሁ ኑ ያለን? በውል መንገዋለልና መንከራተት ምንድር ነው? መንግሥትም ቢሆን የተያያዘው ጉዳይ የማንቃት ሥነ-ዘዴውን ነው፤ ‹‹motivational speech›› መሳይ ነገሮች፣ ነገር ግን ከሥሌት ይልቅ ሥሜት የበዛባቸው ሥራዎችና ድርጊቶች አጥለቅልቀውናል…
…ይኼ የአንቂ ነገር ጉዳይ ሊታሰብበት ይገባል፤ መንግሥት የሀገር ማልማትና የነገን መንገድ ጥርጊያ ድርጊቱን ቸል ብሎ አንቂ ሆኖ አርፏል፤ አንቂዎች በነቂው ላይ ምቹ ሥሜትን፣ ተነሳሽነትን መፍጠር እንጂ ማጃጃል ሥራቸው አይደለም። ነቂ በአጉል ብጽዕና ታጅሎ ዛሬን ሳይኖር ነገን መጠባበቅ የለበትም። የተያያዝነው ጉዳይ ሐይማኖት አይደለምና መሬት ባለ ነገር እንጅ በተሰፈረ የአንቂ ንግግር ብቻ መወሰን ያለበት አይመስለኝም።
በበኩሌ፣ መሬት ባልረገጠ መናኛ ተስፋ አላምንም፤ በተነገረኝ ሳይሆን በኖርኩበት ልክ ነገሮችን ልመዝን እገደዳለሁ፤ እውነት የስብከት ውጤት ብቻ አይደለም፤ እውነት የሚነገረን መሸንገያ ሳይሆን፣ የምንኖረው ኑሮ ነው፤ በዚህ ዘመን ጥጋብ ረሃባችንን፣ ጥማት ቁርጥማታችንን፣ መውደቅ መነሳታችንን…መንግሥት ነው የሚነግረን፤ የምንኖረው እኛ፤ የሚነግረን ሌላ ከሆነ መጣረስ ተከትሏል ማለት ነው፤ መድኀኒት መግዣ ተወዶብኝ የምንገላታውን እኔ ነኝ የማውቀው እንጂ አድገሃል ስለተባልኩ አዎ የምልበት ምንም ምክንያት የለም፤ ኑሮዬን፣ መንገፍገፌን እኔው አውቀዋለሁና ለእኔው ተውልኝ…
ጉዳዩ የእኛው ክፍተት እንደሆነም ጭምር አድርገን መውሰድ ብልሃት ነው፤ ሕዝብ ተብለን እስከተጠራን እምነትና ተስፋችንን በመልክ፣ በመልኩ ማድረግ አለብን፤ መረጃዎችን ማጥራት፤ ምንጮችን መገምገም ግዴታ ነው፤ ለነገሩ ከመኖር በላይ ምን እውነት አለ? የኖርነውን ለመገምገም ምን አደከመን? መገምገም የቤት ሥራችን ይሁን፤ የማይገመግም ማኅበረሰብ የማሰላሰል ክፍተት እንዳለበት ይገመታል፤ ነገሮችን በቁም በውርዳቸው መሰልቀጥ መዘዙ ብዙ ነውና፣ ቆም ብሎ ማጤን ተገቢ ነው።
ከዚህ ሥር በአጭሩ ስለ አሁናዊ ሁኔታችን የተሰማኝን አወጋለሁ…
…ከምንኖረው ይልቅ የምንሰማው የሚያሳስበን ሕዝቦች ሆነናል፤ ከላመው፣ ከጣመው፣ ካጣጣምነው፣ ከቀመስነው በላይ የተነገረንን አስቀድመን እናስሰልፋለን፤ በአመክኒዮ የትምህርት ዘርፍ ‹‹The problem of proof›› ይሉት ጉዳይ አለ፤ ትክክል መሆንን የማረጋገጥ ክፍተት እንበለው መሰለኝ፤ መድረሻችን፣ ወይም ድምዳሜያችን መነሻን መሠረት ያደረገ መሆን እንዳለበት የሚተነትን ሲሆን፣ ድምዳሜ ላይ ለመድረስ ሁነኛ፣ ወይም ትክክለኛ መነሻ ሊኖረን እንደሚገባ ያትታል።
ኢትዮጵያ ውስጥ ሐይማኖቶች (በርካቶቹ) ከመጡ/ከተዋወቁ ረጅም ጊዜን አስቆጥረዋል፤ ሕዝቡም በተለያዩ ሐይማኖቶች ሥር ተቻችሎ ረጅም ዓመታትን ኖሯል፤ ብሔርም ቢሆን የቆየ ጉዳይ ነው፤ ነገር ግን አልፎ፣ አልፎ በተወሰኑ ግለሰቦች ዘንድ በሐይማኖትና በብሔር ጎራ ከፍሎ መናቸፍ አለ፤ ሐይማኖት የሚያጣላን፣ ብሔር የሚያናክሰን ከሆነ፣ ‹እስከዛሬ ለምን ሳያናክስ ቆየ?› ብሎ መጠየቅ የሕዝቡ ጉዳይ ነው፤ እስከዛሬ በሠላም የኖርን ሰዎች ደርሰን የምንጣላ ከሆነ፣ ሐይማኖት ወይም ብሔር ሳይሆኑ ጥፋተኞቹ እኛው ነን።
ይኼን ሁሉ ዘመን ኖረን፣ ኖረን አሁን ላይ የምንናቸፍበት ምንም ምክንያት ሊኖር አይገባም በማለት መለስ ብሎ የኖርነውን ዘመን ማሰብ መልካም ነው፤ ስህተቶቹ ሕዝቦች ነን፤ በሶስዮሎጂ መስክ ደግሞ ‹‹Noble Lies›› የሚባል ነገር አለ፤ ዋሽቶ ማስታረቅ ዓይነት ጉዳይ ነው፤ ዋሽቼ ላስታርቃችሁ አይደለም፤ ሕጸጻችሁን አምናችሁ መነቃቅራችሁ እንድትጥሉት ለመናገር ያህል ነው። ከመስማት መኖር፣ ከመቅዳት ማጣጣም ይቀድማሉና ኑሯችሁን እመኑ።
