Administrator

Administrator

ጥንት በቀዝቃዛው ጦርነት ዘመን አንድ ምስኪን አሜሪካዊ፤ በአሜሪካኑ ሁዋይት ሐውስ ፊት ለፊት፣ ሣር ሲግጥ ይታያል፡፡ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሰገነታቸው ላይ ቆመው ይህ ዜጋ ሳር ሲግጥ በማየታቸው እጅግ ተደንቀው ያስጠሩታል፡፡
ፕሬዚዳንት፤
“ምን ሆነህ ነው ሳር የምትግጠው?”
ምስኪኑ ዜጋም፤
“ርቦኝ፡፡ ጠኔ ሊገለኝ ሲሆን ሳርም ቢሆን ልቅመስ ብዬ ነው!”
ፕሬዚዳንት፤
“በል በቃህ፡፡ ለአምስት ዓመት በቀን ሶስት ጊዜ ማክዶናልድ (ሀምበርገር) በእኔ ሂሳብ ትበላለህ”፤ ግን ሥራ ፈልግ” ብለው አሰናበቱት፡፡ ተደስቶ ጮቤ እየረገጠ ሄደ፡፡
አምስት ዓመት በላ፡፡ አምስት ዓመት ጠገበ፡፡ ሥራ ግን አሁንም አላገኘም!
ስለዚህ ወደ ሩሲያ ሄደ፡፡ ሩሲያ ጥቂት እንደቆየ መራብ ጀመረ፡፡ ረሀቡን ለማስታገስ ወደ ዋናው የመንግሥት መናኸሪያ ወደ ክሬምሊን ሄደ፡፡ ከዚያም ፊት ለፊት ያገኘውን ሣር መጋጥ ጀመረ፡፡ የሩሲያው ፕሬዚዳንት ብሬዤኔቭ አዩት፡፡ ነገሩ ገርሟቸው አስጠሩት፡፡ በአጃቢ ገብቶ ፊታቸው ቀረበ፡፡ ብሬዥኔቭም፤
“ምን ሆነህ ነው እንዲህ እየተስገበገብክ ሳር የምትግጠው?” ሲሉ ጠየቁት፡፡
ምስኪኑ አሜሪካዊም፤
“ርሃብ! ጠኔ ሊገለኝ ነው ክቡር ፕሬዚዳንት!”
ፕሬዚዳንቱ ትንሽ አቅማሙና፤
“ታዲያ ለነገዬ አትችልም? ፕላንድ ኢኮኖሚ አታውቅም? በአንድ ቀን ግጠህ ልትጨርሰው ነው?” ብለው ኢኮኖሚያዊ ግሳፄ ሰጡት!!
*   *   *
አሜሪካኖች ሥራ ከመስጠት ይልቅ፤ ብር መስጠት ወደዱ፡፡ ሩሲያውያን በባዶ ሆድህ ቁጠባን ዕወቅ አሉ፡፡ ዓለም እንደዚያ ነበረች፡፡ ከዚያ ይሰውረን!
ለያዥ ለገራዥ ያስቸገረው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ፤ ዛሬም በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሆነ አለ! የዓለም ባንክና የዓም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ዘገባዎች፤ (የአየለ አይኤምኤፍን ነብስ ይማር!) በኢትዮጵያ ኑሮና ካዝና አንፃር፡-
“ላም አለኝ በሰማይ
ወተቷንም አላይ” ናቸው፡፡ እንጂ እንደ  ካፒታሊስቶቹ ምኞትማ፡-
“ላም አለኝ በሰማይ
ወተቷ እሚከራይ!” በሆነ ነበር!
ከሁሉም ያውጣን!
“ገንዘቤን የወሰደ ሰው፣ ወሰደ እንበል ከንቱ ነገር የእኔም የሱም የዚያም ነበር
ግና ስሜን የሰረቀኝ የማያከብረውን ወስዶ፣ እኔን በግልፅ አደኸየኝ” (ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን)
ከማለት ሌላ ምን አቅም አለን፡፡
ካርል ማርክስ እንደሚለንም፤
“ፖለቲካ የኢኮኖሚ ጥርቅም መልክ ነው” (Politics is the concentrated form of economics)
ይህ እንግዲህ በሀገራችን ተሾመም፣ ተመረጠም፣ መሪ የሆነ ሰው፤ የፖለቲካም የኢኮኖሚም የአደራ ዕዳ እንዳለበት ነው፡፡ የህዝቡ ኑሮ እጅግ ጠያቂ ነው፡፡ ማንንም አይምርም! ይፈታተናል፡፡ ብልህ መሪ፤ አስተዋይ፣ ሆደ - ሰፊ፣ ትዕግሥቱን በብዛት የሰጣቸውን ባለ ራዕይ ጠቢባን የኢኮኖሚ ባለሙያዎችን በዙሪያው ሰብስቦ፡-
“ነገርን ከሥሩ
ውሃን ከጥሩ”
ማጤን ይጠበቅበታል!
“ጣሊያን ሊማሊሞን በመድፍ ሲደበድበው አደረ” ቢሉት፤
“ተወው ይበለው! እሱም መገተሩን አብዝቶት ነበር” አለ አሉ የጎንደር ሰው፡፡ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ግን በመድፍም ቢመታ ውልፊት አይልም! እንኳንስ በአንድ ጀምበር በአያሌ ጀምበሮችም የማይነቀነቅ ስለሆነ፣ “እንኳን ተለያይተን አንድ ሆነንም አስቸጋሪ ነው” ማለት ትክክለኛ አቅጣጫ ነው!
ተባብረን የኢኮኖሚያችንን ነገር ምን እናድርገው? እንባባል!
የቀድሞ፣ ቀድሞ መሪያችንን ራዕይ ብቻ የሙጥኝ በማለት አንወጣውም! ከአዳጊው ሁኔታ ጋር ምን ምን የኢኮኖሚ መንገድ እንቀይስ ካልተባባልን፣ የተሾመን የሚሽር፣ የመጣን የሚያወርድ አደጋ ፊታችን ላይ ተደቅኗል! እንደ ወትሮው፣
“ብቆጣም እመታሻለሁ፤ ብትቆጪም እመታሻለሁ” ዓይነት ዲሞክራሲ ዛሬ ወንዝ አያሻግርም! ደጋግመን “ፖለቲካው የኢኮኖሚው ጥርቅም መልክ ነው!” የሚለውን ጥልቅ አስተሳሰብ፤ በጥልቅ ግምገማም ቢሆን እንመርምረው!
ለክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች
መልካም የዳግማይ ትንሣዔ በዓል!

 ትዝ ይለኛል የዛሬ አስራ አራት አመት ነው፡፡ ከባለቤቴ ጋር አብረን ለመኖር ስወስን አንድ የቅርብ ወዳጄን ላገባ ነው ብዬ አማከርኩት፡፡ “እሱም ትዳር ጥሩ ነው፤ አግባ ግን ሪሞት ኮንትሮልህን አሳልፈህ እንዳትሰጥ” አለኝ፡፡ የመጀመሪያዎቹን ስድስት ወራት ሪሞት ኮንትሮሉን ላለመስጠት ብዙ ታገልኩ። ግን አልቻልኩም ፍቅር አሸነፈኝ፡፡ እናም ሪሞት ኮንትሮሉን አሳልፌ ሰጠሁ፡፡
ይህን በማድረጌ ግን ሦስት በዚህ ዓለም ላይ ካሉ ጥሩ ነገሮች ሁሉ አብልጬ እምወዳቸው ውብ ልጆች አተረፍኩ፡፡
ታዲያ ሁሌ የቴሌቪዥኔን ሪሞት ኮንትሮል ባየሁ ቁጥር፣ ያ ወዳጄ ትዝ ይለኛል፡፡ አንዳንዴ ደግሞ አስባለሁ፤ አሁን እሳት ቢነሳ እማድነው ሪሞት ኮንትሮሉን ነው ወይስ ቴሌቪዥኑን? የሚቀለው ሪሞት ኮንትሮሉን ብድግ አድርጎ መሮጥ ነው፤ ግን ቴሌቪዥኑ ከሌለ ሪሞት ኮንትሮሉ ብቻውን ምን ይሰራል? ቢከብድም ቴሌቪዥኑን ማዳን ግን  ይጠቅማል፤ ምክንያቱም ቴሌቪዥኑ ከዳነ በኋላ ሪሞት ኮንትሮሉ በቀላሉ ስለሚገኝ፤ ባይገኝም  ቴሌቪዥኑ ምቾት ይቀንሳል እንጂ ያለ ሪሞት ኮንትሮል ማሳየት ስለሚችል! አሁን ሀገራችንን  እንደ ቴሌቪዥን፣ ስልጣንን ደግሞ እንደ ሪሞት ኮንትሮል እንይ፡፡
እሳት ሀገራችን ላይ ተነስቷል፡፡ እምናተርፈው ሪሞቱን ነው ወይስ ቴሌቪዥኑን? 180 አሁን ይህ ቁጥር ለሐገራችን ብዛትን መግለጫ ተራ ቁጥር አይደለም፡፡ ይህ ቁጥር ቀጣዩን የኢትዮጵያን እጣ ፈንታ የሚወስን ቁጥር ነው፡፡ እናንተ አንድ መቶ ሰማንያ ሰዎች!! ምናልባትም በታሪካችን ለመጀመሪያ ጊዜ ሀገራችሁ እጃችሁ ላይ ወድቃለች፡፡
ይህ ወቅት እንደ ሌላው ጊዜ እጅ አውጥታችሁና አጨብጭባችሁ የምትለዩት ወቅት አይደለም!! ይህ ወቅት እድሜ ልካችሁን በፀፀት ወይም በእርካታ የሚከተላችሁ ታሪካዊ ወቅት ነው!! እናም ተተኪውን ጠቅላይ ሚኒስትራችንን ስትመርጡልን.........ስለ ብሄር ሳታስቡ.......በተፅእኖ ሳትረቱ.........ስለ ምቾታችሁ ሳትጨነቁ.......በሆዳችሁም በልባችሁም ሳይሆን በጭንቅላታችሁ ብቻ አስባችሁ........... ለወከላችሁ ብሔር ብቻ ሳይሆን ሳይፈልጉ እጃችሁ ስር ለወደቁ መላ ኢትዮጵያውያን ጭምር ተጨንቃችሁ፣ ይህቺን አገር ከገባችበት አዘቅት የሚያወጣት፤ ኢትዮጵያውያንን  ከዞረብን የዘረኝነት አባዜ የሚያላቅቀን፤ እያደር በጥልቀት ከምንሰምጥበት ያስተሣሠብ ድህነት የሚያድነን፤ ከዘወትር ተመፅዋችነት የምንገላገልበትን አቅጣጫ የሚያሣየን፤ መሪ ምረጡልን!ሪሞት ኮንትሮሉን ሳይሆን ቴሌቪዥኑን አድኑልን፡፡ ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ፡፡
(ከቴዎድሮስ ተሾመ ፌስቡክ)

 ትዝ ይለኛል የዛሬ አስራ አራት አመት ነው፡፡ ከባለቤቴ ጋር አብረን ለመኖር ስወስን አንድ የቅርብ ወዳጄን ላገባ ነው ብዬ አማከርኩት፡፡ “እሱም ትዳር ጥሩ ነው፤ አግባ ግን ሪሞት ኮንትሮልህን አሳልፈህ እንዳትሰጥ” አለኝ፡፡ የመጀመሪያዎቹን ስድስት ወራት ሪሞት ኮንትሮሉን ላለመስጠት ብዙ ታገልኩ። ግን አልቻልኩም ፍቅር አሸነፈኝ፡፡ እናም ሪሞት ኮንትሮሉን አሳልፌ ሰጠሁ፡፡
ይህን በማድረጌ ግን ሦስት በዚህ ዓለም ላይ ካሉ ጥሩ ነገሮች ሁሉ አብልጬ እምወዳቸው ውብ ልጆች አተረፍኩ፡፡
ታዲያ ሁሌ የቴሌቪዥኔን ሪሞት ኮንትሮል ባየሁ ቁጥር፣ ያ ወዳጄ ትዝ ይለኛል፡፡ አንዳንዴ ደግሞ አስባለሁ፤ አሁን እሳት ቢነሳ እማድነው ሪሞት ኮንትሮሉን ነው ወይስ ቴሌቪዥኑን? የሚቀለው ሪሞት ኮንትሮሉን ብድግ አድርጎ መሮጥ ነው፤ ግን ቴሌቪዥኑ ከሌለ ሪሞት ኮንትሮሉ ብቻውን ምን ይሰራል? ቢከብድም ቴሌቪዥኑን ማዳን ግን  ይጠቅማል፤ ምክንያቱም ቴሌቪዥኑ ከዳነ በኋላ ሪሞት ኮንትሮሉ በቀላሉ ስለሚገኝ፤ ባይገኝም  ቴሌቪዥኑ ምቾት ይቀንሳል እንጂ ያለ ሪሞት ኮንትሮል ማሳየት ስለሚችል! አሁን ሀገራችንን  እንደ ቴሌቪዥን፣ ስልጣንን ደግሞ እንደ ሪሞት ኮንትሮል እንይ፡፡
እሳት ሀገራችን ላይ ተነስቷል፡፡ እምናተርፈው ሪሞቱን ነው ወይስ ቴሌቪዥኑን? 180 አሁን ይህ ቁጥር ለሐገራችን ብዛትን መግለጫ ተራ ቁጥር አይደለም፡፡ ይህ ቁጥር ቀጣዩን የኢትዮጵያን እጣ ፈንታ የሚወስን ቁጥር ነው፡፡ እናንተ አንድ መቶ ሰማንያ ሰዎች!! ምናልባትም በታሪካችን ለመጀመሪያ ጊዜ ሀገራችሁ እጃችሁ ላይ ወድቃለች፡፡
ይህ ወቅት እንደ ሌላው ጊዜ እጅ አውጥታችሁና አጨብጭባችሁ የምትለዩት ወቅት አይደለም!! ይህ ወቅት እድሜ ልካችሁን በፀፀት ወይም በእርካታ የሚከተላችሁ ታሪካዊ ወቅት ነው!! እናም ተተኪውን ጠቅላይ ሚኒስትራችንን ስትመርጡልን.........ስለ ብሄር ሳታስቡ.......በተፅእኖ ሳትረቱ.........ስለ ምቾታችሁ ሳትጨነቁ.......በሆዳችሁም በልባችሁም ሳይሆን በጭንቅላታችሁ ብቻ አስባችሁ........... ለወከላችሁ ብሔር ብቻ ሳይሆን ሳይፈልጉ እጃችሁ ስር ለወደቁ መላ ኢትዮጵያውያን ጭምር ተጨንቃችሁ፣ ይህቺን አገር ከገባችበት አዘቅት የሚያወጣት፤ ኢትዮጵያውያንን  ከዞረብን የዘረኝነት አባዜ የሚያላቅቀን፤ እያደር በጥልቀት ከምንሰምጥበት ያስተሣሠብ ድህነት የሚያድነን፤ ከዘወትር ተመፅዋችነት የምንገላገልበትን አቅጣጫ የሚያሣየን፤ መሪ ምረጡልን!ሪሞት ኮንትሮሉን ሳይሆን ቴሌቪዥኑን አድኑልን፡፡ ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ፡፡
(ከቴዎድሮስ ተሾመ ፌስቡክ)

