Administrator

Administrator

በአዲስ አበባ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ፋብሪካ ለመገንባት ከአውሮፓ ኩባንያ ጋር ስምምነት መደረሱ ተዘግቧል፡፡
የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በረኦ ሐሰን፣ መቀመጫውን አውሮፓ ካደረገው ባትስዋፕ አውቶሞቲቭ ኃላፊዎች ጋር በጉዳዩ ዙሪያ ተወያይተዋል።
ትብብሩ አዲስ አበባ ውስጥ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ማምረቻ ፋብሪካ መትከል፣ የባትሪ ማምረቻና ጥናትና ምርምር እንዲሁም የአረንጓዴ ትራንስፖርት ዘርፍ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ማቋቋምን ያካትታል።
በ2026 በሚተገበረው የስምምነቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ፣ 240 የሙከራ የኤሌክትሪክ ጭነት ተሽከርካሪዎች ሲገነቡ፤ 10 አውቶማቲክ የባትሪ መለዋወጫ ጣቢያዎች በአዲስ አበባ ይዘረጋሉ።
ስምምነቱ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአረንጓዴ እንቅስቃሴ ዘርፍ ቁልፍ ተዋናይ ከመሆን ራዕይዋ ጋር የተጣጣመ ነው መባሉን ስፑትኒክ ዘግቧል፡፡
ሩሲያ ቤተሰቦች ልጆች እንዲወልዱ እያበረታታች ሲሆን፤ ለዚህም ሦስት ወይም ከዚያ በላይ ልጆች ለሚወልዱ ቤተሰቦች ብዙ ጥቅማጥቅሞችን አቅርባለች፡፡ ጥቅማጥቅሞቹ የሚከተሉትን ይጨምራሉ፡-
• እስከ 1 ሚሊዮን ሩብልስ የሚደርስ የገንዘብ ጉርሻ
• መኖሪያ ቤት መገንቢያ መሬት
• ነፃ የትራንስፖርት አገልግሎትና የት/ቤት ምገባ ለልጆች
• ነጻ የሕክምና አገልግሎቶች
• የመብራትና የነዳጅ ክፍያዎች ከቀረጥ ነፃና ቅናሽ
• ዓመታዊ የቤተሰብ ጉዞዎችና የእረፍት ጊዜያት
ይሄ ፖሊሲ ወደፊት ወላጅነትን ወደ ኢንቨስትመንት የሚቀይር ነው ተብሏል፡፡
 
 
 
የአፍሪካ ቁጥር አንድ ቢሊየነር የሆኑት አሊኮ ዳንጎቴ፣ በኮትዲቯር የ160 ሚሊዮን ዶላር የሲሚንቶ ፋብሪካ ፕሮጀክት ማስጀመራቸው ተገለጸ፡፡ ይህም በምዕራብ አፍሪካ የኩባንያቸውን አሻራ የሚያጠናክር ነው ተብሏል፡፡
ከአቢጃን በስተሰሜን 30 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው አቲንጉዌ ውስጥ የተገነባው የዳንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካ፣ 50 ሄክታር የሚሸፍን ሲሆን፤ በዓመት 3 ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ የማምረት አቅም አለው፡፡
ፕሮጀክቱ ከ1ሺ በላይ ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆኑ የስራ እድሎችን እንደሚፈጥር የሚጠበቅ ሲሆን፤ ይህም ለወጣት አይቮሪያውያን ዕድሎችን ከመክፈቱም ባሻገር የአገሪቱን የግንባታ ዘርፍ ያሳድጋል ነው የተባለው፡፡
"ይሄ ከፋብሪካ በላይ ነው" ሲሉ የተናገሩት የዳንጎቴ ሲሚንቶ ኮትዲቯር ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሰርጌ ግቦታ፤ "በወደፊቷ ኮትዲቯር በራስ የመተማመን መግለጫ ነው" ብለዋል፡፡
አሊኮ ዳንጎቴ በበኩላቸው፤ ኢንቨስትመንቱ ለህዝቦቿ የምታመርት፣ የምትፈጥርና የምትገነባ አፍሪካን ለመፍጠር ካላቸው ራዕይ ጋር የሚጣጣም መሆኑን አፅንዖት ሰጥተዋል።
አዲሱ ፕሮጀክት የአካባቢውን ማህበረሰቦች በመሠረተ ልማት፣ በንፁህ ውሃ አቅርቦትና በጤና ክብካቤ መርሃ ግብሮች እንደሚደግፍም ቢሊየነር አፍሪካ ዘግቧል፡፡
 
 
 