ኑሯችንን ስለማናምን ጠንካራ ሐይማኖተኛ፣ ጠንካራ ዜጋ፣ ተቆርቋሪ ትውልድ ከማፍራት አፈግፍገናል፤ ስለ ሀገሩ የሚጮኽ እንጂ ስለ ሀገሩ የሚተጋ ማግኘት ዘበት እየሆነ መጥቷል፤ ሰሚዎች፣ ጢያራ ጋላቢዎች፣ አጉል ተስፈኞች፣ ተነጂዎች ስለሆንን እውንና ሕልማችን ተባርዘዋል፤ ጠንካራ ሕዝብና መንግሥት እንዳይኖረን ከሚያደርጉ ጉዳዮች መካከል አንዱ ይኼው አመላችን ነው።
ሕዝብን የሚቀርጸው ሕዝብ ነው፤ መንግሥትንም ቢሆን በአብዛኛው የሚቀርጸው ሕዝብ ነው፤ ሕዝቡ መንግሥትን ሥራህን ሥራ ሊለው ይገባል፤ መንግሥትን ሊመከርና ሊዘክር ይጠበቃል፤ መንግሥትን መደገፍ አንድ ነገር ነው፤ ለሀገር ዋስትና ሀገርን የሚያስቀድም መንግሥት ሊደገፍ ይገባል፤ ነገር ግን በእኛ ዘመን መንግሥትን ማበረታታት፣ መደገፍ፣ ከጎኑ መሆን… ሳይሆን እየተደረገ ያለው የመንግሥት አክቲቪስት የመሆን ዳርዳርታ ነው።
ቢቻል መንግሥትን ደግፎ፣ መንግሥትን አበርትቶ ለሕዝብ ነው አክቲቪስት መሆን የሚገባው፤ የሕዝባዊ ግዴታን መወጣት፣ መብትና ግዴታን አውቆ በሕግና ሥርዐት መተዳደር፣ ልማትን በንቃት መተግበር… መንግሥትን ከመደገፍ የሚመደቡ እና የዜግነት ግዴታ ተብለው ከሚታሰቡ ጉዳዮች መካከል ዋንኞቹ ናቸው፤ ነገር ግን ለመንግሥት ማጎብደድ፣ ለሕዝቡ ጠብ የማይል ሥራን እየሠራ ሕዝቡን የሚያንገሸግሸውን መንግሥት ሙጥኝ ማለት የአመክኒዮ ክፍተት ነው።
አሁን፣ አሁን ላይ አብዛኛው ሕዝብ በአንቂ ንግግሮች፣ በተራ ተስፋ ሰጪ ወሬዎች፣ ሐሳዊ በሆኑ አብቂ አባባሎች ታጅሎ ኑሮውን በመግፋት ላይ እንዳለ መገመት ከባድ አይደለም፤ በሚሰማው የተቀነባበረ አንቂ ንግግር ነገውን ይጠባበቃል፤ አንገሽጋሽ ኑሮው የሚነግረውን ከማመን ባለፈ የመንግሥትንና የሚዲያዎችን ተረታ፣ ተረት እየቀረደደ ይባትላል።
ማነው መባተል ዕጣ-ፈንታችሁ ነው ያለን? ማነው ጢያራ ስትጋልቡ፣ ነፋስ ስትከተሉ ከርማችሁ ኑ ያለን? በውል መንገዋለልና መንከራተት ምንድር ነው? መንግሥትም ቢሆን የተያያዘው ጉዳይ የማንቃት ሥነ-ዘዴውን ነው፤ ‹‹motivational speech›› መሳይ ነገሮች፣ ነገር ግን ከሥሌት ይልቅ ሥሜት የበዛባቸው ሥራዎችና ድርጊቶች አጥለቅልቀውናል…
…ይኼ የአንቂ ነገር ጉዳይ ሊታሰብበት ይገባል፤ መንግሥት የሀገር ማልማትና የነገን መንገድ ጥርጊያ ድርጊቱን ቸል ብሎ አንቂ ሆኖ አርፏል፤ አንቂዎች በነቂው ላይ ምቹ ሥሜትን፣ ተነሳሽነትን መፍጠር እንጂ ማጃጃል ሥራቸው አይደለም። ነቂ በአጉል ብጽዕና ታጅሎ ዛሬን ሳይኖር ነገን መጠባበቅ የለበትም። የተያያዝነው ጉዳይ ሐይማኖት አይደለምና መሬት ባለ ነገር እንጅ በተሰፈረ የአንቂ ንግግር ብቻ መወሰን ያለበት አይመስለኝም።
በበኩሌ፣ መሬት ባልረገጠ መናኛ ተስፋ አላምንም፤ በተነገረኝ ሳይሆን በኖርኩበት ልክ ነገሮችን ልመዝን እገደዳለሁ፤ እውነት የስብከት ውጤት ብቻ አይደለም፤ እውነት የሚነገረን መሸንገያ ሳይሆን፣ የምንኖረው ኑሮ ነው፤ በዚህ ዘመን ጥጋብ ረሃባችንን፣ ጥማት ቁርጥማታችንን፣ መውደቅ መነሳታችንን…መንግሥት ነው የሚነግረን፤ የምንኖረው እኛ፤ የሚነግረን ሌላ ከሆነ መጣረስ ተከትሏል ማለት ነው፤ መድኀኒት መግዣ ተወዶብኝ የምንገላታውን እኔ ነኝ የማውቀው እንጂ አድገሃል ስለተባልኩ አዎ የምልበት ምንም ምክንያት የለም፤ ኑሮዬን፣ መንገፍገፌን እኔው አውቀዋለሁና ለእኔው ተውልኝ…
ጉዳዩ የእኛው ክፍተት እንደሆነም ጭምር አድርገን መውሰድ ብልሃት ነው፤ ሕዝብ ተብለን እስከተጠራን እምነትና ተስፋችንን በመልክ፣ በመልኩ ማድረግ አለብን፤ መረጃዎችን ማጥራት፤ ምንጮችን መገምገም ግዴታ ነው፤ ለነገሩ ከመኖር በላይ ምን እውነት አለ? የኖርነውን ለመገምገም ምን አደከመን? መገምገም የቤት ሥራችን ይሁን፤ የማይገመግም ማኅበረሰብ የማሰላሰል ክፍተት እንዳለበት ይገመታል፤ ነገሮችን በቁም በውርዳቸው መሰልቀጥ መዘዙ ብዙ ነውና፣ ቆም ብሎ ማጤን ተገቢ ነው።