 “--አጎዛውን ግድግዳ ላይ ሰቅለው፣ ለጌጥና ለዓይን ማረፊያ ያደርጉታል፡፡ ከዚያ ያወርዱና አንጥፈው ይተኙበታል፡፡ ሲተኙ ደግሞ ያሸትቱታል፡፡ እነዚህ የውበት ልምምዶች ሁለት አይነት ነገር አላቸው፤ ተግባራዊም ውበታዊም፡፡--”

    ተወልዶ ያደገው በጎጃም ገጠር ቢሆንም ያደገውና የተማረው በባህርዳር ከተማ ነው - ሰዓሊ እያዩ ገነት፡፡ የመጀመሪያ ድግሪውን ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ ቢያገኝም የነፍሴ ጥሪ እንዳልሆነ ስገነዘብ፣የወርልድ ቪዥን ሥራዬን ጥዬ፣ ወደ አዲስ አበባ መጣሁና የስዕል ት/ቤት ገባሁ ይላል፡፡ በትምህርቴ “ሰቅዬ” በመቅረት በስዕል    ት/ቤት ውስጥ የተወሰነ አበርክቶ ይኖረኛል የሚል እምነት ነበረኝ የሚለው ሰዓሊው፤ ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች ሳይሳካ ቀረና የሀይስኩል ተማሪዎችን በራሴ ተነሳሽነት፣ ስዕል ማስተማር ጀመርኩኝ ብሏል፡፡ በፋይን አርት ዲግሪውን ከአገኘ በኋላስ? የጥበብ ጉዞው ምን ይመስላል? ወደ ባህርዳር ይዤው ሄድኩ ስለሚለው ህልሙ ያወጋናል፡፡ ስዕል እንጀራ አይሆንም በሚል የሚንጸባረቀውን  አመለካከትም ይሞግታል። ስለ ምዕራቡ ዓለም የሥነ ጥበብ ፍልስፍና፣ “ነቁጥ” በሚል ስያሜ በጉራማይሌ የሥነጥበብ ጋለሪ ለዕይታ ስላቀረበው አውደ ርዕይ ያብራራል፡፡ ሰዓሊው በቅርቡ በግብጽና በኢኳዶር በሚካሄድ የሥነ ጥበብ ሲምፖዚየም ላይ እንደሚሳተፍም ይገልጻል፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ፤ ሰዓሊውን በጥበብ ህይወቱ ዙሪያ አነጋግራዋለች፡፡ እነሆ፡-  