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት የለውጥ ዓመታት እመርታዊ ስኬቶችን እያስመዘገበች የሚመጥናትን ከፍታ እየያዘች ትገኛለች። ለዘመናት የቁጭት እና እንጉርጉሮ ትርክት ምንጭ የነበረውን ዓባይን ገርታ የኃይል እና ብርሃን ምንጭ አድርጋለች፡፡
በንጋት ኃይቅ በምግብ ሉዓላዊነቷ ላይ ጉልህ ሚና የሚጫወት የዓሣ ምርት ማግኘት ችላለች፤ ዐዲስ የቱሪዝም መዳረሻ ደሴቶችንና ከተሞችን ፈጥራለች፡፡ የዓባይን የቁጭት ትርክት ወደ ድል እና አሸናፊነት ብስራት ቀይራለች፡፡
ተጨማሪ የኃይል ምንጮችን ከውኃ እስከ እንፋሎት፣ ከፀሐይ ብርሃን እስከ ኒውክሌየር ኃይል እና ነፋስ በመገንባት ላይ ናት፡፡ እነዚህ ሁሉ የሰንደቋን ከፍታ እና ተምሳሌትነት የሚያጎሉ ናቸው፡፡
ኢትዮጵያ ከገጸ ምድር ባሻገር በከርሰ ምድር ያሉ ሀብቶቿን ወደመጠቀም ተሸጋግራለች፡፡ በተፈጥሮ ጋዝ ማውጣት የታየውን ስኬት ለማላቅ፣ በነዳጅ ዘይትም ለመድገም ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ጀምራለች፡፡
የግብርና ዘርፉን ውጤታማነት ለማሳደግ የዐፈር ማዳበሪያ በራሷ ለማምረት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሳለች፡፡ ይህም የምግብ ሉዓላዊነታችንን ለማረጋገጥ የተጀመረውን ሥራ ይበልጥ የሚያጠናክር ሆኗል።
የሕዝቧን የአኗኗር ዘይቤ ለመቀየር ከቢሮ እስከ ግቢ በሚል ጀምራ፣ ከከተማ እስከ ገጠር ወደሚል ተሸጋግራለች፡፡ በአዲስ አበባ የተጀመረው የከተሞችን ገጽታ የመቀየር ንቅናቄ ዘመናዊነትን፣ የስማርት ሲቲ ጽንሰ ሐሳብን እና ሰውን ከተፈጥሮ የማስማማት ልምምድን ያስተዋወቀ ነው፡፡ ይህም የዲፕሎማሲ ማእከል የሆነችውን መዲናችንን በዓለማቀፍ ደረጃ ያላትን ገጽታ የሚያጎላ፣ የሰንደቃችንን ከፍታ የሚጨምር ነው፡፡
ከተማችንን የማዘመኑን ጅማሮ ወንዞቻችን በማከም የተፋሰሶችን ደኅንነት የሚያረጋግጥ ሆኗል፡፡ ከእንጦጦ ጀምሮ እየተሠራ ያለዉ የወንዞች ዳርቻ ልማት የአዋሽ ተፋሰስን ሥነ ምኅዳር ጭምር የሚያክም ለአካባቢ ጥበቃ አብነት ነው፡፡ የገጠር አኗኗር ዘይቤያችንን በማዘመን ኢትዮጵያን በበጎ የምትመሰል ሀገር የማድረግ ጥረታችንም ፍሬው እየታየ ነው፡፡ እነዚህ ሁሉ የሰንደቃችንን በኩራት መውለብለብ የሚያጎሉ የትጋታችን ውጤቶች ናቸው፡፡
ዛሬ የምናከብረው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በነፃነት ቀን የተገኘ አይደለም፤ ነፃ ሆኖ ለሌሎች ነፃነት ከፍ ብሎ ሲውለበለብ የታየ የነፃነት ምልክት እንጅ፡፡ ነፃነቱን ለማስከበር ግን ቀደምቶቻችን ደም፣ ሥጋ እና ዐጥንት ገብረዋል፡፡ ኢትዮጵያን የዓለም የነፃነት ቀንዲል አድርገው አስረክበውናል፡፡
ዛሬም እንደትናንቱ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በደም እና በዐጥንት ለማስከበር የቆረጡ ጀግኖች አሉን፡፡ በምድር፣ በአየር፣ በባሕር እና በሳይበር የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በማስከበር ሰንደቋ የነፃነት ተምሳሌትነቱ እንዲቀጥል የሚተጉ ጀግኖቻችን አሉ፡፡
የሰንደቅ ዓላማ ቀንን የምናከብረዉ በሁሉም ግንባር፣ በሁሉም ዓውድ ስለኢትዮጵያ ዋጋ የሚከፍሉ ጀግኖቻችንን በማመስገን፣ ሰንደቃችንንም በክብር ከፍ አድርገን በማውለብለብ፣ ለላቀ ከፍታው እንደምንተጋ ቃል በመግባት ነው፡፡ የተጀመሩ ትልልቅ የሰንደቅ ዓላማ ፕሮጀክቶችን ለማሳካት ደግሞ ያለስስት በጋራ መጣር፣ የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን ለማድረግ ማናቸውንም ዋጋ መክፈል ከዜጎች ይጠበቃል፡፡
እንኳን ለሰንደቅ ዓላማ ቀን አደረሳችሁ!
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም

በፊልሙ ላይ 70 የሚያህሉ ተዋንያን የተሳተፉበት ሲሆን ሰለሞን ሙሄ ፣ መኮንን ላዕከ፣ ዘላለም ይታገሱ ፣ንጉሱ መልጌታ፣ፍቅረተ ደሳለኝ፣ ህይወት ጌታሁን፣ሰለሞን ተካ፣ችሮታው ከልካይ እና ሌሎች አንጋፍና ወጣት ተዋንያን ተሳትፈውበታል ።

የቻይና ተመራማሪዎች ከአጥንት ስብራት ለማገገም ወራት ይፈጅ የነበረውን ሂደት የሚቀይርና በ3 ደቂቃዎች ውስጥ የተሰበረ አጥንትን የሚገጥም ግኝት ይፋ ማድረጋቸው ተዘግቧል፡፡
'ቦን -02' የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ ግኝት፤ ተጨማሪ ቀዶ ጥገና ሳያስፈልግ የተሰበሩ አጥንቶችን የሚገጥም ነው፡፡
በሃንግዙ ሰር ሩን ሾው ሆስፒታል የአጥንት ሕክምና ባለሙያ የሆኑት ሊን ዢያንፌንግ እንደገለጹት፤ ሕክምናው በመርፌ መልክ የሚሰጥና የተሰበሩ አጥንቶችን በደቂቃዎች ውስጥ አንድ ላይ እንዲጣበቁ የሚያደርግ ነው።
'ቦን 02' በሰው አካል ውስጥ ከገባ በኋላ በተፈጥሮ መንገድ እንዲዋሃድ ተደርጎ መሰራቱም ተመላክቷል።
ከዚህ በፊት ይደረግ እንደነበረው ማጣበቂያውን ለማስወገድ ሁለተኛ ቀዶ ጥገና ባለማስፈለጉም የኢንፌክሽን አደጋን ይቀንሳል ነው የተባለው።
በ'ዠይጂያንግ' ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች በተሰራው በዚህ ግኝትም፣ ከ150 በላይ የሚሆኑ ሰዎች ሕክምና በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን ኦዲቲ ሴንትራልን ጠቅሶ ኢቢሲ መዝናኛ አስነብቧል፡፡
የሬጌ ሙዚቃ አቀንቃኙ ድምጻዊ ጆኒ ራጋ፣ በአዲሱ "እሳት እና ውሃ" አልበሙ እና በአልበም ቅምሻ ፕሮግራሙ፣ ከቴክኖ ከሞን 40 ስልክ ሞዴል ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
ለበርካታ ዓመታት ድምጹ የጠፋው ጆኒ ራጋ ከሰሞኑ "እሳት እና ውሃ" የተሰኘ ሁለተኛ አልበሙን ይዞ መምጣቱ ይታወቃል፡፡
በአረርቲ ከተማ አስተዳደር አረርቲ ማርያም ቤተክርስቲያን ዓመታዊ የቅድስት ድንግል ማርያም ክብረ በዓል ላይ እየተሰራ ያለው ቤተክርስቲያን እየተጎበኘ ባለበት ‎ሰዓት፣ ለፊኒሺንግ ሥራ የተረበረበው እንጨት ተደርምሶ በርካታ ምዕመናን ላይ የሞትና የአካል ጉዳት መድረሱ ይታወቃል።
እስካሁን ትክክለኛ የሟቾችና ተጎጂዎች ቁጥር አልታወቀም። አሁንም ሰዎችን ከተናደው ርብራብ የማውጣት ስራ እየተሰራ ነው።
የአረርቲ ከተማ ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ፤ የጉዳቱ መጠን ከፍተኛ በመሆኑና ከእንጨት ርብራቡ ሥር ያልወጡ ሠዎች በመኖራቸው የጉዳት መጠኑን መገመት አስቸጋሪ እንደሆነ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ገልጿል።
ከሆስፒታል በተረጋገጠው እስካሁን የ22 ሠዎች ሕይወት ማለፉን፣ በተጨማሪ 55 ሰዎች ላይ ከመካከለኛ እስከ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን አሳውቋል።
ለተጎጂዎች የመጀመሪያ ሕክምና በአንድ ሆስፒታል እና በ4 ጤና ጣቢያዎች እየተሠጠ ሲሆን፤ ከፍተኛ ጉዳት የደረሠባቸው 5 ተጎጂዎች ለተጨማሪ ሕክምና ወደ አዲስ አበባ ተልከዋል።