ከዕለታት አንድ ቀን የገና ዕለት፤ ቤተሰብ ለእራት እየተዘጋጀ ሳለ አንድ የዘመድ ጥቁር እንግዳ ከተፍ ይላል።
“እንዴት ናችሁ?” ይላል ከደጃፍ።
“ደህና፤ እንደምን ሰነበትክ?” ይላሉ አባወራ።
“እኔ ደህና ነኝ። ዛሬ ጥቁር እንግዳ ሆንኩባችሁ”
“ኧረ ምንም አላስቸገርከንም። ዛሬ ገና እኮ ነው። መልካም ቀን መጥተሃል። ጥቂት ሰላምታ እንደተለዋወጡ፣
“እራት ተዘጋጅቷል። ና እንመገብ” ይሉትና እሺ ብሎ ይቀመጣል።
መሶቡ ቀረበ።
ዶሮው በጎድጓዳ ሳህን ከማዕድ ቤት መጣ። ዙሪያውን ከበቡ፤ ቤተሰብ። መሶቡ ተከፈተና መብላት ተጀመረ።
ቤተሰቡ ውስጥ እጅግ አስቸጋሪ፣ እጅግ ሞገደኛ ልጅ አለ። አመለኛ ነው።
ገና መብላት እንደተጀመረ እንግዳው ፊት አንድ ዕንቁላል ሲቀመጥ፣ ያ ልጅ አፈፍ አድርጎ ዋጠው።
አባት፤ “ኧ፤ አንተ ባለጌ! ከፊትህ ብላ!” አለው።
ልጁ አልተበገረም።
እንግዳው፤ “ግዴለም ተወው። ልጅ አይደለም እንዴ?” አለ።
ባለቤትየዋ ለእንግዳው አንድ የዶሮ ብልት አወጣችለት።
በጥቂት ሰከንዶች ልጅ፣ ያቺን ብልት ያለምንተፍረት ላፍ አደረገው።
አባት፤ የልጁን ክንድ ይዞ በንዴት ጠበጠበው።
እንግዳው፤ “በፍፁም አይገባም። ነውር ነው። ገበታ ላይ ልጅ አይመታም። በጊዜ መምከር ነው እንጂ መደብደብ ተገቢ አይደለም።”
የመጨረሻ ብልት ለሁሉም ወጣ። ያ ልጅ የራሱ እያለለት፣ የእንግዳውን አፈፍ አደረገ። አባት ገና ወዳፉ ሳይከተው እጁን በፍጥነት ይዞ ክፉኛ ደበደበውና ወደ እንግዳው ዞሮ፤ “ይቅርታ ወዳጄ፤ ይሄ ልጄ እጅግ ባለጌ ነው።”
እንግዳው በይሉኝታ፤ “ኧረ ይህን ያህል አላጠፋም። የእኛ ልጅ’ኮ ዶሮውን ከነድስቱ ነው ይዞት የሚሄደው!” አለ።
ይሄኔ አባወራው፤ “አይ፤ ለእሱስ ልጃችንን ደህና አርገን ቀጥተነዋል!” አሉ።
* * *
ከመሰረቱ ያልተቀጣ ከመነሻው ሥነ-ምግባር ያልያዘ ሰው፤ ውሎ አድሮ የማይመለስበት አደጋ ላይ ይወድቃል። “የተማርኩ አይደለሁም ወይ? እኔ አድነዋለሁ” ማለት በፍፃሜው አይሆንም! የኋላ ኋላ ችግር እየሆነ ዋጋ ያስከፍለናል!
አቶ ታደሰ ገብረ ኪዳን የተባሉ የሀገራችን ደራሲ በአንድ መጽሐፋቸው፤ ሚስተር ሮበርት ማክናማራ በዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ስለ አፍሪካውያን ችግር አውስተዋል። ኢትዮጵያውያንን አንድ ላይ ተሰባስበን ቢያገኙን ኖሮ፣ “በአገራችሁ ለምንድነው ረሀብ፣ ድንቁርና መታረዝና በሽታ የነገሱት? ለምንድነው ወደፊት መራመድ ያልቻላችሁት?” ብሎ መጠየቁ አይቀሬ ነበር። እኛ ደግሞ ኢትዮጵያን ለማስቀደም የምናደርገው ጥረት የሚመክነው ከቶ ለምንድን ነው? “ከጥረት ማነስ? ጥረታችንን የሚያስተባብር በመጥፋቱ? ወይስ ራሳችን ለራሳችን ፍቱን መርዝ ስለሆንን?” ብለን መጠየቅ ይገባናል።
ይህን ጥያቄ ለመመለስ ያለጥርጣሬ፣ ልብ በልብ መገናኘት ያስፈልገናል። የእኔ ማደግ የሌላው ማነስ ነው የሚለውን አስተሳሰብ አሽቀንጥረን መጣል አለብን። ሁሉን ውንጀላ መንግሥት ላይ ማነጣጠር አይገባንም። ከግለሰብ፣ እስከ ማህበረሰባት፣ ከማህበረሰብና ተቋማት እስከ መንግሥት የየራሳችንን ሙዳ መውሰድ አለብን። ሌላው ጉዳይ አለመናበብ ነው።
አለመናበብ ትልቅ አደጋ ነው። ህግ አውጪው፣ ህግ ተርጓሚውና ህግ አስፈፃሚው አካል ሲጣጣሙ ካየን የበለጠ አደጋ አለ። አለመግባባት ጠፋ ወይም ተዛባ ማለት የአገር ህልውና ሥርዓት ተዛባ ማለት ነው። የህዝብን ጥርጣሬ የሚፈበርኩ ውሳኔዎች አለመረጋጋትን ሲፈጥሩ ወደ አደጋ ያመራሉ። በሀገራችን አደጋ እንዳይፈጠር ከማድረግ ይልቅ ከመጣ በኋላ የመዝመት ባህል አለ። ለአገሪቱ ደህንነት አስጊ አካሄድ ነው።
እንደ ናይጄሪያ የሥልጣን ሹመኞች መቃብርን ገንዘብ ማስቀመጫ ማድረግ ደረጃ መድረስ፣ የአፍሪካን የሙስና ደረጃ ጣራ እያመላከተን ባለንበት ሰዓት፣ እኛስ ወዴት እያመራን ነው? ብለን መጠየቅ ይገባናል። ሐብት የማጋበስ ልማድ አንዴ ከጀመረ ማደጉን አያቆምም። በርናንድ ሾው፤ There is no little pregnancy እንዳለው ነው። (የእርግዝና ትንሽ የለውም እንደ ማለት)።
ያለጥናት የእግረኛ መንገድ ይሠራል፤ የእግረኛ መንገድ ይፈርሳል። ተሰርቶ ሊጠናቀቅ የደረሰ ግዙፍ ህንፃ ከፕላን ውጭ ነው ተብሎ ይፈርሳል። መመሪያ ይወጣል፤ ፉርሽ ባትሉኝ ይባላል። ሁሉንም መሸከሚያ ትከሻ ያለው ህዝብ ይታገሣል። ዛሬ የቀረን ከመነሻው “የማፍረስ መጠባበቂያ ህግ መደንገግ ነው!” ማንም ተጠያቂ፣ ማንም ኃላፊ የለም ለጥፋቱ።
“ድክመቶቻችንን ለማስወገድ መተራረም አስፈላጊ ነው። ነገር ግን ሒስን ስለምንጠላ ሒስ ደርዳሪን እንደ ጦር እንፈራለን። ወቀሳን በፀጋ መቀበል አናውቅበትም። ሰውን ላለማስቀየም እየተባለ ችግሮችን ሸፋፍነን ማለፍ ይቀናናል። … ማስተዳደር ማለት ረግጦ ወይም አዋርዶ መግዛት ይመስለናል። በመሆኑም የበቀል ልጆችን መፈልፈል ብሔራዊ መለያችን ሆኗል። ለችግሮቻችን መፍትሔ ሳናገኝላቸው እየቀረን፣ በችግር ላይ ችግር እየተደራረብን፣ በልማት ወደፊት መግፋት አቅቶናል። በኋላ ቀርነታችን እያንዳንዳችን ጥፋተኞች መሆናችንን አምነን መቀበል አልቻልንም። አንዳችን በሌላችን ማሳበብና እራሳችንን ነፃ ለማውጣት መቀበጣጠር እንጂ ለውድቀታችን ኃላፊነትን መውሰድ አልተማርንም” ይሉናል በዚያው መጽሐፍ። ያ መጽሐፍ ይህን ያስመዘገበን በ1999 ዓ.ም ነው። ዛሬስ? የተጠቀሱት ችግሮች በመቶ ተባዝተው ይገኛሉ። ብዙ የተዛቡ ሕግጋት ለአንድ ተረት ምቹ ሆነው እናያለን። ያንን ልብ ካላልን፣ የባሰ ችግር ውስጥ እንገባለን። ይህ ወቅታዊ ተረት፤”ብላ ያለው ተጋግሮ ይጠብቀዋል፤ ተሸከም ያለው ታሥሮ ይጠብቀዋል!” የሚለው ነው።