   ስሜትህ ለስነ-ጥበብ እያደላ እንዴት ኢኮኖሚክስ ለመማር ዩኒቨርሲቲ ገባህ?
“ብልጥ ልጅ እየበላ ያለቅሳል” ይላሉ አበው። በውስጤ የስነ-ጥበብ ፍቅር ቢኖረኝም አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተገብቶ መማር እንደሚቻል የነገረኝ ወይም መንገዱን ያሳየኝ አልነበረም፡፡ ብቻ ባህርዳር ላይ ዘውዱ ባይሌ የሚባል ሰዓሊ ነበር (ነፍሱን ይማርና) ጋለሪ ከፍቶ የማስታወቂያ ስራ ሲሰራ እያየሁ፣ እሱን ነበር መሆን የምፈልገው፡፡ ነገር ግን በወቅቱ የትምህርት ውጤቴ ጥሩ ስለነበር ካሉት ትምህርቶች የተሻለ ነው ብዬ ያመንኩትን የኢኮኖሚክስ ትምህርት ልማር ቻልኩኝ፡፡
በተማርከው ትምህርት ሰራህበት ታዲያ? ከዚያስ እንዴት ወደ አለ የስነ ጥበብና ዲዛይን ት/ቤት ገባህ?
በኋላ ላይ ጥሪሽ እንዳልሆነ ሲገባሽ ሁሉም ነገር ትግልና ፈተና ይሆንብሻል፡፡ ላልተፈጠርንበት አላማ ምናልባት ችለን በእጃችን ልንሄድ እንችላለን ግን እጅ እንደ እግር እንደማይሆን የተረዳን ሰዓት፣ በእግር መሄድ ስንሞክርና በጣም ምቹ መሆኑን ስንረዳ በእጃችን የሄድንበትን ጊዜ እንፀፀትበታለን። ምን ለማለት ነው… ለአፍንጫም ለአይንም አሁን ካለበት የተሻለ ቦታ የለም። በኢኮኖሚክሱ ሰርተህበታል ወይ ላልሺኝ፤ እርግጥ ነው ወርልድ ቪዥን ገብቼ ስራ ጀምሬ ነበር፡፡ ነገር ግን ለዚያ ቦታና ስራ የተፈጠርኩ አለመሆኔ ሲገባኝና የነፍሴ ጥሪ አርት እንደሆነ ስረዳ፣ ወደ አዲስ አበባ መጥቼ አርት ት/ቤት ገባሁ፡፡ በወቅቱ ቤተሰቤም እንጀራ ትተህ ሄደህ እንጀራ አይወጣልህም ብለውኝ ነበር፤ ደስተኞችም አልነበሩም፡፡ እኔ ግን ትዝ ይለኛል፣ ወደ አዲስ አበባ ስመጣ በኪሴ የነበረው 300 ብር ብቻ ነበር። ጫማ ጠርጌም ቢሆን የተጠራሁበትን ዓላማ አሳካለሁ የሚለውን ህልም ይዤ ነው የወጣሁት። ከዚያ አራት አመት በአርት ስኩል ትምህርቴን ስከታተል ቆይቼ፣ በፋይን አርት ዲግሪዬን አገኘሁ፡፡
በስዕል ት/ቤት በነበረህ ቆይታህ ከመደበኛው ትምህርት ውጭ በራስህ ላይ የጨመርከውን ነገር ንገረኝ…?
እንደኔ አመለካከት ትምህርት አንቺን አይፈጥርሽም ግን የተፈጠረውን አቅምሽን ቅርፅ በመስጠትና አቅጣጫ በማስያዝ ከፍተኛ እገዛ ያደርግልሻል፡፡ እኔ በተለይ ከመምህራኖቼ በጣም የሚያስገርሙ አቅሞችን አግኝቻለሁ፡፡ እነ መዝገቡ ተሰማ፣ ታደሰ መስፍን፣ ጌታሁን አሰፋ፣ በቀለ መኮንንና ሌሎችም አመለካከትን ሊቀይሩ ከሚችሉ ሰዎች ጋር የመገናኘት ዕድል ማግኘትሽ ያለሽን ነገር ጥልቀት ይጨምርልሻል፡፡ በዚህ ምክንያት ለሙያው ያለኝ ጥማት ጨርሶ ነደደ፡፡ መጀመሪያም ፓሺን ነበረኝ፤ ትምህርቱ ደግሞ የበለጠ ፍቅርና ፍላጎቱን አቀጣጠለልኝ፡፡ እርግጥ ነው መጀመሪያ ላይ የሚያሳጣሽ ነፃነት አለ…፡፡
ምን አይነት ነፃነት ነው የሚያሳጣው?
የምንማርበት ሥርዓተ ትምህርት የተቀረፀው በምዕራቡ አስተሳሰብ ላይ ማዕከል አድርጎ በመሆኑና የአገራችንን ነባራዊ ሁኔታ ከግንዛቤ ውስጥ ስለማያስገባ በጣም ገዳቢ ነው፡፡ ነገር ግን አንቺ ብልህ ከሆንሽ ያንን ትምህርት ከራስሽ ሁኔታ አንፃር እየቃኘሽ መጠቀም ትችያለሽ፡፡ እኔም በት/ቤት ቆይታዬ ይህንን ሳደርግ ነው የቆሁት፡፡ ከዚያ በኋላ በነበረኝ ፍቅር… በውጤቴ ምክንያት እዚያው ት/ቤት በመምህርነት እቆያለሁ የሚል እምነት ነበረኝ፡፡ እንደው እዚያው ጨርሶ መቅረትም ባይሆን እንኳን የተወሰነ አበርክቶ ይኖረኛል የሚል ሀሳብ ነበረኝ፡፡ ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች ሳይሳካ ቀረና የሀይስኩል ተማሪዎችን በራሴ ተነሳሽነት፣ ደስ ብሎኝ ስዕል ማስተማር ጀመርኩኝ። ይህን እያደረግኩኝ ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ አርኪቴክቸር ዲፓርትመንት የማስተማር ዕድል አገኘሁ፡፡ እዛም ለአንድ ዓመት ያህል ሰራሁ፡፡
ብዙ የስዕል አውደ ርዕዮች ላይም ተሳትፈሃል…?
አውደ ርዕዮችን--- በአሊያንስ ኢትዮ ፍራንሴዝ፣ በጎተ ኢንስቲትዩት፣ በአሜሪካ ኤምባሲና በሌሎች ቦታዎች በቡድን አቅርቤአለሁ፡፡ ይህንን ሳደርግ ግን የቀደሙ አርቲስቶች የሚሰሩትን እንደምደግም እንጂ አዲስ ነገር እንደማልሰራ ተረዳሁ፡፡ ከዚያ አንድ ህልም ይዤ ወደ ባህርዳር ሄድኩኝ፡፡ እንደምታውቂው አለ የስነ-ጥበብና የዲዛይን ት/ቤት 50 ዓመት ሞልቶታል፡፡ ከዚያ የሚወጡ አብዛኞቹ ሰዓሊዎች እዚህ አዲስ አበባ ነው የሚሆኑት። ምክንያቱም አዲስ አበባ የብዙ ኤምባሲዎች፣ የዲፕሎማቶች መቀመጫ በመሆኗ ገበያው ያለው እዚሁ ስለሆነ ነው፡፡ ወደ ክልል አይወጡም፡፡ ክልል ላይ ደግሞ በተደራጀ መልኩ የሚካሄድ የአርት እንቅስቃሴ የለም፡፡ እኔ ደግሞ ባህርዳር ያደግኩባት ከተማ ናት፡፡ ቤተሰቦቼም ያሉት እዚያው ናቸው፡፡ ስለዚህ ባህርዳር የቱሪስት ከተማ በመሆኗ አማራጭ የስነ ጥበብ ከተማ (Alternative Art corner) የማድረግ ህልም ይዤ ወደ ከተማዋ ተመለስኩኝ። እድለኛ ነኝ፤ ባለቤቴም ስራዋን ትታና ህልሜን ተከትላ አብራኝ መጣች፡፡ ከዚያም አንድ ት/ቤት ውስጥ ማስተማር ጀመርኩኝ፡፡
በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የአርኪቴክቸር ዲፓርትመንት የአርት ኮርሶችን ትሰጣለህ አይደል?
ትክክል ነው፤ አስተምራለሁ፡፡ ቅድም ያልኩሽ ት/ቤት እያስተማርኩ እያለሁ አቫንቲ ብሉናይል ሆቴል፣ አሁን ብሉናይል ሪዞርት ሆቴል ሆኖ የተቀየረው አንድ ነገር አደረገልኝ፡፡ አንድ ቀን፤ “ፈጣሪ እባክህ ያለምኩትን አሳካልኝ” ብዬ ፀሎት አደረግሁኝ፡፡ እኔ ህልሜ ታዋቂ ለመሆን አይደለም፤ ብዙ ብር ለመሰብሰብ አይደለም፤ ግን ይህ ህልሜ የእውነት መስመር እንዲይዝ እፈልጋለሁ” አልኩና ፀልዬ ወደ ነገርኩሽ ሆቴል ሄድኩኝ፡፡ ሀላፊው ሚስተር ስቴቨን ይባላል፤ አገኘሁት፡፡ በሚገርም ሁኔታ ሆቴሉ መቶ ሺህ ብር ስፖንሰር አድርጎኝ፣ 50 ያህል ስራዎችን ማቅረብ ቻልኩኝ፡፡ ካቀረብኳቸው ስራዎች ውስጥ እድለኛ ሆኜ፣ ከ20-30 ያህሉ ስዕሎች ከ2-7 ሺ ብር በሚደርስ ዋጋ ተሸጡ፡፡ በዚህ ውጤት ህይወቴን፣ ከቤተሰቤም ጋር ያለውን ነገር አስተካከልኩኝ፡፡ በርካታ ጉዳዮችን ከወንኩኝ፡፡
በዚህ መሃል የቀድሞው የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ባይሌ ዳምጤ፣ በስዕል ኤግዚቢሽኑ ስነ-ስርዓት ላይ ከባለቤታቸው ጋር ታድመው ነበርና፣ “ከተማችን እንዲህ አይነት ልጅ አለን እንዴ? ለአርኪቴክቸር ዲፓርትመንት ብዙ ጊዜ ማስታወቂያ አውጥተን አላገኘንም” ብለው ሪኮመንድ አደረጉኝ፡፡ ቅድም እንዳልሺው በዩኒቨርሲቲው ማስተማር ጀመርኩኝ ማለት ነው። ለሙያው ካለኝ ፍቅር የተነሳ ተማሪም እያለሁ፣ ሁለት ክረምቶች 80 ያህል ወጣቶችን በስዕል ትምህርት በበጎ ፈቃደኝነት አሰልጥኛለሁ፡፡  ከነዚህ መካከል ከ10 በላይ ሰልጣኞች፣ አለ የስነ ጥበብ ዲዛይን ትምህርት ቤት ለመግባት ችለዋል፡፡ ይሄም እድለኛ ነኝ ያሰኘኛል፡፡ አሁን ልጆቹ በጥሩ ሁኔታ እየተንቀሳቀሱ ነው፡፡ በዚህ በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡
እኛ አገር ላይ ስዕል እንጀራ አይሆንም የሚለው አመለካከት በስፋት ይንፀባረቃል፡፡ አንተስ ይህን አመለካከት  ትጋራዋለህ?
ምን መሰለሽ… እንጀራ ይሆናል ብለሽ፣ እንጀራ እንጀራውን እያሰብሽ ከገባሽበት እንጀራ አይሆንም። ነገር ግን ሙያውን የእውነት ወደሺው፣ ራስሽን ሰጥተሸ ከልብሽ ስትሰሪ እንጀራ መሆን ይጀምራል። ስለዚህ ሙያችንን ወድደነው፣ በፍቅርና በትጋት ነወይ የምንሰራው? የሚለው ጥያቄ መመለስ አለበት፡፡ ሙያችንን ወድደን ራሳችንን ሆነን ሥንሰራ፣ የማንንም አንገለብጥም፡፡ ስለዚህ ትኩረት እንስባለን፡፡ አሁን ሰው ለአርቱ ያለው አመለካከት እየተቀየረና አይኑ እየተከፈተ ነው። እኔ ለምሳሌ ሙያዬ በአንድ አቅጣጫ ብቻ ገቢ እንዲያመጣልኝ አልፈልግም፡፡ የህትመት ስራዎች ሰርቻለሁ፣ ዲዛይኖች ሰርቻለሁ፡፡ ጨጨሆ የባህል ምግብ አዳራሽን ካየሺው፣ የባህርዳሩንም የአዲስ አበባውንም ስዕሎች የሰራሁት እኔ ነኝ፡፡ አሁን ይህ ስራ አድካሚና እልህ አስጨራሽ ነው፡፡ 20 ሜትር በ7 ሜትር ስዕል መሳል ከባድ ነው፡፡ ከዚያ ይልቅ ትንንሽ ብዙ ስዕሎችን መስራት ይቀላል፡፡ እኔ የማስበው ያሉኝን ነገሮች ተጠቅሜ፣ ሙያዬን ወደ ገንዘብ መቀየርና ከአንድ አቅጣጫ ጠባቂነት ራሴን ማውጣት ነው፡፡ በዚህ በኩል እድለኛ ነኝ፤ ፈጣሪ እረድቶኛል፡፡ ለምሳሌ “አርት ቴራፒ” በሚል ለጋምቢ ሆስፒታል ፕሮፖዛል አስገብቼ መልስ እየጠበቅኩ ነው፡፡
“አርት ቴራፒ” ምንድን ነው?
አንድ ታማሚ በተኛበት የሆስፒታል ክፍል ፊት ለፊቱ አንድ ማራኪ ስዕል ቢሰቀል፣ ያንን ስዕል በማየትና በመመራመር፣ ህመሙን ለአፍታ ያህል ቢረሳ ቀላል አይደለም፤ የጎንዮሽ ጉዳት የሌለው መድሀኒት ነው፤ ስለዚህ በዚህ መልኩ ስዕሎችን ሰርቼ ህመምተኞች ክፍል ለመስቀል ምክረ ሀሳብ ባህርዳር ለሚገኘው ጋምቢ ሆስፒታል አቅርቤያለሁ። ምን ለማለት ነው… ያሉትን አማራጮች ሁሉ እሞክራለሁ፤ ከማንኳኳቸው 10 በሮች አንዱ ይከፈታል፡፡
በአሁኑ ወቅት በጉራማይሌ አርት ጋለሪ “ነቁጥ” የተሰኘ የስዕል አውደ ርዕይ ለዕይታ አቅርበሃል፡፡ ስራዎችህ ሁሉ የተሰሩት ደግሞ በከብት ቆዳ ላይ ነው። የስዕል (art) ፍልስፍናህ ምንድን ነው?
እንግዲህ የእኔ አርት ፍልስፍና የምለው ገና በሂደት ላይ እንዳለ ይሰማኛል፡፡ እኔ እንደ ትልቅ ነገር የማነሳው፣ በዚህኛው በ“ነቁጥ” ብቻም ሳይሆን ከመጀመሪያው አንስቶ በነበሩ ሥራዎቼ ጎልቶ የሚታይ ነገር አለ፡፡ “ተቃርኖን ማስታረቅ” የሚል ነው፡፡ ሁለት በሀሳብ፣ በቅርፅና በቀለም የሚለያዩ ነገሮች አንድ ላይ የሚሆኑበት ክፍል ፈልጎ፣ የማቀራረብና ማስታረቅ አካሄድ ነው። ለምሳሌ ኢትዮጵያ የምትባለው አገር በአስደማሚ ተቃርኖዎች የተሞላች፤ ነገር ግን ተቃርኖዎቿ ጌጥ የሆኑላት አገር ናት፡፡ ለአብነትም ዳሎል በጣም የአገሪቱ ዝቅተኛ ቦታ ነው፣ ራስ ዳሽን ከአፍሪካ በከፍታው ሁለተኛ ደረጃ  ላይ የሚገኝ ትልቅ ተራራ ነው፡፡ ሁለቱ በአንድ አገር በጣም በተቃርኖ ደግሞም ውበት ሆነው ተቀምጠዋል፡፡
ለእኔ ምዕራባዊ የሆነው አጠቃላይ ፍልስፍና “ትራዲሽናል” ሲል ያስቀኛል፡፡ ዘመናዊነት (ሞደርኒቲ) የባህላዊ ሂደቶች ቅጥያ ነው እንጂ በተለየ ሁኔታ የተፈጠረ አይደለም፡፡ ቀደም ብሎ የነበረው ባህላዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ሂደት ቀስ በቀስ እየተቀየረ ይሄዳል እንጂ በአንዴ ብጥስ ብሎና ከባህላዊነቱ ተለይቶ ብቻውን የቆመ አይደለም፡፡ ስለዚህ ዘመናዊነት ራሱን ለማስቀጠል አሁንም ባህላዊነት የግድ ያስፈልጋል፡፡ እኔ በስራዬ በአብዛኛው ባህላዊ ኤለመንቶችን እወስዳለሁ። በዚያው ልክ በጣም ዘመናዊዎቹንም እወስድና በጣም አስታርቄ አንድ የተጣጣመና የተቀናጀ ነገር እፈጥራለሁ። ብዙ ስራዎቼ ላይ የሚታይ ባህርይ ነው፡፡ ፈጣሪ በስራዎቹ ላይ የገለፀውም ይህንን ውበት ይመስለኛል፡፡ ይሄ ነገር ነው እንዳይሰለቸን የሚያደርገው፡፡ አሁን ቅጠል አንድ አይነት ተመሳስሎ ይኖረውና በዚያ ውስጥ ልዩነት አለው። ፋብሪኬትድ የሆነ ወይም ሰው የሰራው ነገር ነው ቶሎ የሚሰለቸው፡፡ ይሄ ከፈጣሪ የወሰድኩት ትልቅ ጥበብ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ ሰው ሁሉ በፈጣሪ ሊነቃቃ ይችላል፡፡ በተፈጥሮ ብቻ ወይም በተለያየ ነገር ሊነቃቃም ይችላል፡፡ እኔ በራሱ በፈጣሪ ነው የተነቃቃሁት፡፡ እንደ አምላክ ከማምለክ በዘለለ  እንደሚጠበብ ሰው “creative-personality” አድናቂው ነኝ፡፡
“ነቁጥ” በሚል በሰየምከው  አውደ ርዕይህ ላይ ስራዎችህ ለምንድን ነው በከብት ቆዳ የተሰሩት? “ነቁጥ” ስትል የሰየምከውስ በምን ምክንያት ነው?