የሰላምና የኢኮኖሚ አርበኞች 20 ሚ. ብር ተሸለሙ

 

ላለፉት 7 ዓመታት በአዳማ ኢንዱስትሪያል ፓርክ በጨርቃጨርቅ ምርት ላይ የተሰማራው የቻይናው አንቴክስ ጨርቃጨርቅ ኃ.የተ.የግ.ማ፤ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ልማትና ሰላም የላቀ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ግለሰቦችና ድርጅቶችን አወዳድሮ 20 ሚሊዮን ብር እንደሚሸልም ያስታወቀው የዛሬ ሁለት ወር ገደማ ነበር፡፡
ከትላንት በስቲያ ታህሳስ 17 ቀን 2017 ዓ.ም ተሲያት በኋላ፣ በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ በተከናወነ ታላቅ ሥነስርዓት፣ በሁለቱም የውድድር ዘርፎች አሸናፊዎች ተለይተው ሽልማታቸው በክብር ተበርክቶላቸዋል፡፡ በሰላም ዘርፍ የጋሞ አባቶች ያሸነፉ ሲሆን፤ በኢኮኖሚ ዘርፍ ደግሞ ኢንቨስተሩ ኢንጂነር ቢጃይ ናይከር አሸንፈዋል፡፡ እያንዳንዳቸውም በነፍስ ወከፍ 10 ሚሊዮን ብርና ከ5 ኪ.ግ ንጹህ ብር የተሰራ ግዙፍ ዋንጫ ተሸልመዋል፡፡
የጋሞ አባቶች የሰላም አሸናፊ መሆናቸው ይፋ መደረጉን ተከትሎ፣ አዳራሹን በባህላዊ ዜማቸው በደስታ አድምቀውታል፡፡ ሽልማታቸውን በክብር ከተቀበሉ በኋላ አንድ ተወካያቸው የተሰማቸውን እንዲናገሩ ተጋበዙ፡፡ የጋሞ አባቶች ተወካይ አንደበተ ርዕቱ ናቸው፡፡ በሰላም ዙሪያ ከፍልስፍና የማይተናነስ አጭር ንግግር አቀረቡ፡፡
“ይሄ ሽልማት እዚህ የመጣን የጋሞ አባቶች ሽልማት ብቻ ሳይሆን የመላው ጋሞ ህዝብ ነውና፣ የጋሞ ህዝብ እንኳን ደስ አለህ” ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ ይሄን ሽልማት ያበረከተልን ድርጅት “ሰላም ከሌለ ቢዝነስ የለም” ይላል፤ ጋሞ ደግሞ “ሰላም ከሌለ ህይወት የለም ብሎ ያምናል” ሲሉም የሰላምን ፋይዳ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡
በጋሞ ግጭትና ሞት ወይም መፈናቀል የለም ያሉት ተወካዩ፤ ”ለዚህም ምክንያቱ እኛ በሞት መሃል ነው የምንገባው፤በሚወረወር ቀስት መሃል እንገባለን፤ ህዝብ ከሚያልቅ ሁለት ሽማግሌ ሞቶ ትውልድ ቢተርፍ ይሻላል” ብለዋል፡፡
ለሰላም የሚንበረከኩ ሁሉ በክብር ከፍ ይላሉ ያሉት የጋሞ አባቶች ተወካይ፤ በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍሎች ያሉ ሽማግሌዎች ለሰላም ይንበረከኩ ዘንድ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡
የ10 ሚሊዮን ብር ሽልማቱን ላበረከቱት የአንቴክስ ኢትዮጵያ መሥራችና ባለቤት ሚ/ር ቻን ዋ፣ ምስጋናና ምርቃት ያቀረቡ ሲሆን፤ “የውጭ ሰው ቢሆንም የእግዚአብሄር መላዕክተኛ ነው” ብለዋል፡፡ እንደ ማር የሚጣፍጥ ንግግራቸውን ሲቋጩም፤ “እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ጨምሮ ጨማምሮ ይባርካት” በሚል ምርቃት ነው፡፡
በህመም ምክንያት በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ ያልተገኙት የኢኮኖሚ ዘርፍ አሸናፊው ኢንጂነር ቢጃይ ናይከር፣ በልጃቸው አማካይነት ባስተላለፉት መልዕክት፣ በሽልማቱ ያገኙትን 10 ሚሊዮን ብር በፌስቡክ ላይ ወጣቶችን አወዳድረው ለ62 አሸናፊዎች መልሰው እንደሚያበረከቱት አስታውቀዋል፡፡
ድምጻቸውን በመስጠት ለአሸናፊነት ላበቋቸው ደጋፊዎቻቸው ሁሉ ጥልቅ ምስጋናቸውን በልጃቸው በኩል አቅርበዋል - ኢንጂነሩ ኢንቬስተር፡፡
”ሰላም ከሌለ ንግድ የለም“ (No Peace, No Business) በሚል መርህ በተዘጋጀው በዚህ ውድድር፤ እጩ ተሸላሚዎቹ የተመረጡት 30 በመቶ በህዝብ ድምጽ፣ 70 በመቶ ደግሞ በዳኞች ድምጽ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ በሁለቱም ዘርፎች ለመወዳደርና እጩ ተሸላሚ ለመሆን ዘጠኝ ዘጠኝ መስፈርቶች ተቀምጠዋል፡፡ በኢኮኖሚ ዘርፍ ከተዘረዘሩት ዘጠኝ መስፈርቶች የመጀመሪያዎቹ አራቱ፡- ከትንሽ ተነስቶ በራሱ ጥረት የተሻለ ደረጃ ላይ መድረስ የቻለ፣ ለብዙዎች የሥራ በር የከፈተ፣ በሥራ ፈጠራ የተካነ፣ ህዝብና አገርን ለመጥቀም የሚሰራ-- ይላሉ፡፡ በተመሳሳይ በሰላም ዘርፍ ከተዘረዘሩት መስፈርቶች የመጀመሪያዎቹ አራቱ፡- በአመለካከቱ፣ በንግግሩ፣ በአኗኗሩ ሰላምን ከፍ የሚያደርግ፤ ለሰብአዊ መብት መከበር ግድ የሚለው፤ ዋጋ ከፍሎ በህብረተሰብ መካከል እርቅን ለማውረድ የሰራ፤ ይቅርታን እየኖረ፣ ይቅርታን የሰበከ-- የሚሉ ናቸው፡፡
በዚህም መሰረት የሚከተሉት የሰላም ዘርፍ እጩ ተሸላሚዎች ሆነው ተመርጠዋል፡፡
ብጹዕ አቡነ ኤርምያስ
የጋሞ የዕርቅ አባቶች
የድምጻችን ይሰማ አባላት
ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ
ድምጻዊ ታሪኩ ካንጊሲ (ጂሽካጊና)
የኢኮኖሚ ዘርፍ እጩ ተሸላሚዎች ሆነው የተመረጡት ደግሞ እነሆ፡፡
ኢንጂነር ቢጃይ ናይክር
ወጣት ኢዘዲን ከሚል
ዶ/ር መሃመድ ሽኩር
ወ/ሮ በረከት ወርቁ (በረከት ገበሬዋ)
ዶ/ር ዘሩ ገብረሊባኖስ
በሁለቱም ዘርፎች የተመረጡት እጩ ተሸላሚዎች፤ ከ2 ኪ.ግ ንጹህ ብር የተሰራ ዋንጫ የተሸለሙ ሲሆን፤ በየበኩላቸው ላበረከቱት አስተዋጽኦ ይፋ ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል - በዕለቱ በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ በተዘጋጀው ታላቅ ሥነስርዓት፡፡
በሚያስገርም ሁኔታ፣ የዚህ ውድድርና ሽልማት አዘጋጅ፣ የአንቴክስ ኢትዮጵያ መሥራችና ባለቤት ሚ/ር ቻን ዋ፤ ከዕለቱ እንግዶች ታላቅ ክብርና አድናቆት ጎርፎላቸዋል፡፡ በእጅጉም ተመስግነዋል፡፡
በሥነስርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሃፊ ቄሲስ ታጋይ ታደለ ባደረጉት ንግግር፤ “ዛሬ በጣም ደስ የሚል ቀን ነው፤ ኢትዮጵያ እንዲህ ሰላምን መፈለግ ከጀመረች ለውጥ ታመጣለች፤” ብለዋል፡፡
አንቴክስ ኢትዮጵያን በተመለከተም በሰጡት አስተያየት፤ “ሌሎች የውጭ ድርጅቶች የጸጥታ ችግር ሲፈጠር ሥራቸውን ዘግተው፣ ሠራተኞቻቸውን በትነው ሰላም ወዳለበት አገር ይሄዳሉ፤ አንቴክስ ግን የሰላም ሁኔታውን ማሻሻል ይቻላል በሚል እምነት የመፍትሄ አካል ነው የሆነው፡፡ ይሄ በእጅጉ ያስመሰግነዋል፡፡ ለሌሎችም አርአያ የሚሆን ተግባር ነው፡፡” ሲሉ አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡
ሌላዋ የክብር እንግዳ የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ወ/ሮ መሰንበት ሸንቁጤ በበኩላቸው፤ ለአንቴክስ ኢትዮጵያ መሥራችና ባለቤት ትልቅ ክብርና አድናቆት እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡ በተለይ አዳማ የጨርቃጨርቅ ፋብሪካን በጎበኙ ወቅት የሠራተኞቹን አያያዝ ተመልክተው መደመማቸውን ተናግረዋል፡፡
“ኢትዮጵያን ከማናችንም በተሻለ ይወዳታል፤ እንዲህ ዓይነት ቁርጠኛ ኢትዮጵያዊ ያልሆነ ሰው ማግኘት መታደል ነው፡፡” ብለዋል፤ ወ/ሮ መሰንበት፡፡
እ.ኤ.አ በ2017 ዓ.ም ኢትዮጵያን ከጎበኟት በኋላ ከአገሪቷና ህዝቧ ጋር በፍቅር ወደቅሁ የሚሉት የአንቴክስ ኢትዮጵያ መሥራች ሚ/ር ቻን ዋ፤ ወዲያው ያለአንዳች ማመንታት ኢንቨስት ለማድረግ መወሰናቸውን ያስታውሳሉ፡፡ በንግግራቸው የቻይናን ስኬት እያጣቀሱ የኢትዮጵያን ሁኔታ የሚያስረዱት ሚ/ር ቻን፤ ለቻይና ከፍተኛ የዕድገት ስኬት ሁለት መሰረታዊ ምሰሶዎች አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ይገልጻሉ፡፡ አንዱ ላለፉት 40 ዓመታት ቻይና በዘላቂ ሰላምና የተረጋጋ ሁኔታ ውስጥ መዝለቋ ነው ለስኬት ያበቃት ይላሉ፡፡ አንዱ ምሰሶ ሰላም ነው፡፡
ሰላም ብቻ ግን ለአንድ አገር ልማትና ብልጽግና በቂ አይደለም ባይ ናቸው፤ ቻይናዊው ኢንቬስተር፡፡ ሁሉም ዜጎች (በዕድሜ፣ በጾታ፣ በዘር፣ በሃይማኖትና በአመለካከት የተነሳ ልዩነት ሳይደረግባቸው) በአገሪቱ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ውስጥ በእኩልነት መሳተፍ አለባቸው፤ እኩል ዕድል ማግኘት ይገባቸዋል፡፡ ለዜጎች ሁሉ እኩልና ፍትሃዊ ዕድል መኖር አለበት፤ ሁለተኛው ምሰሶ ይሄ ነው ሲሉ፣ የቻይናን የዕድገትና ብልጽግና ምስጢር ያስረዳሉ፡፡ ኢትዮጵያ ይሄን ማድረግ ከቻለች ከቻይናም ባጠረ ጊዜ ስኬትን እንደምትቀዳጅ በልበሙሉነት ይናገራሉ፤ ሚ/ር ቻን፡፡
አንቴክስ ኢትዮጵያ ላለፉት 7 ዓመታት በአገሪቱ ውስጥ በነበረው ቆይታ፣ ያሉትን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ውጣ ውረዶች በመገንዘብ፣ መፍትሄ የማፈላለግ ሂደት ውስጥ የራሱን ሚና ለመወጣት ባቋቋመው ፉድ ኤንድ ፕላስ የተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት አማካኝነት በርካታ እርዳታዎችና ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱ ይነገራል፡፡
በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ልማትና ሰላም ዘርፍ የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ድርጅቶች ዕውቅና የሚሰጥ ምርጥ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሥራዎች (Best Influencer Work Prize) ሽልማትም የዚሁ እንቅስቃሴ አካል ነው፡፡ የBIW Prize ዓላማም፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማምጣት በተለየ መንገድ ጥረት ለሚያደርጉና በህዝቡ መካከል ሰላማዊ አብሮነትን ለማጎልበት ለሚተጉ፣ በሥራቸውም ለሌሎች አርአያ መሆን የቻሉ ግለሰቦችና ድርጅቶችን ማበረታታትና ሥራቸውንም ማገዝ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡
የዛሬ ሁለት ወር ገደማ በአዳማ የኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ አንቴክስ ኢትዮጵያ በሰጠው መግለጫ፣ የBIW Prize በየዓመቱ እንደሚካሄድ አስታውቋል፡፡ በእርግጥም “ሰላም ከሌለ ንግድ የለም” - (ኖ ፒስ ኖ ቢዝነስ) ለሚለው ጉዳይ፣ ሁሉም በቢዝነስ ላይ የተሰማሩ ወገኖች ትኩረት ሊሰጡትና ለመፍትሄውም የድርሻቸውን ሊያዋጡ ይገባል፡፡ በዚህ ረገድ የአንቴክስ ኢትዮጵያ ፈር ቀዳጅ ተግባር ለብዙዎች አርአያ እንደሚሆን ይታመናል፡፡
አንቴክስ ኢትዮጵያ በአዳማ ኢንዱስትርያል ፓርክ ከ10 በላይ ሼዶች ያሉት ሲሆን፤ ለ4500 ሰራተኞች የሥራ ዕድል የፈጠረ ድርጅት ነው፡፡ ድርጅቱ የስፖርት ልብሶችን፣ የውስጥ ልብሶችን፣ የተጠለፉና የተሸመኑ ልብሶችን፣ እንዲሁም ሁሉንም ዩኒፎርሞች እያመረተ ወደ ውጭ ገበያ ያቀርባል፡፡ አንቴክስ ግሩፕ፤ እ.ኤ.አ በ2003 ዓ.ም በቻይና የተመሰረተ ኩባንያ ሲሆን፣ ከቻይና በተጨማሪም በእስያና በአፍሪካ በጨርቃጨርቅና ሌሎች ዘርፎች ላይ እየሰራ የሚገኝ ድርጅት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
የውድድርና ሽልማት ዝግጅቱን ከጅምሩ እስከ ፍጻሜው ያስተባበረው በሻቱ ቶለማርያም መልቲሚዲያ ሲሆን፤ ይሄን ፕሮጀክት በአስገራሚና አስደናቂ ብቃት በመወጣቱ ሊመሰገን ይገባዋል፡፡ በተለይ በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ የተዘጋጀው የሽልማት መርሃ ግብር ለብዙዎቹ የአገራችን ኹነት አዘጋጆች መማሪያ የሚሆን ነው፡፡ ጥንቅቅ ያለ ጥራቱን የጠበቀ መርሃግብር ነው ያዘጋጀው - በሻቱ ቶለማርያም መልቲሚዲያ፡፡