እኔ ወደ ቆዳ አርት የገባሁት መጀመሪያ እንደ አንድ ገጠር እንደተወለደ ልጅ፣ ከበሬና ላም ጋር ያለኝ ግንኙነትና ቅርበት የጠበቀ ነው፡፡ እንደውም አያቴ ስታሳድገኝ “ትርባልኝ” የምትባል ላም ነበረች፤ለእኔ ብቻ የተመደበች፡፡ ቀጥታ አፌን ከፍቼ፣ አያቴ ወተት አፌ ላይ እደረገች ነው ያሳደገችኝ፡፡ ከዚህ አለፍ ብዬ በሬን መመልከት ጀመርኩ፡፡ በሬ እየተገረፈ አርሶ ያበላል፣ ከዚያ ስጋውን ይሰጣል፡፡ ቆዳውን ለገመና መሸፈኛ ይሰጣል፡፡
በመፅሐፍ ቅዱስ አማኒያን ዘንድ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰው በሀጢያቱ ምክንያት ፀጋውን ተገፍፎ፣ ራቁቱን ሲቀር ገመናው ለመሸፈን የተጠቀመው ቅጠል ነው። ነገር ግን ቅጠል ረጅም ጊዜ ስለማይቆይ ጌታ ራሱ ቆዳ ነው የሰጣቸው፤“ለምድ አለበሳቸው” ይላል፡፡ ቀንዱን ለመጠጫ፣ ጅራቱን ለመግረፊያ እንጠቀማለን፡፡ በፖለቲካዊ አንድምታም ከሄድን፣ ነጋሪት ተጎስሞ አዋጅ የሚነገረው ከበሬ ቆዳ ተሰርቶ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ እበቱ ራሱ ማገዶ ይሆናል፡፡
በሬ ቁርጥምጥም አድርገን የምንጠቀመው ፍጥረት ነው፡፡ ለዚህ ሁሉ ፈቃደኛ የሆነም ነው፡፡ ይህ ነው መነሻዬ፤ ቆዳ ላይ ያተኮርኩበት፡፡ በሬ ያ ሁሉ ቆዳው ላይ ያለ ዥንጉርጉር፣ ትልቅም ይሁን ትንሽ ነቁጥ፣ ብዙ በሬ አያደርገውም፤ እነዛ ተባብረው ነው በሬ የሚያሰኙት፡፡ ይህ እሳቤ የበለጠ ስለሳበኝ ነው ያተኮርኩበት፡፡
በተለይ በገጠር አካባቢ ቆዳ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት ነው ያለው---
እውነት ነው፡፡ የገጠሩ የቆዳ አጠቃቀም ከተነሳ አይቀር በጣም የሳበኝ፣ አጎዛውን ግድግዳ ላይ ሰቅለው፣ ለጌጥና ለአይን ማረፊያ ያደርጉታል፡፡ ከዚያ ያወርዱና አንጥፈው ይተኙበታል፡፡ ሲተኙ ደግሞ ያሸትቱታል፡፡ እነዚህ የውበት ልምምዶች ሁለት አይነት ነገር አላቸው፤ ተግባራዊም ውበታዊም። እነዚህን ሁለት መልክ ያላቸው ስራዎች ለእይታ ማቅረብ በምዕራባዊያን አረዳድ፤ “ማቴሪያል ካልቸር” ነው የሚሉት፡፡ ምን ማለት ነው? ሰው ለዕለት ተዕለት ኑሮው የሚጠቀምባቸው እንጂ የተጠበበት አርት አይመስላቸውም፡፡ እንደኔ እምነት ግን ሙዚየም ባለማቅረባቸው እንጂ እነዚህ ስራዎች በምዕራባዊያን ሙዚየሞች ከሚታዩ ስዕሎች በላይ ጠንካራ ናቸው፡፡
እንደውም አሁን በዘመናዊ ስነ-ጥበብ ትልቁና ጠንካራ መሆን አለበት የሚባለው አርቲስቱ በአይን ታይቶ ከሚያበቃና ዋው ከሚያስብል ስራ በዘለለ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የሆኑ ጉዳዮችን የሚያነሳ፣ የሚቀሰቅስና የሚታገል ነው። እነዚህ አርቲስቶች ከእለት ተእለት ህይወታቸው ጋር የተቆራኙ ነገሮችን ወስደው ለታይታና ለእይታ ብለው ሳይሆን ከልብ የመነጨ ሀሳባቸውን ያንጸባርቁባቸዋል፡፡ ለነዚህ ስራዎች ደግሞ ቦታ ተሰጥቶ መካተት አለባቸው የሚል ሀሳብ ይዤ  ነው የተነሳሁት፡፡
ታዲያ ስራዎችህ ተቀባይነት አግኝተውልሃል?
አሁን ይሄን የሚደግፉልኝ ሱዛን ፎግል፣ ካሮል ዳንከል እና ሌሎችም ፀሀፊዎች አሉ፡፡ እነዚህ ፀሀፊዎች የአፍሪካዊያን አርት በምዕራባዊያን ሙዚየም ለእይታ ሲቀርብ እንደ እቃ ነው የሚከለኮለው እንጂ እንደ ሪፋይን አርት በስርዓቱና በክብር አያቀርቡትም፡፡ የራሳቸውን ግን ከአምላክና ከሰማይ የወረደ አድርገሽ እንድትመለከቺው፣ ያንን ስሜት ይፈጥሩብሻል፡፡ እኔ እንደምታዪው፤ እነዚህን ሞሰቦች፣ አገልግሎችና ሌሎች እቃዎችን ከእቃነት በዘለለ ራሳቸው ጥልቅ የሆነ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ እሳቤ ያላቸው መሆኑን ለማሳየት ሞክሬያለሁ፡፡ ቅድም የጠቀስኩልሽ ፀሀፊዎች፣ይህንን ስራና አስተሳሰብ ይደግፉታል፤ተቀባይነቱ የሚያጠራጥር አይደለም፡፡
በአውደ ርዕዩ ላይ ከቀረቡት መካከል የገረመኝ፣ ትልቁ በቆዳ የተለበጠው መሶብ፣ በቁልፍ ተቆልፎ በርካታ የቁልፍ መክፈቻዎች ከበውታል፡፡ እስቲ የዚህን መሶብና የቁልፍ መክፈቻዎቹን ምስጢር አብራራልኝ?
በዚህ መሶብና በቁልፉ ማስተላለፍ የፈለግኩት እንጀራ፣ ተስፋና ዕድልን ነው፡፡ የእቃዎቹን አቀራረብ installation (ኩልኩል) እንለዋለን። ጥልቅ የሆነውን የሰው ህይወትና በሕይወቱ የሚገጥሙትን ጉዳዮች ሊገልፅ በሚችል መንገድ የምናስቀምጥበት ነው:: ሰው ተስፋ አለው፣ ዕድልም አለው፣ እንጀራም አለው፡፡ ተስፋው ያለ ማቋረጥ ይሄንን ቁልፍ ለመክፈት እንዲሞክር ያደርገዋል። ዕድሉ ሙከራውን ያሳካለታል፡፡ እንጀራው በነዚህ ሂደቶች የሚገኝ ስኬት ነው፡፡ ይህ የተቆለፈ መሶብ በስሩ ከተደረደሩት መዓት ቁልፎች አንዱ ይከፍተዋል። የሚከፍተው ቁልፍ ምንም ምልክት የለውም፡፡ ይሄ የብዙ ሰዎችን ሀሳብ ይሞግታል፡፡
በምን መልኩ?
ቁልፉ ከእነዚህ ቁልፎች መሀል እንዳለ እናውቃለን። የሰው ልጅ ከእነ ዕድሉ፣ ከእነ ስጦታው ነው የተፈጠረው፤ ነገር ግን አብዛኛው የሚሞክርና የሚጥር አይደለም፡፡ አንድ ሰው ተስፋ ካደረገ፣ ከጣረ ዕድሉ ቁልፉን እንዲያገኝ ያደርገዋል። ይሄ ሙግት በውስጥሽ መመላለሱ አይቀርም፡፡
ለጉብኝት የሚመጡ ሰዎችን የዚህን ሞሰብ ቁልፍ ሞክረው እንዲያገኙ ስትጋብዝ አይቻለሁ። እኔም በርካታ ቁልፎችን ሞክሬ መሶቡን መክፈት አልቻልኩም፡፡ ለመሆኑ እስካሁን ሞክሮ የተሳካለትና የከፈተው አለ?
የሚገርምሽ አንድ ልጅ ሞክሮ ተሳክቶለታል፡፡ በውስጡ ምን አገኘ የሚለውን አሁን አልናገረም፤ ነገር ግን ይሄ ልጅ መክፈት አለብኝ ብሎ ቆርጦና ወስኖ ነው የተቀመጠው፡፡ ልጁ ምን ያህል ሰዓት  ታግሶ ወስኖ እንደተቀመጠ ስመለከት፣ የልጁ ቁርጠኝነት ለብዙ ሰው ትምህርት የሚሆን ነው። ህፃናትም በብዙ ትዕግስት ፈልገው ፈልገው፣ “እባካችሁ የትኛው ነው፣ አሳዩን?” እስከ ማለት ደርሰዋል፡፡
አንተ ግን ቁልፉ የትኛው እንደሆነ ታውቀዋለህ?
በፍፁም! እኔም አላውቀውም፡፡ አንድም የሌላው ህብረተሰብ አካል ለመሆን፣ በሌላም በኩል ለራሴ እንዳላዳላ በሚል አላውቀውም፡፡ እንግዲህ በምዕራቡ ዓለም ስዕል በእጅ አይነካም፤ አይዳሰስም፤ በቃ ሀይማኖታዊ ነገር አድርገው ነው የሚያስቀምጡት። አምስት ሜትር ከስዕሉ ርቀሽ ነው የምትመለከቺው። እኛ ጋ ትነኪዋለሽ፣ ትዳስሺዋለሽ፣ የሰቀልሺውን ራሱ አውርደሽ ትተኚበታለሽ፤ ስለዚህ የሚዳሰስ የሚታይና የሚሸተት ሥራ ነው የምንሰራው፡፡
አውደ ርዕዩን ብዙ የውጭ ዜጎች ሲጎበኙት ተመልክቻለሁ፡፡ ጎብኝዎች የሰጡህ አስተያየት ምን ይመስላል?
ያገኘኋቸው ሁሉ በጣም ፍላጎት ያሳደረባቸው ነገር ምን መሰለሽ? ወይ ዘመናዊነቱ ውስጥ ጥልቅ ብለህ አልገባህ ወይ በጣም ባህላዊ በሚባል መንገድ አልመጣህ፤ ሁለቱን አቻችለህ ስለምትሞግተን እኛም የሀሳብ ለውጥ ለማድረግ ተመችቶናል፡፡ በሌላ በኩል በአይን ከመታየት አልፎ እንድንነካ፣ አገላብጠን እንድናይ ዕድል አግኝተናል፡፡ የሚዳሰስ የሚሸተት የሚታይ ስዕል ማየታችን አዲስ ስሜት ፈጥሮብናል ሲሉ  ተናግረዋል፡፡
ሌላ መናገር የምፈልገው ነገር፣ በምዕራባዊያን ፕላት ፎርም ውስጥ የተካተተው የስነ- ጥበብ ፍልስፍና እና ታሪክ የሌላውን አለም ያላቀፈ ነው የሚል ሙግት አለ። እነ ፒካሶ በተነሱበት ዘመን በተጓዳኝ በአፍሪካ፣ በላቲን አሜሪካ፣ ከምዕራቡ ተመጣጣኝ የሆኑ የአርት ክንውኖች የነበሩ ቢሆንም የተካተተው የምዕራቡ ብቻ ነው የሚል የሀሳብ ፍጭት ስላለ፣ በዚያ ሙግት ውስጥ የእኔን ትንሽ ነፀብራቅ ለማሳየት ነው እየሞከርኩ ያለሁት፡፡
በስዕሎቹ በቆዳ የተለበጠ ቴሌቪዥን ተመልክቻለሁ። ትርጉሙ ምንድን ነው?
ቴሌቪዥን በአገራችን የማህበረሰብን ስትራክቸር የቀየረ ነው፡፡ ምን ማለት ነው--- ቀደም ባለው ጊዜ ቤት ውስጥ ስንቀመጥ፣ ትልልቅ ሰዎችን ከብበን ነበር፡፡ ማዕከል የሚሆኑት እናት አባቶቻችን ናቸው። አሁን ደግሞ ቴሌቪዥን ከበን ነው የምንቀመጠው፡፡ የቴሌቪዥኑ አቀማመጥ ደግሞ ለሁሉም ለህፃን ለአዋቂው እንዲመች ተደርጎ ነው የሚዘጋጀው፡፡ ዱሮ ተረት፣ ምክር የምንሰማው ከታላላቆቻችን የሚጠቅመንን ብቻ ነበር፡፡ አሁን ቴሌቪዥን የምናየው ያለ ዕድሜ ገደብ ነው፡፡ ለልጅ ነው ለአዋቂ ነው የለም፣ ያውም ተገምግሞ በማያልፍ የትኛውም ሀሳብ ውስጥ አብረን እንሰለፋለን፡፡ ይሄ ለእኔ አስጊ ነው፡፡ ቴሌቪዥኑን ቆዳ ያለበስኩት፣ ከቴሊቪዥኑ የሚወጣውን እኛ ብናስተካክለውና ብንዋጀው የሚል ምኞቴን ለማስተላለፍና የሚጠቅመንን ብቻ የምንሰማበት ልናደርገው ብንችል የሚለውን ህልሜን ለማሳየት ነው፡፡ እንግዲህ የሀሳብ ተቃርኖውን የሚያሳይ ነው። ቆዳው የእኛ ነው፤ ቴክኖሎጂው የእነሱ ነው። ይሄ በእጄ የያዝኩት ስልክ ጥሩም መጥፎም አይደለም፤ በስልኩ የምጠቀምበት ነገር ነው ጥሩና መጥፎ ሊያሰኘው የሚችለው፡፡ በስልኩ ደውዬ “ሰው ግደል ወይም የወደቀ ሰው አንሳ” ስል ውጤቱ ይወሰናል ማለት ነው፡፡
አሁን ደግሞ በአሜሪካ ስላሳየኸው አውደ ርዕይ  እና በቅርቡ በግብፅና በኢኳዶር ስለምታሳየው የስዕል አውደ ርዕይ አጫውተኝ ----
ቀደም ብዬ እንደነገርኩሽ፣ አንድም ቀን ታዋቂ ለመሆን ብዬ ከአርት ጋር ተቆራኝቼ አላውቅም፤ ነገር  ግን በፍቅርና በፍላጎት ተሞልተሽ ስትሰሪ፣ አይን ውስጥ ትገቢያለሽ፡፡ በመጀመሪያ ያገኘሁት እድል በአሜሪካ ላስቬጋስ በኔቫዳ ዩኒቨርሲቲ የሚገኝ የስነ-ጥበብ ተቋም ነው፡፡ በማይመች አካባቢ ውስጥ ሆኜ በባህርዳር ለአምስት ዓመታት ሥነ-ጥበብ ላይ በመስራቴ በተለይም ከወጣሁበት አካባቢ ሀይለኛ ግንነት ያለው ስራ መፍጠር በሚል “ፐብሊክ ሌክቸር” ሳደርግ፣ በተጨማሪም ስራዎቼን “ባሪክ” ሙዚየም ውስጥ ከንግግሬ ጎን ለጎን ለእይታ አቅርቤ ነበር፡፡ ከዚያም ለሶስት ሳምንታት ያህል ግራንት ሆል ጋለሪ ሆል ውስጥ ስራዎቼ ለእይታ በቁ፡፡ ቦልደርሲቲ በሚባል ከተማም ስራዎቼ ለህዝብ ለእይታ በቁ፡፡ በዚያው ከተማም ለህዝብ ንግግር አድርጌአለሁ። ይሄ በጣም ያስደሰተኝ ኢትዮጵያን የማያውቁ ሰዎች ገጥመውኝ ነበር፡፡ በእኔ ስራ ምክንያት ኢትዮጵያን ማወቃቸው ትልቅ ደስታ ፈጥሮብኛል፡፡ እነ ኃይሌ ገ/ሥላሴን እያወቁ ኢትዮጵያን አያውቁም፡፡ ለእነዚህ ሰዎች ስለ ኢትዮጵያ መናገሬ ያስደስተኛል። እርግጥ ነው ስሄድ አበባ ይዞ የተቀበለኝ የለም፤ የሰራኋቸውን ለእይታ ያቀረብኳቸውን ስራዎቼን ብዙ ግምት ውስጥ ያስገባ የለም፤ ሆኖም ኢትዮጵያን አስተዋውቄያለሁ፡፡ እርግጥ ሲጠሩኝ ከወጣሁበት አካባቢና ባህል ጋር የተቆራኘ ሥራ በመስራቴ ሁኔታዎች በማያበረታቱበት ድባብ፣ በፈተና ውስጥ ያለማቋረጥ የስዕል አውደ ርዕይ ለአምስት ዓመት በማቅረቤ ነው፡፡ በባህርዳር በቆየሁባቸው በነዚህ ጊዜያት አመታዊ አውደ ርዕዮች እንዲኖሩ አድርጌያለሁ፡፡
ሁለቱ ላይ በተለይ የአዲስ አበባ አርቲስቶች እንዲሳተፉ በማድረግ፣ ባህርዳርን አማራጭ የስነ-ጥበብ ማዕከል የማድረግ ህልሜን ለማሳካት ሙከራዬን የጀመርኩበት ነው፡፡ “ጥበበ ባህርዳር” “አርት ኦፍ ዘ ናይል” በተሰኙ ኤግዚቢሽኖች ነው ይህን የሰራሁት። በኋላም በግሌ ሦስት ኤግዚቢሽኖች አቅርቤያለሁ፡፡ በብሔራዊ ሙዚየምም “ሀገረ ቀለም ኢትዮጵያ” የተሰኘ በሀሳብም፣ በቴክኒክም ሆነ በቀለም በዛና ተለቅ ያለ ኤግዚቢሽን ነበረኝ። አሁን በሶሻል ሚዲያም በርትቼ እየሰራሁ ነው፡፡ አንዳንድ ሰዎችም በኔ ተነቃቅተው እየፃፉ ይገኛሉ። ናይጄሪያ በሚታተም “ታይምስ” የተሰኘ መፅሄት ላይ “ዘ አርቲስት ኦፍ ናሽናል ኮንሺየስነስ” በሚል ርዕስ ሽፋን አግኝቻለሁ፡፡
በግብፅና በኢኳዶር ስለምታቀርበው አውደ ርዕይ ንገረኝ---?
በኢኳዶር የሚካሄደው ዓለም አቀፍ ሰሚት ነው። በግብፅ ደግሞ “ኢንተርናሽናል አርት ሲምፖዚየም” ከአፕሪል 12 እስከ 24 ቀን 2018 ይካሄዳል፡፡ በዚያ ላይ እሳተፋለሁ፡፡ በዚህ ሁሉ ደስኛ ነኝ፡፡ አገራችን የ3 ሺህ ዓመት ታሪክ ያላትና የባህልና ታሪክ አገር መሆኗ፣ ለአንድ የፈጠራ ሰው በተለይ በስነ-ጥበብ ሙያ ውስጥ ላለ ሰው እድለኝነት ነው፡፡ ብዙ የምንሰራበት እድል አለ፡፡ ህልሜ ስዕልን ለእይታ አቅርቦ ከመሸጥ በዘለለ ጠንካራ ንቅናቄ ለመፍጠር ነው፡፡ ይህ ደግሞ ይሳካል፡፡  