“ህ ዝቡን ለተደራረበ የግብር ወጪ የሚዳርግ ነው


የታክስ አስተዳደርን እንደሚያዘምን የተነገረለት የንብረት ታክስ ረቂቅ አዋጅ ትችት የቀረበበት ሲሆን፤ አዋጁ ጸድቆ ወደ ተግባር ከመገባቱ በፊት ሕዝብ ሊመክርበት ይገባል ተብሏል።
ይህ የተነገረው ከትላንት በስቲያ ሐሙስ ታህሳስ 17 ቀን 2017 ዓ.ም. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ላይ በተደረገ ውይይት ነው። በውይይቱም ከምክር ቤት አባላት የተለያዩ አስተያየቶች የተሰነዘሩ ሲሆን፤ ስለ ዓዋጁ ሰፋ ያለ ማብራሪያም ተሰጥቷል።
ረቂቁን ለቋሚ ኮሚቴው አባላት ያቀረቡት የገንዘብ ሚኒስቴር የሕግ ጉዳዮች መመሪያ ሃላፊ አቶ ተወዳጅ መሃመድ ናቸው፡፡ ሌሎች አገራት ተንቀሳቃሽ ንብረቶች ላይ የንብረት ታክስን እንደሚጥሉ የጠቆሙት ሃላፊው፤ ኢትዮጵያ ግን ተሽከርካሪ ወይም ተንቀሳቃሽ ንብረት ላይ ታክሱን ተግብራ እንደማታውቅ ተናግረዋል፡፡ በዚህም ማብራሪያ ላይ እንደተጠቆመው፣ በንብረት ታክስ አማካይነት የሚሰበሰበው ገቢ በየከተሞቹ ለሚከናወኑ የተለያዩ የልማት ስራዎች ይውላል። በተጨማሪም፣ ከሌሎች የታክስ ሥርዓቶች ይልቅ ለቁጥጥር ቀላልና ግልጽ ነው ተብሏል፡፡
ረቂቅ አዋጁ ሲዘጋጅ የሌሎች አገራትን ተሞክሮ በጥናት ለመዳሰስ ጥረት መደረጉ የተገለጸ ሲሆን፤ ከዚህ ቀደም በጣሪያና ግድግዳ፣ በቤት ግብርና በመሳሰሉ አነስተኛ ገንዘብ ሲሰበሰብ እንደቆየ ተጠቁሟል፡፡ ከተሞች ከእነዚህ የተለያዩ ገቢዎች ውስጥ ለልማት ከሚያስፈልጋቸው የገንዘብ መጠን የሚያገኙት 1.8 በመቶውን ብቻ መሆኑም ተመልክቷል፡፡
ይህንን ለማሻሻልና ለከተሞች ዘላቂ ለውጥ ለማምጣት ሲባል ረቂቅ ዓዋጁ እንደተዘጋጀና በባሕር ዳር፣ መቐለ እና ድሬዳዋ ከተሞች ለአዋጁ እንደ ግብዓት የሚያገለግል ጥናት መደረጉን ተመልክቷል። በረቂቅ አዋጁ ላይ እንደሰፈረው ከሆነ፤ አጠቃላይ ንብረቱ ካለው ግምት 25 በመቶ ተወስዶ፣ ከእርሱ ላይ 0.2 በመቶ ቢጣል ተብሎ ቀርቧል።
የንብረት ታክስ ከሌሎች የታክስ ዓይነቶች የሚለየው ግብር ከፋዩ “ይህን ያህል መክፈል እችላለሁ” ብሎ  የሚያቀርበው ሳይሆን፤ በከተሞች ውሳኔ ተተምኖ የሚሰበሰብ ነው ተብሏል፡፡
በዚህ ውይይት ላይ ሃሳባቸውን የገለጹት የምክር ቤቱ አባል ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ፤ “ከዚህ ቀደም የኤክሳይዝ ታክስ አሻሽለናል፤ የተጨማሪ እሴት ታክስም እንደዛው። የመንግስት ሰራተኛው ላይ ከ25 እስከ 35 በመቶ የገቢ ግብር የሚከፍል ሲሆን፤ ለሚገዛቸው የተለያዩ ሸቀጣሸቀጦች ተጨማሪ ዕሴት ታክስ ተጥሎበታል። አሁን ደግሞ የንብረት ታክስ ይጠበቃል። ይህ ደግሞ ሕዝቡን ለተደራረበ የግብር ወጪ መዳረግ ነው” ሲሉ ተናግረዋል፡፡ አክለውም፤ ረቂቅ ዓዋጁ “ይፈጥረዋል” ያሉትን ጫና የንግዱ ማሕበረሰብ መቋቋም እንደሚችል በመግለጽ፣ ረቂቅ አዋጁ በሌላው ማሕበረሰብ ላይ ከፍተኛ ችግርና መማረር እንዳይፈጥር ስጋት እንዳላቸው አንስተዋል።
“የንብረት ታክስ አዋጅ ግብሩ የተሻለ ገቢ ባለው ላይ ነው ‘የሚጣለው’ ይላል። ኢትዮጵያ ውስጥ የተሻለ ገቢ ስንት ነው? ኢትዮጵያ ውስጥ የተሻለ ገቢ ያለውስ ማን ነው? የገቢው መነሻስ ስንት ነው?” ሲሉ ዶ/ር ደሳለኝ ሞግተዋል፡፡ ዶ/ር ደሳለኝ አክለውም፤ “እዚህ ቤት ብዙ ሰው ስጋት አንስቷል። በተደጋጋሚ የተለያዩ ስጋቶችን እናነሳለን። ድምጽ ስንሰጥ ግን ድምጽ የሚሰጠው ሰው ምክር ቤት ውስጥ ከሚሰጠው አስተያየት ጋር አይገናኝም። አንዳንዴ እንደ ምክር ቤት አባላትና እንደ ሕዝብ ተወካይነታችን፣ ስጋታችን በምንሰጠው ድምጽ በኩል መንጸባረቅ አለበት ብዬ አምናለሁ።” በማለት መልዕክታቸውን አጋርተዋል።
ሌሎች የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው፣ አዋጁ ጸድቆ ወደ ስራ ከመግባቱ በፊት ግልጽ በሆነ መልኩ ህዝቡን ማወያየት እንደሚገባ አሳስበዋል። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ በበኩላቸው፤ “የታክስ ገቢን ማሳደግና የዕዳ ክምችትን መቀነስ የሪፎርሙ አንዱ አካል ከመሆኑ አንጻር ረቂቅ ዓዋጁ የታክስ አስተዳደሩን ለማዘመን ያግዛል።” ሲሉ አስረድተዋል፡፡

 

 

የሲቪክ ተቋማት በነፃነት የሚሰሩበት ምህዳር እንዲፈጠር ተጠይቋል


በለውጡ ማግስት የሲቪክ ተቋማት በነፃነት እንዳይንቀሳቀሱ የሚያግዱና የሚያፍኑ ህጎች መሻሻላቸውን ተከትሎ፤ ምህዳሩ የበለጠ ምቹና ነፃ እንደሚሆን ብዙዎች ጠብቀው ነበር፡፡ በእርግጥም ላለፉት 4 እና 5 ዓመታት በአንፃራዊነት የተሻለ እንቅስቃሴ ታይቶ ነበር፡፡ በርካታ ሲቪል ተቋማት ተመስርተዋ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን ሁኔታዎች ፈፅሞ ተለይተዋል ይላሉ - የሰብአዊ መብ ተሟጋቾች፡፡
ከሰሞኑ አንጋፋው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) እና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት አዳዲስ ተሟጋቾች ማዕከል ባወጡት መግለጫ፤ በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶ ባለስልጣን መታገዳቸውን አስታውቀዋል፡፡ ድርጅቶቹ የታገዱት “ከተቋቋሙበት ዓላማ ውጪ ሲንቀሳቀሱ ተገኝተዋል” በሚል ምክንያት መሆኑን ጠቁመዋል።
ኢሰመጉ ከትላንት በስቲያ ታሕሳስ 17 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፣ በተሻሻለው የሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ዓዋጅ መሰረት ተመዝግቦ ሲንቀሳቀስ ቢቆይም፣ ታሕሳስ 14 ቀን 2017 ዓ.ም. ከሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን በተጻፈ ደብዳቤ መታገዱን አመልክቷል። ድርጅቱ ለዕግድ የበቃበትን ምክንያት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሲገልጽ፣ ከተቋቋመለት ዓላማ ውጪ እየተንቀሳቀሰ መሆኑንና፣ ገለልተኛ እንዳልሆነ ጠቁሞ፣ እ.ኤ.አ. በ2023 የበጀት ዓመት የአስተዳደር ወጪ ገደብ ጠብቆ እንዳልሰራና ሃላፊነት በጎደለው መልኩ እንደተንቀሳቀሰ በደብዳቤው ላይ ጠቅሷል።
በአሁኑ ሰዓት ዕግዱ በሚነሳበት ሁኔታ ላይ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጋር በመነጋገር ላይ እንደሚገኝ የገለፀው ኢሰመጉ፣ “የገጠመንን ተግዳሮት በንግግር በመፍታት አሁንም ቢሆን ለሰብዓዊ መብት መከበር፣ ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታና ለሕግ የበላይነት የአገራችንን ሕግና ስርዓትን በመከተልና የድርጅታችን ሕገደንብ በሚፈቅድልን መሰረት እንደ ሁልጊዜው በገለልተኝነትና በሃላፊነት መንፈስ ስራችንን በትጋት ለመወጣት እንጥራለን” ብሏል፣ በመግለጫው።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ማዕከል በበኩሉ፣ ከትላንት በስቲያ ሐሙስ ታሕሳስ 17 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፤ ታህሳስ 16 በደረሰው ደብዳቤ፣ ድርጅታቸው ከማንኛውም እንቅስቃሴዎች እገዳ እንደተጣለበት ማወቁን ጠቁሟል። አያይዞም፣ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የተላከለት ደብዳቤ የተጻፈው ታሕሳስ 14 መሆኑን ገልጾ፣ እንደ ኢሰመጉ ሁሉ ማዕከሉ የታገደው “ድርጅቱ ከተቋቋመበት ዓላማ ውጭ በመንቀሳቀሱና ገለልተኛ ባለመሆኑ” በሚሉ ምክንያቶችና “ግልጽ የሆነ የአደረጃጀት መዋቅር የሌለው ነው” በሚል ክስ እንደሆነ ተጠቅሷል።
በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ በባለስልጣን መ/ቤቱ በተጻፈው ደብዳቤ ማዕከሉ፤ “ሃላፊነት በጎደለው መልኩ የተንቀሳቀሰ መሆኑ በተደረገ ክትትልና ግምገማ ለማረጋገጥ ተችሏል” ብሏል። ይሁንና በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የቀረቡበትን ክሶች ያጣጣለው ማዕከሉ፣ “ድርጅታችን ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ከተቋቋመበት አላማ ውጭ በየትኛውም ያልተገባ ወይም ከህግ የሚጻረር እንቅስቃሴ ላይ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ተሳትፎ የማያውቅ መሆኑን ገልጷል” ሲል አትቷል።
ድርጅቱ አክሎም፣ በማያውቀው መልኩ ሃሳቡ በሕግ አግባብ ባልተጠየቀበት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ክትትልና ግምገማ ያካሄደ መሆኑን በመግለጽ፣ ያስተላለፈው ዕገዳ “አግባብነት ያለውና ሕግን የተከተለ ነው” ብሎ እንደማያምን በመግለጫው ጠቅሷል። በዕግዱ ዙሪያ “በቂ ማብራሪያ” እንዲሰጠው የሚጠይቅ ደብዳቤ ለባለስልጣኑ ማስገባቱንም ማዕከሉ አመልክቷል።
ባለስልጣኑ ይህንን ደብዳቤ ተመልክቶ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስም ድርጅቱ ከየትኛውም ሥራዎቹ መታገዱንና ጽሕፈት ቤቱም መዘጋቱን ድርጅቱ በመግለጫው አመልክቷል፡፡
ባለፈው ሕዳር ወር ውስጥ በጥቂት ቀናት ልዩነት የመብቶችና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ)፣ የሕግ ባለሞያዎች ለሰብዓዊ መብቶች ስብስብ ለሰብዓዊ መብቶች በኢትዮጵያ በባለስልጣኑ መ/ቤት የታገደ ሲሆን፤ ከቀናት በኋላ በድርጅቶቹ ላይ የተጣለው ዕግድ ቢነሳም፤ ካርድና የሕግ ባለሞያዎች ለሰብዓዊ መብቶች በድጋሚ መታገዳቸው ይታወሳል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ላይ እየተጣለ ያለው ዕገዳ አሳሳቢ መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል አስታውቋል፡፡
በተመሳሳይ፣ “የኢትዮጵያ መንግስት፣ የሰብአዊ መብቶች እንዲከበሩ የሚሰሩ ድርጅቶችን ማዋከብና፣ ማገድ ሊያቆም ይገባል” በማለት ዓለማቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ሂዩማን ራይት ሰዎች ህዳር 27 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ አሳስቦ ነበር። ተቋሙ አክሎም፤ በአገሪቱ የሲቪክ ተቋማት በነጻነት ሊሰሩበት የሚያስችል ምህዳር እንዲፈጠር ጠይቋል።
ይህ ዜና ማተሚያ ቤት እስከገባበት ሰዓት ድረስ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን የሰጠው መግለጫም ሆነ ማብራሪያ የለም።

 

 

አንጋፋው የሙዚቃ ባለሙያ ኤልያስ መልካ የቅንብር አሻራውን ያሳረፈበት የድምጻዊ አብርሃም በላይነህ (አብርሃም ሻላዬ) “ቀን በቀን” የተሰኘ አልበም ሊወጣ መሆኑ ተነግሯል። በአልበሙ ወጣትና አንጋፋ ባለሞያዎች እንደተጣመሩበት ተጠቅሷል።

የፊታችን ታኅሳስ 22 ቀን 2017 ዓ.ም. በድምፃዊው የዩቱዩብ ቻናል ለአድማጭ በሚደርሰው በዚሁ አልበም ላይ፣ የዚህ ትውልድ ቀለም የሆኑት ኤልያስ መልካና ሚካኤል ሃይሉ (ሚኪ ጃኖ) በላቀ ደረጃ በሙዚቃ ቅንብር የተጣመሩበት ሲሆን፤ ወንደወሰን ይሁብ፣ መሰለ ጌታሁን፣ ናትናኤል ግርማቸውና አንተነህ ወራሽን የመሳሰሉ የግጥምና ዜማ ሞያተኞች በአልበሙ ላይ ተሳትፈዋል።

“ቀን በቀን” አልበምን ሰርቶ ለማጠናቀቅ 9 ዓመታትን እንደፈጀ ተነግሯል።

ከአስራ ሦስት ዓመታት በፊት ለሙዚቃ አድማጮች ባደረሰው “ሻላዬ” የተሰኘ ባሕላዊ ነጠላ ዜማው ከፍተኛ ተወዳጅነትና ዕውቅናን ያተረፈው አብርሃም በላይነህ (አብርሃም ሻላዬ)፤ ለዓመታት በለቀቃቸው ነጠላ ዜማዎቹ በሙዚቃ አፍቃሪያን ዘንድ ከፍ ያለ ዝናን ከማትረፉም በላይ፣ “እቴ ዓባይ” በተሰኘ ስራውም በ“All African Music Award" አሸናፊ መሆኑ ይታወሳል፡

በዘውዴ አለልኝ የተጻፈው ‹‹ጊዜን መሸከም›› የተሰኘ የግጥም መድበል ለንባብ በቃ። መድበሉ 54 ግጥሞችን የያዘ ሲሆን በ162 ገጾች የተቀነበበ ነው፡፡