 “--አጎዛውን ግድግዳ ላይ ሰቅለው፣ ለጌጥና ለዓይን ማረፊያ ያደርጉታል፡፡ ከዚያ ያወርዱና አንጥፈው ይተኙበታል፡፡ ሲተኙ ደግሞ ያሸትቱታል፡፡ እነዚህ የውበት ልምምዶች ሁለት አይነት ነገር አላቸው፤ ተግባራዊም ውበታዊም፡፡--”

    ተወልዶ ያደገው በጎጃም ገጠር ቢሆንም ያደገውና የተማረው በባህርዳር ከተማ ነው - ሰዓሊ እያዩ ገነት፡፡ የመጀመሪያ ድግሪውን ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ ቢያገኝም የነፍሴ ጥሪ እንዳልሆነ ስገነዘብ፣የወርልድ ቪዥን ሥራዬን ጥዬ፣ ወደ አዲስ አበባ መጣሁና የስዕል ት/ቤት ገባሁ ይላል፡፡ በትምህርቴ “ሰቅዬ” በመቅረት በስዕል    ት/ቤት ውስጥ የተወሰነ አበርክቶ ይኖረኛል የሚል እምነት ነበረኝ የሚለው ሰዓሊው፤ ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች ሳይሳካ ቀረና የሀይስኩል ተማሪዎችን በራሴ ተነሳሽነት፣ ስዕል ማስተማር ጀመርኩኝ ብሏል፡፡ በፋይን አርት ዲግሪውን ከአገኘ በኋላስ? የጥበብ ጉዞው ምን ይመስላል? ወደ ባህርዳር ይዤው ሄድኩ ስለሚለው ህልሙ ያወጋናል፡፡ ስዕል እንጀራ አይሆንም በሚል የሚንጸባረቀውን  አመለካከትም ይሞግታል። ስለ ምዕራቡ ዓለም የሥነ ጥበብ ፍልስፍና፣ “ነቁጥ” በሚል ስያሜ በጉራማይሌ የሥነጥበብ ጋለሪ ለዕይታ ስላቀረበው አውደ ርዕይ ያብራራል፡፡ ሰዓሊው በቅርቡ በግብጽና በኢኳዶር በሚካሄድ የሥነ ጥበብ ሲምፖዚየም ላይ እንደሚሳተፍም ይገልጻል፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ፤ ሰዓሊውን በጥበብ ህይወቱ ዙሪያ አነጋግራዋለች፡፡ እነሆ፡-  