የመጽሐፉ ቅርጽ በዋሽንት አውታረ ቅኝት የተሠራ ሆኖ በጥቁር፣ ሰማያዊ፣ ሐምራዊና ነጭ ቀለማት የተከፋፈለ ነው። ቀለማቱ ከኢትዮጵያ ባህላዊ የሙዚቃ መሳሪያዎች ዋሽንት፣ ክራር፣ ነጋሪትና ሞረሽ ከምትባል ወፍ ጋር የተቀነባበረ ነው። እያንዳንዱ ክፍል ቀለማዊና ሙዚቃዊ ፍካሬ መግቢያ አለው።

የግጥም መድበሉ ታትሞ ለሽያጭ ተዘጋጅቷል፡፡ መጽሐፉን ለመግዛት የምትፈልጉ በኦንላይን ይዘዙን፡፡ ዋጋው ለአገር ውስጥ 350 ብር ሲሆን፣ ለውጭ ሀገር በ20 ዶላር ተተምኗል።


የባንክ ሂሳብ ቁጥር...
አቢሲኒያ ባንክ ( bank of abyssinia) 200869327 ዘውዱ አለልኝ አራገው ( zewdu alelgn aragaw)

ዳሽን ባንክ (Dashen bank) 5472769396011 ዘውዱ አለልኝ አራጋው ( zewdu alelgn aragaw)

ንግድ ባንክ (CBE ) 1000298476936 (Daniel abreha) ዳንኤል አብርሃ

ቴሌ ብር / tellebirr፦ 0913240885 zewdu alelgn

እባክዎ ክፍያ የፈጸሙበትን የባንክ ደረሰኝ Screenshot አድርገው፣ ወይም ፎቶ አንስተው በዚህ የቴሌግራም ሊንክ @Gizienmeshekem2424 ይላኩልን፡፡

በተለያዩ የፊልምና የመድረክ ተውኔቶች የምትታወቀው አርቲስት መስከረም አበራ፤ የኢቭ የሕጻናት ዳይፐር የብራንድ አምባሳደር ሆና ተመርጣለች። አርቲስት መስከረም ለብራንድ አምባሳደርነቱ የተከፈላትን ክፍያ በይፋ ከመግለጽ ተቆጥባለች።

ዛሬ ታህሳስ 19 ቀን 2017 ዓ.ም. በስካይላይት ሆቴል በተካሄደ መርሃግብር፣ ስለ አርቲስት መስከረም አበራ ሞያዊ አበርክቶና ስነ ምግባር፣ በደራሲና ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ተ/አረጋይና በተውኔት ደራሲና አዘጋጅ ዳግማዊ “አመለወርቅ” ፈይሳ አማካይነት የቀረበ ሲሆን፤ ኢቭ ሞዴስ እና የሕጻናት ዳይፐር፣ አርቲስት መስከረምን ለብራንድ አምባሳደርነት መምረጡ ተገቢ መሆኑን ተናግረዋል።

አርቲስት መስከረም በበኩሏ፤ ከኢቭ ሞዴስ ጋር የነበራትን ቀደም ያለ መስተጋብር በማውሳት፣ “ከራሴ ሴትነት ጋር በተገናኘ የ’ኢቭ’ን ምርት አውቀዋለሁ” ብላለች። አያይዛም፣ “ልጅ የለኝም፤ ነገር ግን ልጅ ለወለዱ ወዳጆቼ በመስጠት ምርቱን እንዲጠቀሙ አደርጋለሁ” ስትል ቃል ገብታለች።

የብራንድ አምባሳደርነቱ ለአንድ ዓመት የሚቆይ ሲሆን፣ የቢልቦርድ፤ የቴሌቪዥንና የራዲዮ ማስታወቂያዎችን መስራት የሚያስችላት መሆኑ ተነግሯል። አርቲስቷ ከአምራች ድርጅቱ ስለተከፈላት የገንዘብ መጠን በይፋ ከመግለጽ ተቆጥባለች።

“የእኔ ደስታ በሞያዬ መቆየት ነው፤ ፍላጎቴም የሕዝቡን ስሜት መረዳት ነው። የኢቭ ዳይፐር የብራንድ አምባሳደርነት የመጀመሪያ ስራዬ ይሆናል። ወደፊት ሌሎች ስራዎች ይኖራሉ” ብላለች፤ አርቲስት መስከረም አበራ፡፡

ኢቭ ሞዴስ እና ዳይፐርን የሚያመርተው ጊዮፒዮን የንጽህና መጠበቂያ ግብዓቶች አቅራቢ ድርጅት፣ በኢትዮጵያ ስራውን ከጀመረ 16 ዓመታት ያስቆጠረ ሲሆን፤ የተለያዩ የጥራት ሽልማቶችን እንዳሸነፈ ለማወቅ ተችሏል።

ዳሸን ባንክ የሴቶችን የመሪነት ሚና ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያስችል መርሃ ግብር አስጀምሯል፡፡ መርሃ ግብሩ የሴት ሰራተኞቹን አቅም ይበልጥ ለማጎልበት ያስችላል ተብሏል።


በመርሃ-ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ንግግር ያደረጉት የባንኩ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አፋው ዓለሙ፤ “ዛሬ የምንኮራባቸው የአገራችን ታሪካዊ ድሎችን እንድንጎናፀፍ ሴቶች ከፍተኛ አስተዋፅዎ አበርክተዋል” ብለዋል፡፡


ከታላላቅ አገራዊና ተቋማዊ ስኬቶች ጀርባ የሴቶች ሚና የጎላ መሆኑን የገለጹት አቶ አስፋው፤ ሴቶች ተገቢው ዕውቅና ሊሰጣቸው እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡


ዳሸን ባንክ ይህን ክፍተት በአግባቡ ተገንዝቦ የሚሰራ በመሆኑ ከምስረታው ጀምሮ ሴቶችን በከፍተኛ የአመራር እርከኖች ላይ በመሾም ወደፊት በማምጣት ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡


ባንኩ ሴቶችን በአግባቡ ያካተተ አሰራር በመፍጠር አዳዲስ ፈጠራዎችንና ውጤታማነትን እንደሚያጎለብት ተመላክቷል፡፡


መርሃ-ግብሩ ባንኩ ሁሉም ሰራተኞች ዕኩል ዕድል የማግኘትና የማደግ አጋጣሚ እንዲያገኙ ለማድረግ ካለው ራዕይ ጋር አብሮ የሚሄድ እንደሆነም ተጠቁሟል፡፡


በዳሸን ባንክ የሰው ሐብት ዋና መኮንን ወ/ሮ ህይወቴ ከፈለኝ በበኩላቸው፤ “ፕሮግራሙ በባንካችን ወደፊት ከፍተኛ አመራር መሆን የሚችሉ ሴቶችን ከወዲሁ ለመለየትና ለማብቃት የተነደፈ ነው” ብለዋል፡፡


በተጨማሪም፣ የተሻለ ልምድ ያላቸውን ሴቶች ድጋፍ ከሚሹ ሴቶች ጋር በማገናኘት ጠቃሚ የሙያ ዕድገት እንዲያገኙ የሚያስችሉ ድጋፎችን ለመስጠት ያለመ እንደሆነም አብራርተዋል፡፡

በመድረኩ ላይ ሐሳባቸውን ያጋሩት የ'ሴታዊት ንቅናቄ' መስራች ዶ/ር ስህን ተፈራ፤ ዳሸን ባንክ ሴቶችን በሁሉም መስክ ብቁ ለማድረግ እየሰራ ያለው ሥራ ለሌሎች ተቋማት ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዋል።

Page 4 of 748