   ስሜትህ ለስነ-ጥበብ እያደላ እንዴት ኢኮኖሚክስ ለመማር ዩኒቨርሲቲ ገባህ?
“ብልጥ ልጅ እየበላ ያለቅሳል” ይላሉ አበው። በውስጤ የስነ-ጥበብ ፍቅር ቢኖረኝም አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተገብቶ መማር እንደሚቻል የነገረኝ ወይም መንገዱን ያሳየኝ አልነበረም፡፡ ብቻ ባህርዳር ላይ ዘውዱ ባይሌ የሚባል ሰዓሊ ነበር (ነፍሱን ይማርና) ጋለሪ ከፍቶ የማስታወቂያ ስራ ሲሰራ እያየሁ፣ እሱን ነበር መሆን የምፈልገው፡፡ ነገር ግን በወቅቱ የትምህርት ውጤቴ ጥሩ ስለነበር ካሉት ትምህርቶች የተሻለ ነው ብዬ ያመንኩትን የኢኮኖሚክስ ትምህርት ልማር ቻልኩኝ፡፡
በተማርከው ትምህርት ሰራህበት ታዲያ? ከዚያስ እንዴት ወደ አለ የስነ ጥበብና ዲዛይን ት/ቤት ገባህ?
በኋላ ላይ ጥሪሽ እንዳልሆነ ሲገባሽ ሁሉም ነገር ትግልና ፈተና ይሆንብሻል፡፡ ላልተፈጠርንበት አላማ ምናልባት ችለን በእጃችን ልንሄድ እንችላለን ግን እጅ እንደ እግር እንደማይሆን የተረዳን ሰዓት፣ በእግር መሄድ ስንሞክርና በጣም ምቹ መሆኑን ስንረዳ በእጃችን የሄድንበትን ጊዜ እንፀፀትበታለን። ምን ለማለት ነው… ለአፍንጫም ለአይንም አሁን ካለበት የተሻለ ቦታ የለም። በኢኮኖሚክሱ ሰርተህበታል ወይ ላልሺኝ፤ እርግጥ ነው ወርልድ ቪዥን ገብቼ ስራ ጀምሬ ነበር፡፡ ነገር ግን ለዚያ ቦታና ስራ የተፈጠርኩ አለመሆኔ ሲገባኝና የነፍሴ ጥሪ አርት እንደሆነ ስረዳ፣ ወደ አዲስ አበባ መጥቼ አርት ት/ቤት ገባሁ፡፡ በወቅቱ ቤተሰቤም እንጀራ ትተህ ሄደህ እንጀራ አይወጣልህም ብለውኝ ነበር፤ ደስተኞችም አልነበሩም፡፡ እኔ ግን ትዝ ይለኛል፣ ወደ አዲስ አበባ ስመጣ በኪሴ የነበረው 300 ብር ብቻ ነበር። ጫማ ጠርጌም ቢሆን የተጠራሁበትን ዓላማ አሳካለሁ የሚለውን ህልም ይዤ ነው የወጣሁት። ከዚያ አራት አመት በአርት ስኩል ትምህርቴን ስከታተል ቆይቼ፣ በፋይን አርት ዲግሪዬን አገኘሁ፡፡
በስዕል ት/ቤት በነበረህ ቆይታህ ከመደበኛው ትምህርት ውጭ በራስህ ላይ የጨመርከውን ነገር ንገረኝ…?
እንደኔ አመለካከት ትምህርት አንቺን አይፈጥርሽም ግን የተፈጠረውን አቅምሽን ቅርፅ በመስጠትና አቅጣጫ በማስያዝ ከፍተኛ እገዛ ያደርግልሻል፡፡ እኔ በተለይ ከመምህራኖቼ በጣም የሚያስገርሙ አቅሞችን አግኝቻለሁ፡፡ እነ መዝገቡ ተሰማ፣ ታደሰ መስፍን፣ ጌታሁን አሰፋ፣ በቀለ መኮንንና ሌሎችም አመለካከትን ሊቀይሩ ከሚችሉ ሰዎች ጋር የመገናኘት ዕድል ማግኘትሽ ያለሽን ነገር ጥልቀት ይጨምርልሻል፡፡ በዚህ ምክንያት ለሙያው ያለኝ ጥማት ጨርሶ ነደደ፡፡ መጀመሪያም ፓሺን ነበረኝ፤ ትምህርቱ ደግሞ የበለጠ ፍቅርና ፍላጎቱን አቀጣጠለልኝ፡፡ እርግጥ ነው መጀመሪያ ላይ የሚያሳጣሽ ነፃነት አለ…፡፡
ምን አይነት ነፃነት ነው የሚያሳጣው?
የምንማርበት ሥርዓተ ትምህርት የተቀረፀው በምዕራቡ አስተሳሰብ ላይ ማዕከል አድርጎ በመሆኑና የአገራችንን ነባራዊ ሁኔታ ከግንዛቤ ውስጥ ስለማያስገባ በጣም ገዳቢ ነው፡፡ ነገር ግን አንቺ ብልህ ከሆንሽ ያንን ትምህርት ከራስሽ ሁኔታ አንፃር እየቃኘሽ መጠቀም ትችያለሽ፡፡ እኔም በት/ቤት ቆይታዬ ይህንን ሳደርግ ነው የቆሁት፡፡ ከዚያ በኋላ በነበረኝ ፍቅር… በውጤቴ ምክንያት እዚያው ት/ቤት በመምህርነት እቆያለሁ የሚል እምነት ነበረኝ፡፡ እንደው እዚያው ጨርሶ መቅረትም ባይሆን እንኳን የተወሰነ አበርክቶ ይኖረኛል የሚል ሀሳብ ነበረኝ፡፡ ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች ሳይሳካ ቀረና የሀይስኩል ተማሪዎችን በራሴ ተነሳሽነት፣ ደስ ብሎኝ ስዕል ማስተማር ጀመርኩኝ። ይህን እያደረግኩኝ ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ አርኪቴክቸር ዲፓርትመንት የማስተማር ዕድል አገኘሁ፡፡ እዛም ለአንድ ዓመት ያህል ሰራሁ፡፡
ብዙ የስዕል አውደ ርዕዮች ላይም ተሳትፈሃል…?
አውደ ርዕዮችን--- በአሊያንስ ኢትዮ ፍራንሴዝ፣ በጎተ ኢንስቲትዩት፣ በአሜሪካ ኤምባሲና በሌሎች ቦታዎች በቡድን አቅርቤአለሁ፡፡ ይህንን ሳደርግ ግን የቀደሙ አርቲስቶች የሚሰሩትን እንደምደግም እንጂ አዲስ ነገር እንደማልሰራ ተረዳሁ፡፡ ከዚያ አንድ ህልም ይዤ ወደ ባህርዳር ሄድኩኝ፡፡ እንደምታውቂው አለ የስነ-ጥበብና የዲዛይን ት/ቤት 50 ዓመት ሞልቶታል፡፡ ከዚያ የሚወጡ አብዛኞቹ ሰዓሊዎች እዚህ አዲስ አበባ ነው የሚሆኑት። ምክንያቱም አዲስ አበባ የብዙ ኤምባሲዎች፣ የዲፕሎማቶች መቀመጫ በመሆኗ ገበያው ያለው እዚሁ ስለሆነ ነው፡፡ ወደ ክልል አይወጡም፡፡ ክልል ላይ ደግሞ በተደራጀ መልኩ የሚካሄድ የአርት እንቅስቃሴ የለም፡፡ እኔ ደግሞ ባህርዳር ያደግኩባት ከተማ ናት፡፡ ቤተሰቦቼም ያሉት እዚያው ናቸው፡፡ ስለዚህ ባህርዳር የቱሪስት ከተማ በመሆኗ አማራጭ የስነ ጥበብ ከተማ (Alternative Art corner) የማድረግ ህልም ይዤ ወደ ከተማዋ ተመለስኩኝ። እድለኛ ነኝ፤ ባለቤቴም ስራዋን ትታና ህልሜን ተከትላ አብራኝ መጣች፡፡ ከዚያም አንድ ት/ቤት ውስጥ ማስተማር ጀመርኩኝ፡፡
በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የአርኪቴክቸር ዲፓርትመንት የአርት ኮርሶችን ትሰጣለህ አይደል?
ትክክል ነው፤ አስተምራለሁ፡፡ ቅድም ያልኩሽ ት/ቤት እያስተማርኩ እያለሁ አቫንቲ ብሉናይል ሆቴል፣ አሁን ብሉናይል ሪዞርት ሆቴል ሆኖ የተቀየረው አንድ ነገር አደረገልኝ፡፡ አንድ ቀን፤ “ፈጣሪ እባክህ ያለምኩትን አሳካልኝ” ብዬ ፀሎት አደረግሁኝ፡፡ እኔ ህልሜ ታዋቂ ለመሆን አይደለም፤ ብዙ ብር ለመሰብሰብ አይደለም፤ ግን ይህ ህልሜ የእውነት መስመር እንዲይዝ እፈልጋለሁ” አልኩና ፀልዬ ወደ ነገርኩሽ ሆቴል ሄድኩኝ፡፡ ሀላፊው ሚስተር ስቴቨን ይባላል፤ አገኘሁት፡፡ በሚገርም ሁኔታ ሆቴሉ መቶ ሺህ ብር ስፖንሰር አድርጎኝ፣ 50 ያህል ስራዎችን ማቅረብ ቻልኩኝ፡፡ ካቀረብኳቸው ስራዎች ውስጥ እድለኛ ሆኜ፣ ከ20-30 ያህሉ ስዕሎች ከ2-7 ሺ ብር በሚደርስ ዋጋ ተሸጡ፡፡ በዚህ ውጤት ህይወቴን፣ ከቤተሰቤም ጋር ያለውን ነገር አስተካከልኩኝ፡፡ በርካታ ጉዳዮችን ከወንኩኝ፡፡
በዚህ መሃል የቀድሞው የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ባይሌ ዳምጤ፣ በስዕል ኤግዚቢሽኑ ስነ-ስርዓት ላይ ከባለቤታቸው ጋር ታድመው ነበርና፣ “ከተማችን እንዲህ አይነት ልጅ አለን እንዴ? ለአርኪቴክቸር ዲፓርትመንት ብዙ ጊዜ ማስታወቂያ አውጥተን አላገኘንም” ብለው ሪኮመንድ አደረጉኝ፡፡ ቅድም እንዳልሺው በዩኒቨርሲቲው ማስተማር ጀመርኩኝ ማለት ነው። ለሙያው ካለኝ ፍቅር የተነሳ ተማሪም እያለሁ፣ ሁለት ክረምቶች 80 ያህል ወጣቶችን በስዕል ትምህርት በበጎ ፈቃደኝነት አሰልጥኛለሁ፡፡  ከነዚህ መካከል ከ10 በላይ ሰልጣኞች፣ አለ የስነ ጥበብ ዲዛይን ትምህርት ቤት ለመግባት ችለዋል፡፡ ይሄም እድለኛ ነኝ ያሰኘኛል፡፡ አሁን ልጆቹ በጥሩ ሁኔታ እየተንቀሳቀሱ ነው፡፡ በዚህ በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡
እኛ አገር ላይ ስዕል እንጀራ አይሆንም የሚለው አመለካከት በስፋት ይንፀባረቃል፡፡ አንተስ ይህን አመለካከት  ትጋራዋለህ?
ምን መሰለሽ… እንጀራ ይሆናል ብለሽ፣ እንጀራ እንጀራውን እያሰብሽ ከገባሽበት እንጀራ አይሆንም። ነገር ግን ሙያውን የእውነት ወደሺው፣ ራስሽን ሰጥተሸ ከልብሽ ስትሰሪ እንጀራ መሆን ይጀምራል። ስለዚህ ሙያችንን ወድደነው፣ በፍቅርና በትጋት ነወይ የምንሰራው? የሚለው ጥያቄ መመለስ አለበት፡፡ ሙያችንን ወድደን ራሳችንን ሆነን ሥንሰራ፣ የማንንም አንገለብጥም፡፡ ስለዚህ ትኩረት እንስባለን፡፡ አሁን ሰው ለአርቱ ያለው አመለካከት እየተቀየረና አይኑ እየተከፈተ ነው። እኔ ለምሳሌ ሙያዬ በአንድ አቅጣጫ ብቻ ገቢ እንዲያመጣልኝ አልፈልግም፡፡ የህትመት ስራዎች ሰርቻለሁ፣ ዲዛይኖች ሰርቻለሁ፡፡ ጨጨሆ የባህል ምግብ አዳራሽን ካየሺው፣ የባህርዳሩንም የአዲስ አበባውንም ስዕሎች የሰራሁት እኔ ነኝ፡፡ አሁን ይህ ስራ አድካሚና እልህ አስጨራሽ ነው፡፡ 20 ሜትር በ7 ሜትር ስዕል መሳል ከባድ ነው፡፡ ከዚያ ይልቅ ትንንሽ ብዙ ስዕሎችን መስራት ይቀላል፡፡ እኔ የማስበው ያሉኝን ነገሮች ተጠቅሜ፣ ሙያዬን ወደ ገንዘብ መቀየርና ከአንድ አቅጣጫ ጠባቂነት ራሴን ማውጣት ነው፡፡ በዚህ በኩል እድለኛ ነኝ፤ ፈጣሪ እረድቶኛል፡፡ ለምሳሌ “አርት ቴራፒ” በሚል ለጋምቢ ሆስፒታል ፕሮፖዛል አስገብቼ መልስ እየጠበቅኩ ነው፡፡
“አርት ቴራፒ” ምንድን ነው?
አንድ ታማሚ በተኛበት የሆስፒታል ክፍል ፊት ለፊቱ አንድ ማራኪ ስዕል ቢሰቀል፣ ያንን ስዕል በማየትና በመመራመር፣ ህመሙን ለአፍታ ያህል ቢረሳ ቀላል አይደለም፤ የጎንዮሽ ጉዳት የሌለው መድሀኒት ነው፤ ስለዚህ በዚህ መልኩ ስዕሎችን ሰርቼ ህመምተኞች ክፍል ለመስቀል ምክረ ሀሳብ ባህርዳር ለሚገኘው ጋምቢ ሆስፒታል አቅርቤያለሁ። ምን ለማለት ነው… ያሉትን አማራጮች ሁሉ እሞክራለሁ፤ ከማንኳኳቸው 10 በሮች አንዱ ይከፈታል፡፡
በአሁኑ ወቅት በጉራማይሌ አርት ጋለሪ “ነቁጥ” የተሰኘ የስዕል አውደ ርዕይ ለዕይታ አቅርበሃል፡፡ ስራዎችህ ሁሉ የተሰሩት ደግሞ በከብት ቆዳ ላይ ነው። የስዕል (art) ፍልስፍናህ ምንድን ነው?
እንግዲህ የእኔ አርት ፍልስፍና የምለው ገና በሂደት ላይ እንዳለ ይሰማኛል፡፡ እኔ እንደ ትልቅ ነገር የማነሳው፣ በዚህኛው በ“ነቁጥ” ብቻም ሳይሆን ከመጀመሪያው አንስቶ በነበሩ ሥራዎቼ ጎልቶ የሚታይ ነገር አለ፡፡ “ተቃርኖን ማስታረቅ” የሚል ነው፡፡ ሁለት በሀሳብ፣ በቅርፅና በቀለም የሚለያዩ ነገሮች አንድ ላይ የሚሆኑበት ክፍል ፈልጎ፣ የማቀራረብና ማስታረቅ አካሄድ ነው። ለምሳሌ ኢትዮጵያ የምትባለው አገር በአስደማሚ ተቃርኖዎች የተሞላች፤ ነገር ግን ተቃርኖዎቿ ጌጥ የሆኑላት አገር ናት፡፡ ለአብነትም ዳሎል በጣም የአገሪቱ ዝቅተኛ ቦታ ነው፣ ራስ ዳሽን ከአፍሪካ በከፍታው ሁለተኛ ደረጃ  ላይ የሚገኝ ትልቅ ተራራ ነው፡፡ ሁለቱ በአንድ አገር በጣም በተቃርኖ ደግሞም ውበት ሆነው ተቀምጠዋል፡፡
ለእኔ ምዕራባዊ የሆነው አጠቃላይ ፍልስፍና “ትራዲሽናል” ሲል ያስቀኛል፡፡ ዘመናዊነት (ሞደርኒቲ) የባህላዊ ሂደቶች ቅጥያ ነው እንጂ በተለየ ሁኔታ የተፈጠረ አይደለም፡፡ ቀደም ብሎ የነበረው ባህላዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ሂደት ቀስ በቀስ እየተቀየረ ይሄዳል እንጂ በአንዴ ብጥስ ብሎና ከባህላዊነቱ ተለይቶ ብቻውን የቆመ አይደለም፡፡ ስለዚህ ዘመናዊነት ራሱን ለማስቀጠል አሁንም ባህላዊነት የግድ ያስፈልጋል፡፡ እኔ በስራዬ በአብዛኛው ባህላዊ ኤለመንቶችን እወስዳለሁ። በዚያው ልክ በጣም ዘመናዊዎቹንም እወስድና በጣም አስታርቄ አንድ የተጣጣመና የተቀናጀ ነገር እፈጥራለሁ። ብዙ ስራዎቼ ላይ የሚታይ ባህርይ ነው፡፡ ፈጣሪ በስራዎቹ ላይ የገለፀውም ይህንን ውበት ይመስለኛል፡፡ ይሄ ነገር ነው እንዳይሰለቸን የሚያደርገው፡፡ አሁን ቅጠል አንድ አይነት ተመሳስሎ ይኖረውና በዚያ ውስጥ ልዩነት አለው። ፋብሪኬትድ የሆነ ወይም ሰው የሰራው ነገር ነው ቶሎ የሚሰለቸው፡፡ ይሄ ከፈጣሪ የወሰድኩት ትልቅ ጥበብ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ ሰው ሁሉ በፈጣሪ ሊነቃቃ ይችላል፡፡ በተፈጥሮ ብቻ ወይም በተለያየ ነገር ሊነቃቃም ይችላል፡፡ እኔ በራሱ በፈጣሪ ነው የተነቃቃሁት፡፡ እንደ አምላክ ከማምለክ በዘለለ  እንደሚጠበብ ሰው “creative-personality” አድናቂው ነኝ፡፡
“ነቁጥ” በሚል በሰየምከው  አውደ ርዕይህ ላይ ስራዎችህ ለምንድን ነው በከብት ቆዳ የተሰሩት? “ነቁጥ” ስትል የሰየምከውስ በምን ምክንያት ነው?
እኔ ወደ ቆዳ አርት የገባሁት መጀመሪያ እንደ አንድ ገጠር እንደተወለደ ልጅ፣ ከበሬና ላም ጋር ያለኝ ግንኙነትና ቅርበት የጠበቀ ነው፡፡ እንደውም አያቴ ስታሳድገኝ “ትርባልኝ” የምትባል ላም ነበረች፤ለእኔ ብቻ የተመደበች፡፡ ቀጥታ አፌን ከፍቼ፣ አያቴ ወተት አፌ ላይ እደረገች ነው ያሳደገችኝ፡፡ ከዚህ አለፍ ብዬ በሬን መመልከት ጀመርኩ፡፡ በሬ እየተገረፈ አርሶ ያበላል፣ ከዚያ ስጋውን ይሰጣል፡፡ ቆዳውን ለገመና መሸፈኛ ይሰጣል፡፡
በመፅሐፍ ቅዱስ አማኒያን ዘንድ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰው በሀጢያቱ ምክንያት ፀጋውን ተገፍፎ፣ ራቁቱን ሲቀር ገመናው ለመሸፈን የተጠቀመው ቅጠል ነው። ነገር ግን ቅጠል ረጅም ጊዜ ስለማይቆይ ጌታ ራሱ ቆዳ ነው የሰጣቸው፤“ለምድ አለበሳቸው” ይላል፡፡ ቀንዱን ለመጠጫ፣ ጅራቱን ለመግረፊያ እንጠቀማለን፡፡ በፖለቲካዊ አንድምታም ከሄድን፣ ነጋሪት ተጎስሞ አዋጅ የሚነገረው ከበሬ ቆዳ ተሰርቶ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ እበቱ ራሱ ማገዶ ይሆናል፡፡
በሬ ቁርጥምጥም አድርገን የምንጠቀመው ፍጥረት ነው፡፡ ለዚህ ሁሉ ፈቃደኛ የሆነም ነው፡፡ ይህ ነው መነሻዬ፤ ቆዳ ላይ ያተኮርኩበት፡፡ በሬ ያ ሁሉ ቆዳው ላይ ያለ ዥንጉርጉር፣ ትልቅም ይሁን ትንሽ ነቁጥ፣ ብዙ በሬ አያደርገውም፤ እነዛ ተባብረው ነው በሬ የሚያሰኙት፡፡ ይህ እሳቤ የበለጠ ስለሳበኝ ነው ያተኮርኩበት፡፡
በተለይ በገጠር አካባቢ ቆዳ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት ነው ያለው---
እውነት ነው፡፡ የገጠሩ የቆዳ አጠቃቀም ከተነሳ አይቀር በጣም የሳበኝ፣ አጎዛውን ግድግዳ ላይ ሰቅለው፣ ለጌጥና ለአይን ማረፊያ ያደርጉታል፡፡ ከዚያ ያወርዱና አንጥፈው ይተኙበታል፡፡ ሲተኙ ደግሞ ያሸትቱታል፡፡ እነዚህ የውበት ልምምዶች ሁለት አይነት ነገር አላቸው፤ ተግባራዊም ውበታዊም። እነዚህን ሁለት መልክ ያላቸው ስራዎች ለእይታ ማቅረብ በምዕራባዊያን አረዳድ፤ “ማቴሪያል ካልቸር” ነው የሚሉት፡፡ ምን ማለት ነው? ሰው ለዕለት ተዕለት ኑሮው የሚጠቀምባቸው እንጂ የተጠበበት አርት አይመስላቸውም፡፡ እንደኔ እምነት ግን ሙዚየም ባለማቅረባቸው እንጂ እነዚህ ስራዎች በምዕራባዊያን ሙዚየሞች ከሚታዩ ስዕሎች በላይ ጠንካራ ናቸው፡፡
እንደውም አሁን በዘመናዊ ስነ-ጥበብ ትልቁና ጠንካራ መሆን አለበት የሚባለው አርቲስቱ በአይን ታይቶ ከሚያበቃና ዋው ከሚያስብል ስራ በዘለለ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የሆኑ ጉዳዮችን የሚያነሳ፣ የሚቀሰቅስና የሚታገል ነው። እነዚህ አርቲስቶች ከእለት ተእለት ህይወታቸው ጋር የተቆራኙ ነገሮችን ወስደው ለታይታና ለእይታ ብለው ሳይሆን ከልብ የመነጨ ሀሳባቸውን ያንጸባርቁባቸዋል፡፡ ለነዚህ ስራዎች ደግሞ ቦታ ተሰጥቶ መካተት አለባቸው የሚል ሀሳብ ይዤ  ነው የተነሳሁት፡፡
ታዲያ ስራዎችህ ተቀባይነት አግኝተውልሃል?
አሁን ይሄን የሚደግፉልኝ ሱዛን ፎግል፣ ካሮል ዳንከል እና ሌሎችም ፀሀፊዎች አሉ፡፡ እነዚህ ፀሀፊዎች የአፍሪካዊያን አርት በምዕራባዊያን ሙዚየም ለእይታ ሲቀርብ እንደ እቃ ነው የሚከለኮለው እንጂ እንደ ሪፋይን አርት በስርዓቱና በክብር አያቀርቡትም፡፡ የራሳቸውን ግን ከአምላክና ከሰማይ የወረደ አድርገሽ እንድትመለከቺው፣ ያንን ስሜት ይፈጥሩብሻል፡፡ እኔ እንደምታዪው፤ እነዚህን ሞሰቦች፣ አገልግሎችና ሌሎች እቃዎችን ከእቃነት በዘለለ ራሳቸው ጥልቅ የሆነ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ እሳቤ ያላቸው መሆኑን ለማሳየት ሞክሬያለሁ፡፡ ቅድም የጠቀስኩልሽ ፀሀፊዎች፣ይህንን ስራና አስተሳሰብ ይደግፉታል፤ተቀባይነቱ የሚያጠራጥር አይደለም፡፡
በአውደ ርዕዩ ላይ ከቀረቡት መካከል የገረመኝ፣ ትልቁ በቆዳ የተለበጠው መሶብ፣ በቁልፍ ተቆልፎ በርካታ የቁልፍ መክፈቻዎች ከበውታል፡፡ እስቲ የዚህን መሶብና የቁልፍ መክፈቻዎቹን ምስጢር አብራራልኝ?
በዚህ መሶብና በቁልፉ ማስተላለፍ የፈለግኩት እንጀራ፣ ተስፋና ዕድልን ነው፡፡ የእቃዎቹን አቀራረብ installation (ኩልኩል) እንለዋለን። ጥልቅ የሆነውን የሰው ህይወትና በሕይወቱ የሚገጥሙትን ጉዳዮች ሊገልፅ በሚችል መንገድ የምናስቀምጥበት ነው:: ሰው ተስፋ አለው፣ ዕድልም አለው፣ እንጀራም አለው፡፡ ተስፋው ያለ ማቋረጥ ይሄንን ቁልፍ ለመክፈት እንዲሞክር ያደርገዋል። ዕድሉ ሙከራውን ያሳካለታል፡፡ እንጀራው በነዚህ ሂደቶች የሚገኝ ስኬት ነው፡፡ ይህ የተቆለፈ መሶብ በስሩ ከተደረደሩት መዓት ቁልፎች አንዱ ይከፍተዋል። የሚከፍተው ቁልፍ ምንም ምልክት የለውም፡፡ ይሄ የብዙ ሰዎችን ሀሳብ ይሞግታል፡፡
በምን መልኩ?
ቁልፉ ከእነዚህ ቁልፎች መሀል እንዳለ እናውቃለን። የሰው ልጅ ከእነ ዕድሉ፣ ከእነ ስጦታው ነው የተፈጠረው፤ ነገር ግን አብዛኛው የሚሞክርና የሚጥር አይደለም፡፡ አንድ ሰው ተስፋ ካደረገ፣ ከጣረ ዕድሉ ቁልፉን እንዲያገኝ ያደርገዋል። ይሄ ሙግት በውስጥሽ መመላለሱ አይቀርም፡፡
ለጉብኝት የሚመጡ ሰዎችን የዚህን ሞሰብ ቁልፍ ሞክረው እንዲያገኙ ስትጋብዝ አይቻለሁ። እኔም በርካታ ቁልፎችን ሞክሬ መሶቡን መክፈት አልቻልኩም፡፡ ለመሆኑ እስካሁን ሞክሮ የተሳካለትና የከፈተው አለ?
የሚገርምሽ አንድ ልጅ ሞክሮ ተሳክቶለታል፡፡ በውስጡ ምን አገኘ የሚለውን አሁን አልናገረም፤ ነገር ግን ይሄ ልጅ መክፈት አለብኝ ብሎ ቆርጦና ወስኖ ነው የተቀመጠው፡፡ ልጁ ምን ያህል ሰዓት  ታግሶ ወስኖ እንደተቀመጠ ስመለከት፣ የልጁ ቁርጠኝነት ለብዙ ሰው ትምህርት የሚሆን ነው። ህፃናትም በብዙ ትዕግስት ፈልገው ፈልገው፣ “እባካችሁ የትኛው ነው፣ አሳዩን?” እስከ ማለት ደርሰዋል፡፡
አንተ ግን ቁልፉ የትኛው እንደሆነ ታውቀዋለህ?
በፍፁም! እኔም አላውቀውም፡፡ አንድም የሌላው ህብረተሰብ አካል ለመሆን፣ በሌላም በኩል ለራሴ እንዳላዳላ በሚል አላውቀውም፡፡ እንግዲህ በምዕራቡ ዓለም ስዕል በእጅ አይነካም፤ አይዳሰስም፤ በቃ ሀይማኖታዊ ነገር አድርገው ነው የሚያስቀምጡት። አምስት ሜትር ከስዕሉ ርቀሽ ነው የምትመለከቺው። እኛ ጋ ትነኪዋለሽ፣ ትዳስሺዋለሽ፣ የሰቀልሺውን ራሱ አውርደሽ ትተኚበታለሽ፤ ስለዚህ የሚዳሰስ የሚታይና የሚሸተት ሥራ ነው የምንሰራው፡፡
አውደ ርዕዩን ብዙ የውጭ ዜጎች ሲጎበኙት ተመልክቻለሁ፡፡ ጎብኝዎች የሰጡህ አስተያየት ምን ይመስላል?
ያገኘኋቸው ሁሉ በጣም ፍላጎት ያሳደረባቸው ነገር ምን መሰለሽ? ወይ ዘመናዊነቱ ውስጥ ጥልቅ ብለህ አልገባህ ወይ በጣም ባህላዊ በሚባል መንገድ አልመጣህ፤ ሁለቱን አቻችለህ ስለምትሞግተን እኛም የሀሳብ ለውጥ ለማድረግ ተመችቶናል፡፡ በሌላ በኩል በአይን ከመታየት አልፎ እንድንነካ፣ አገላብጠን እንድናይ ዕድል አግኝተናል፡፡ የሚዳሰስ የሚሸተት የሚታይ ስዕል ማየታችን አዲስ ስሜት ፈጥሮብናል ሲሉ  ተናግረዋል፡፡
ሌላ መናገር የምፈልገው ነገር፣ በምዕራባዊያን ፕላት ፎርም ውስጥ የተካተተው የስነ- ጥበብ ፍልስፍና እና ታሪክ የሌላውን አለም ያላቀፈ ነው የሚል ሙግት አለ። እነ ፒካሶ በተነሱበት ዘመን በተጓዳኝ በአፍሪካ፣ በላቲን አሜሪካ፣ ከምዕራቡ ተመጣጣኝ የሆኑ የአርት ክንውኖች የነበሩ ቢሆንም የተካተተው የምዕራቡ ብቻ ነው የሚል የሀሳብ ፍጭት ስላለ፣ በዚያ ሙግት ውስጥ የእኔን ትንሽ ነፀብራቅ ለማሳየት ነው እየሞከርኩ ያለሁት፡፡
በስዕሎቹ በቆዳ የተለበጠ ቴሌቪዥን ተመልክቻለሁ። ትርጉሙ ምንድን ነው?
ቴሌቪዥን በአገራችን የማህበረሰብን ስትራክቸር የቀየረ ነው፡፡ ምን ማለት ነው--- ቀደም ባለው ጊዜ ቤት ውስጥ ስንቀመጥ፣ ትልልቅ ሰዎችን ከብበን ነበር፡፡ ማዕከል የሚሆኑት እናት አባቶቻችን ናቸው። አሁን ደግሞ ቴሌቪዥን ከበን ነው የምንቀመጠው፡፡ የቴሌቪዥኑ አቀማመጥ ደግሞ ለሁሉም ለህፃን ለአዋቂው እንዲመች ተደርጎ ነው የሚዘጋጀው፡፡ ዱሮ ተረት፣ ምክር የምንሰማው ከታላላቆቻችን የሚጠቅመንን ብቻ ነበር፡፡ አሁን ቴሌቪዥን የምናየው ያለ ዕድሜ ገደብ ነው፡፡ ለልጅ ነው ለአዋቂ ነው የለም፣ ያውም ተገምግሞ በማያልፍ የትኛውም ሀሳብ ውስጥ አብረን እንሰለፋለን፡፡ ይሄ ለእኔ አስጊ ነው፡፡ ቴሌቪዥኑን ቆዳ ያለበስኩት፣ ከቴሊቪዥኑ የሚወጣውን እኛ ብናስተካክለውና ብንዋጀው የሚል ምኞቴን ለማስተላለፍና የሚጠቅመንን ብቻ የምንሰማበት ልናደርገው ብንችል የሚለውን ህልሜን ለማሳየት ነው፡፡ እንግዲህ የሀሳብ ተቃርኖውን የሚያሳይ ነው። ቆዳው የእኛ ነው፤ ቴክኖሎጂው የእነሱ ነው። ይሄ በእጄ የያዝኩት ስልክ ጥሩም መጥፎም አይደለም፤ በስልኩ የምጠቀምበት ነገር ነው ጥሩና መጥፎ ሊያሰኘው የሚችለው፡፡ በስልኩ ደውዬ “ሰው ግደል ወይም የወደቀ ሰው አንሳ” ስል ውጤቱ ይወሰናል ማለት ነው፡፡
አሁን ደግሞ በአሜሪካ ስላሳየኸው አውደ ርዕይ  እና በቅርቡ በግብፅና በኢኳዶር ስለምታሳየው የስዕል አውደ ርዕይ አጫውተኝ ----
ቀደም ብዬ እንደነገርኩሽ፣ አንድም ቀን ታዋቂ ለመሆን ብዬ ከአርት ጋር ተቆራኝቼ አላውቅም፤ ነገር  ግን በፍቅርና በፍላጎት ተሞልተሽ ስትሰሪ፣ አይን ውስጥ ትገቢያለሽ፡፡ በመጀመሪያ ያገኘሁት እድል በአሜሪካ ላስቬጋስ በኔቫዳ ዩኒቨርሲቲ የሚገኝ የስነ-ጥበብ ተቋም ነው፡፡ በማይመች አካባቢ ውስጥ ሆኜ በባህርዳር ለአምስት ዓመታት ሥነ-ጥበብ ላይ በመስራቴ በተለይም ከወጣሁበት አካባቢ ሀይለኛ ግንነት ያለው ስራ መፍጠር በሚል “ፐብሊክ ሌክቸር” ሳደርግ፣ በተጨማሪም ስራዎቼን “ባሪክ” ሙዚየም ውስጥ ከንግግሬ ጎን ለጎን ለእይታ አቅርቤ ነበር፡፡ ከዚያም ለሶስት ሳምንታት ያህል ግራንት ሆል ጋለሪ ሆል ውስጥ ስራዎቼ ለእይታ በቁ፡፡ ቦልደርሲቲ በሚባል ከተማም ስራዎቼ ለህዝብ ለእይታ በቁ፡፡ በዚያው ከተማም ለህዝብ ንግግር አድርጌአለሁ። ይሄ በጣም ያስደሰተኝ ኢትዮጵያን የማያውቁ ሰዎች ገጥመውኝ ነበር፡፡ በእኔ ስራ ምክንያት ኢትዮጵያን ማወቃቸው ትልቅ ደስታ ፈጥሮብኛል፡፡ እነ ኃይሌ ገ/ሥላሴን እያወቁ ኢትዮጵያን አያውቁም፡፡ ለእነዚህ ሰዎች ስለ ኢትዮጵያ መናገሬ ያስደስተኛል። እርግጥ ነው ስሄድ አበባ ይዞ የተቀበለኝ የለም፤ የሰራኋቸውን ለእይታ ያቀረብኳቸውን ስራዎቼን ብዙ ግምት ውስጥ ያስገባ የለም፤ ሆኖም ኢትዮጵያን አስተዋውቄያለሁ፡፡ እርግጥ ሲጠሩኝ ከወጣሁበት አካባቢና ባህል ጋር የተቆራኘ ሥራ በመስራቴ ሁኔታዎች በማያበረታቱበት ድባብ፣ በፈተና ውስጥ ያለማቋረጥ የስዕል አውደ ርዕይ ለአምስት ዓመት በማቅረቤ ነው፡፡ በባህርዳር በቆየሁባቸው በነዚህ ጊዜያት አመታዊ አውደ ርዕዮች እንዲኖሩ አድርጌያለሁ፡፡
ሁለቱ ላይ በተለይ የአዲስ አበባ አርቲስቶች እንዲሳተፉ በማድረግ፣ ባህርዳርን አማራጭ የስነ-ጥበብ ማዕከል የማድረግ ህልሜን ለማሳካት ሙከራዬን የጀመርኩበት ነው፡፡ “ጥበበ ባህርዳር” “አርት ኦፍ ዘ ናይል” በተሰኙ ኤግዚቢሽኖች ነው ይህን የሰራሁት። በኋላም በግሌ ሦስት ኤግዚቢሽኖች አቅርቤያለሁ፡፡ በብሔራዊ ሙዚየምም “ሀገረ ቀለም ኢትዮጵያ” የተሰኘ በሀሳብም፣ በቴክኒክም ሆነ በቀለም በዛና ተለቅ ያለ ኤግዚቢሽን ነበረኝ። አሁን በሶሻል ሚዲያም በርትቼ እየሰራሁ ነው፡፡ አንዳንድ ሰዎችም በኔ ተነቃቅተው እየፃፉ ይገኛሉ። ናይጄሪያ በሚታተም “ታይምስ” የተሰኘ መፅሄት ላይ “ዘ አርቲስት ኦፍ ናሽናል ኮንሺየስነስ” በሚል ርዕስ ሽፋን አግኝቻለሁ፡፡
በግብፅና በኢኳዶር ስለምታቀርበው አውደ ርዕይ ንገረኝ---?
በኢኳዶር የሚካሄደው ዓለም አቀፍ ሰሚት ነው። በግብፅ ደግሞ “ኢንተርናሽናል አርት ሲምፖዚየም” ከአፕሪል 12 እስከ 24 ቀን 2018 ይካሄዳል፡፡ በዚያ ላይ እሳተፋለሁ፡፡ በዚህ ሁሉ ደስኛ ነኝ፡፡ አገራችን የ3 ሺህ ዓመት ታሪክ ያላትና የባህልና ታሪክ አገር መሆኗ፣ ለአንድ የፈጠራ ሰው በተለይ በስነ-ጥበብ ሙያ ውስጥ ላለ ሰው እድለኝነት ነው፡፡ ብዙ የምንሰራበት እድል አለ፡፡ ህልሜ ስዕልን ለእይታ አቅርቦ ከመሸጥ በዘለለ ጠንካራ ንቅናቄ ለመፍጠር ነው፡፡ ይህ ደግሞ ይሳካል፡፡  


· የደም ዓይነቱ A እና O የሆነ ኩላሊት ለጋሽ ይፈልጋል
         · ለአርቲስቱ ገቢ ለማሰባሰብ የባንክ አካውንት ተከፍቷል
         · ከቤተሰቡ ኩላሊት ለመለገስ የተደገረው ሙከራ አልተሳካም
              ናፍቆት ዮሴፍ

    ከ40 ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ ኪነ- ጥበብ የማይተካ ሚና ሲጫወት የቆየው የመድረክ ፈርጥ አርቲስት ፍቃዱ ተክለማሪያም ሁለቱም ኩላሊቶቹ ከጥቅም ውጪ በመሆኑ ሳቢያ ህይወቱን ለመታደግ የሚያስችል የድጋፍ ጥሪ ቀረበ፡፡ ባለፈው ሐሙስ አርቲስቱን ለመታደግ የተቋቋመው ኮሚቴ በአፍሮዳይት ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ ህዝብ የአርቲስቱን ነፍስ ለማዳን እንዲረባረብ ጥሪ የቀረበ ሲሆን ጉዳዩ ለህዝብ ይፋ ሳይሆን ከቤተሰቡ በሚለገስ ኩላሊት ህክምና ሊያደርግ የነበረው ሙከራ ከለጋሾቹ የጤና ሁኔታ ጋር በተያያዘ ሳይሳካ መቅረቱ ተገልጿል፡፡
አርቲስቱ “ገንዘብ አትለምኑ ህዝብ አታስቸግሩ፤ የሙያውም ክብር አይደፈር፤ እኔም ከነክብሬ ልሙት” በማለት ጉዳዩ ለህዝብ ይፋ ሆኖ ገንዘብ እንዳይሰበሰብ አጥብቆ መጠየቁን የገለፁት የኮሚቴው አባላት፤ ምንም እንኳን አርቲስቱ ባይደግፈው አይናችን እያየ አርቲስቱን ማጣት ስለሌለብን ጉዳዩን ለህዝብ ይፋ አድርገነዋል ብለዋል፡፡
የአርቲስቱ ሁለቱም ኩላሊቶች ሥራ ለማቆም ጥቂት ጊዜ እንደቀራቸው የተነገረ ሲሆን ወደ ዲያሊስስ ሳይገባ በፊት በውጭ አገር በጥሩ ህክምና የኩላሊት ንቅለ ተከላ እንዲደርግ አስፈላጊውን እገዛ በማድረግ ያገለገለው ህዝብ የአርቲስቱን ውለታ እንዲመልስ ጥሪ ቀርቧል፡፡
ህዝቡ በመጀመሪያ በፀሎት እንዲያግዘውና ከዚያም የኩላሊትና የገንዘብ ልገሳ እንዲያደርግለት ተጠይቋል፡፡
“አርቲስቱ ሙሉ በሙሉ ኩላሊቱ ስራ አቁሞ አልጋ ላይ ተኝቷል፡፡” እየተባለ የሚነገረው ፍፁም ሀሰት እንደሆነ የገለፁት የኮሚቴው አባላት፤ አርቲስቱ አሁንም በስራ ላይ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
የኮሚቴ አባላቱ አርቲስት ቴዎድሮስ ተሾመ፣ ሀይሉ ከበደ፣ መቅደስ ፀጋዬ፣ ቴዎድሮስ ተስፋዬ፣ ውድነህ ክፍሌና መሰረት መብራቴና ወዳጁ ሳሙኤል ብርሃኔ ሲሆኑ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አጎዛ ቅርንጫፍ የተከፈተው የገቢ ማሰባሰቢያው የባንክ ቁጥር 1000239345488 በአርቲስት መሰረት መብራቴ፣ በመቅደስ ፀጋዬና በሳሙኤል ብርሃኔ ስም ተከፍቶ ስራ መጀመሩም በዕለቱ ተገልጿል፡፡
በሌላ በኩል በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያን አርቲስቱን ሊረዱ የሚችሉበት “Go fund me” አካውንት በአርቲስት ቴዎድሮስ ተሾመ ስም የተከፈተ ሲሆን በዚህ አካውንት “Please help save Fekadu” ብለው በመግባት የበኩላቸውን እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል፡፡ ከዚህ አካውንት 75 ሺ ዶላር የሚጠበቅ ሲሆን ከተከፈተ ጀምሮ 2015 ዶላር ገቢ መደረጉን አርቲስት ቴዎድሮስ ተሾመ ተናግሯል፡፡
ለህክምና ምን ያህል ወጪ እንደሚያስፈልግውና በአገር ውስጥ የኩላሊት ንቅለ ተከላ በስኬት እየተካሄደ ወደ ውጭ አገር ሄዶ መታከም ለምን አስፈለገ በሚል ለተነሳው ጥያቄ፣ አርቲስቱ ከስኳርና ከሌሎች የጤና ችግሮች ጋር በተያያዘ ህክምናው ውስብስብ በመሆኑ እንዲሁም ኩላሊቶቹ መቀየር እንዳለባቸው ቀድሞ የተደረሰበት በመሆኑ ከአገር ውስጥ ይልቅ ውጭ በተሻለ ቴክኖሎጂና ህክምና ንቅለ ተከላ ቢያደርግ እንደሚሻል በመነገሩ፣ የግድ ውጭ ሄዶ መታከም እንዳለበት ተወስኗል ተብሏል። የህክምናውን ወጪ በተመለከተ በተለያዩ አገራት የተለያዩ የገንዘብ መጠኖች መገለፃቸውንና ለአርቲስቱ ህክምና የሚወጣው ወጪ እንደሚገኘው የህዝብ ድጋፍ እንደሚወሰን ተገልጿል፡፡ በየትኛውም ሁኔታ ግን የተሻለውን ህክምና እንዲያገኝ እስከ መጨረሻው ጥረት እንደሚደረግ የገለፁት የኮሚቴው አባላት፤ በቀጣይ የገቢ ማሰባሰቢያ የኪነ-ጥበብ ፕሮግራሞች እንደሚካሄዱ፣ በየደረጃውም ይፋ እንደሚደረግ ተገልጿል፡፡ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ በርካታ አንጋፋና ወጣት የኪነ-ጥበብ ሰዎች የተገኙ ሲሆን አርቲስት ደበበ እሸቱ፣ አረጋኸኝ ወራሽ፣ አብራር አብዶ፣ ወለላ አሰፋ፣ ፍቅርተ ጌታሁን፣ ሽመልስ አበራ፣ ዳዊት ፍሬው፣ ሀይሉ ሶፊ እና ሌሎችም ተገኝተዋል፡፡
“ሞት በኩላሊት ይብቃ” የተባለ ማህበር ፕሬዚዳንት የሆኑትና የኩላሊት ህመምተኛው አቶ ኢዮብ ዳዊት በሰጡት አስተያየት፤ “የእውቁ አርቲስት የኩላሊት ህመም በኢትዮጵያ በየጥጋጥጉ በኩላሊት ህመም ለሚሰቃዩ ትንሳኤ ነው” ያሉ ሲሆን ይህ ኮሚቴ አርቲስቱ ከዳነ በኋላ ስራውን በመቀጠልና አርቲስቱንም አምባሳደር በማድረግ ለሌሎች ህሙማን እንዲተርፍና የኩላሊት ህክምና ሆስፒታል እስከማሰራት ጥረት እንዲያደርጉ ለኮሚቴው አባላት ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የዘመናችን የፊዚክስ ሊቅ ፕሮፌሰር ስቴፈን ሃውኪንግ በተወለደ በ76 አመቱ ባለፈው ረቡዕ ከዚህ አለም በሞት መለየቱን ተከትሎ፣ የእንግሊዟን ጠቅላይ ሚኒስትር ቴሬሳ ሜይን ጨምሮ በርካታ የአለማችን መሪዎች፣ ሳይንቲስቶች፣ አርቲስቶችና ተቋማት የተሰማቸውን ሃዘን በመግለጽ ላይ ይገኛሉ፡፡
ስቴፈን ሃውኪንግ ለአለማችን ሳይንስ እጅግ የላቀ አስተዋጽኦ ያበረከተና ስለ ህዋው ያለንን እውቀት በማዳበር ረገድ አለማቀፍ አስተዋጽኦ ያበረከተ ታላቅ ሰው ነበር ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ቴሬሳ ሜይ፤ ሳይንቲስቱ በመላው አለም ለሚገኙ በርካታ ዜጎች የመንፈስ መነቃቃት ምንጭ እንደነበር በማስታወስ በሞቱ የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል፡፡
የአሜሪካው የጠፈር ተቋም ናሳ በትዊተር ገጹ ላይ ባሰፈረው የሀዘን መግለጫ፤ ስቴፈን ሃውኪንግ ታላቅ የፊዚክስ ሊቅና የሳይንስ አምባሳደር ነው። የአእምሮው ውጤት የሆኑት ንድፈ ሃሳቦች፣ በዕድሎች ወደተንበሸበሸ ህዋ እንድንገባ በር የከፈቱ ናቸው ሲል የሳይንቲስቱን የላቀ አስተዋጽኦ በክብር ዘክሯል፡፡
የአውሮፓ የጠፈር ተቋም በበኩሉ፤ ስቴፈን ሃውኪንግ ህልማችንን እውን ከማድረግ የሚገታን አንዳች ሃይል እንደሌለ ያሳየን መንገድ መሪያችን ነው ሲል ያወደሰው ሲሆን የጎግል ኩባንያ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሰንዳር ፒቻይ በበኩላቸው፤ አለማችን የላቀ አእምሮና እሳት የላሰ ሳይንቲስት አጣች ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ፣ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ፤ ስቴፈን ሃውኪንግ በምርምር ስራዎቹ ለሳይንስ እድገትና ለአለማችን ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል በማለት እማኝነታቸውን የሰጡ ሲሆን፣ ኬቲ ፔሪ፣ ሻሮን ስቶን እና ጂም ኬሪን ጨምሮ በርካታ የሆሊውድ ዝነኞችና ድምጻውያንም ለሳይንቲስቱ ያላቸውን አክብሮት በተለያዩ መንገዶች ገልጸዋል፡፡
ታዋቂ የአለማችን የጠፈር ተመራማሪዎች፣ ሳይንቲስቶችና የዩኒቨርሲቲዎች ፕሮፌሰሮች የሃዘን መግለጫቸውን ያወጡ ሲሆን ካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ በርካታ የእንግሊዝና የሌሎች አገራት ዩኒቨርሲቲዎችና የምርምር ተቋማት ስቴፈን ሃውኪንግንና በሳይንሱ ዘርፍ ያበረከታቸውን አስተዋጽኦዎች የሚዘክሩ የተለያዩ ዝግጅቶችን ማከናወናቸውንም ሲኤንኤን ዘግቧል፡፡


ባለፈው ረቡዕ ለ80ኛ ጊዜ የግጥም ምሽቱን በድምቀት ያካሄደው “ጦቢያ ግጥም በጃዝ” የዛሬ ሳምንት ቅዳሜ ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች ከመጡ የውጭ ገጣሚያንና የኪነ-ጥበብ ሰዎች ጋር ልዩ የግጥም በጃዝ ዝግጅቱን ከምሽቱ 12፡00 ጀምሮ በራስ ሆቴል አዳራሽ በጥምረት ያካሄዳል፡፡
በምሽቱ ከአሜሪካ፣ ከዴንማርክ፣ ከደቡብ አፍሪካና ከጀርመን የሚመጡ እውቅ ገጣሚያን ሥራቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን ገጣሚ ነቢይ መኮንን፣ ፍሬዘር አድማሱ፣ ምህረት ከበደ፣ ረድኤት ተረፈ፣ ጆርጋ መስፍን፣ ምስራቅ ተረፈ እና ጣሰው ወንድም ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል፡፡


  “…እንደጥንት ዘመዶቼ ወይ እንደዛሬዋ እማማ በየደጀሰላሙ አልጎዘጎዝም፡፡ በቅዱስ መጽሐፍት ቸርቻሪዎች አልጠፈርም፡፡ እዛ ፔርሙዝ ውስጥ ያለው ሻይ ሳይሆን ደም ነው ብልህ አንተ ምን አገባህ? አንቺስ? አሥራት ሁሉን ዝቅና ከፍ ለእኔ ትታ ተኝታለች፡፡ ከንፈሮቿ ስስ ቅጠል ይመስላሉ። የታችኛው ለአመል አበጥ ይላል፡፡ በእኔ በኩል ያለው ቀለሙ ሙሉ በሙሉ አለቀቀም፡፡ በቀስታ እጄን ሰድጄ በአመልካች ጣቴ ያን ለአመል ያበጠ ቦታ ነካሁት፡፡ ዐይኖቿን በትንሹ ገልጣ ፈርጠም አለች። ቀኝ እጇን አንስታ በዳበሳ ፊቴን ነካችኝ፡፡ ጣቴ ከንፈሯ ላይ መሆኑን ረሳሁ፡፡ ዐይኖቿን ስትገልጥ አቡሽ እወድሃለሁ እኮ … መቼ ይገባሃል? አለችና ወደ በለጠ ጥልቅ እንቅልፍ ለመግባት አይነት ተመቻቸች፡፡…” (አዳም ረታ አፍ፤ 205)
በተለየ የአፃፃፍ ብቃትና ዘይቤው የሚታወቀው አንጋፋው ደራሲ አዳም ረታ “አፍ” የተሰኘ አዲስ ረዥም ልብ ወለድ መፅሐፍ ለአንባቢያን የበቃ ሲሆን የፊታችን ማክሰኞ ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር እንደሚመረቅ የምርቃቱ አዘጋጅ ኢጋ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ገለፀ፡፡
በምርቃት ስነ-ስርዓቱ ላይ ደራሲውን ጨምሮ በርካታ አድናቂዎቹ፣ ደራሲያንና ገጣሚያን የሚታደሙ ሲሆን በመፅሐፉ ላይ ዳሰሳ ይቀርባል። ከዚህም በተጨማሪ ግጥምና ወግ እንዲሁም ከመፅሐፉ የቀነጨቡ ታሪኮች ይነበባሉ፡፡ ደራሲው አዳም ረታም በመፅሐፉ ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡ በ254 ገፆች የተቀነበበው መፅሃፉ፤ በ80 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ ደራሲው ከዚህ ቀደም “ማህሌት”፣ “ግራጫ ቃጭሎች”፣ “አለንጋና ምስር”፣ “እቴሜቴ የሎሚ ሽታ”፣ “ከሰማይ የወረደ ፍርፍር”፣ “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ”፣ “ህማማትና በገና”፣ “መረቅ” እና “የስንብት ቀለማት” የተሰኙ መፅሐፍቶችን ለንባብ አብቅቷል፡፡

 የዝነኛው ደራሲ ጃክ ሂግኒስ ተዋቂ መፅሐፍ የሆነው “ድሪንክ ዊዝ ዘ ዴቭል” በተርጓሚ መልዓከ ተሰማ “ሰዎቹ” በሚል ርዕስ ወደ አማርኛ ተመልሶ ለንበብ በቃ፡፡
የጃክ ሂግኒስ ሌሎች ሥራዎች በሚሊዮን ቅጂዎች እንደተቸበቸቡለትና አብዛኛዎቹ መፅሐቱ በ38 ቋንቋዎች ተተርጉመው በመላው ዓለም መሰራጨታቸውን፣ ብዙዎቹም ወደ ፊልምነት መቀየራቸውን ተርጓሚው ጠቁሟል፡፡ “ሰዎቹ” በሚል ወደ አማርኛ የተተረጎመውም መፅሐፍ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች በአፅንኦት ያወደሱትና ያደነቁት ነው ብሏል - ተርጓሚው፡፡
“ሰዎቹ ለፖለቲካ ድርጅታቸው ህልውና በሚል ሽፋን የግል ቢዝነሳቸውን ለማስፋትና ሚሊየነር ለመሆን በሚሊዮን ዶላር የሚቆጠር የወርቅ ነዶ ዘርፈዋል፡፡  በዚህ ሂደት ውስጥ ደግሞ የሰው ደም እንደ ዋዛ ተገብሯል… ዓለማችንም መቼ እና እንዴት እነኚህን የፖለቲካ ቧልተኛና ዳንኪረኛ “ነፃ አውጪዎችን” ነፃ አውጥታ ወደ ትከክለኛው የፍትህና እውነት ትራክ ላይ አሳፍራ መጓዝ እንዳለባት ግራ የተጋባች መስላለች” … ይላል መፅሐፉ ጀርባ ላይ የሰፈረው ቅንጭብ ታሪክ። በ216 ገፆች የተቀነበበው መፅሐፉ፤ በ61 ብር ለሽያጭ ቀርቧል፡፡