ተጎጂዎችን ለማትረፍ ኅብረተሠቡ ጥረት እያደረገ ሲሆን፤ አሁንም ድረስ ከርብራቡ ሥር ያልወጡትን ዜጎች ሕይወት ለማትረፍና ሕክምና እንዲያገኙ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ ነው።
Tikvah-
ቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
ኬንያ ከውጭ ከምታገኘው አጠቃላይ የሃይል አቅርቦት 83 በመቶውን ኢትዮጵያ እንደምታቀርብ ተገለጸ፡፡ በዚህም ኬንያ በዓመት 10 ሚሊየን ዶላር ገደማ ማዳን ችላለች ተብሏል፡፡
ኢትዮጵያ በተያዘው ዓመት እስከ ሰኔ 2025 ድረስ ኬንያ ከውጭ ካስገባችው ጠቅላላ የኤሌክትሪክ ሃይል 83 በመቶውን በመሸፈን ፣ የኬንያ ቀዳሚ የኃይል ምንጭ መሆኗ ተጠቁሟል፡፡
የኬንያው ካፒታል ኤፍ ኤም የአገሪቱን የኢነርጂና ነዳጅ ተቆጣጣሪ ባለሥልጣን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ የኢትዮጵያ የሃይል አቅርቦት ከአገር ውስጥ የኃይል ማመንጫ የበለጠ ወጪ ቆጣቢ ሲሆን፤ ይህም ኬንያ በዓመት 10 ሚሊዮን ዶላር እንድታድን ያስችላታል፡፡
የኬንያው ቢዝነስ ዴይሊ አፍሪካ ጋዜጣ በበኩሉ፤ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት በኬንያ ሊፈጠር የሚችለውን የኃይል ቀውስ በመከላከል ረገድ ወሳኝ ነው ሲል ገልፆታል፡፡
“ኢትዮጵያ ኬንያን ከመብራት መጥፋትና ከፈረቃ ታድጋለች” ሲልም ጋዜጣው ዘግቧል፡፡
AS-
ቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
ህወሓት የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ዋስትና ሰጪ የሆኑት አሜሪካ፣ አውሮፓ ኅብረት፣ አፍሪካ ኅብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የገቡትን ቃል ተግባራዊ ሳያደርጉ ቀርተዋል ሲል ከሰሰ።
ፓርቲው ስምምነቱ ከተፈረመ ከሦስት ዓመታት በኋላም ቢሆን፣ በትግራይ ክልል “በዝምታ ውስጥ እየተፈጸመ ያለ ዘር ማጥፋት ቀጥሏል” ሲልም ገልጿል።
ህወሓት መስከረም 19 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፣ በክልሉ እየተፈጸመ ያለውን ውድመት ለማስቆም ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጣልቃ እንዲገባ አሳስቧል። አክሎም፣ “ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አሁን እርምጃ እንዲወስድ እንጠይቃለን። የትግራይ ውድመት በዝምታ እንዲቀጥል አትፍቀዱ። ለሰላም የገባችሁትን ቃል አክብሩ፣ ንጹሐንን ጠብቁ፣ እናም ሌላ አሳዛኝ ክስተት እንዳይከሰት ተከላከሉ” ብሏል።
ፓርቲው፣ ተፈናቃዮች ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱና የተያዙ ቦታዎች እንዲለቀቁ ለማስቻል በህዳር 2022 የተፈረመው የፕሪቶሪያው ስምምነት በአብዛኛው ሳይተገበር ቀርቷል ብሏል። መግለጫው፣ “አብዛኞቹ ድንጋጌዎች ተፈጻሚ አልተደረጉም፤ተፈናቃዮች ሳይመለሱ ቀርተዋል፣ የተያዙ ቦታዎችም አልተለቀቁም። አደጋው እየከፋ ሄዶ በዝምታ ውስጥ እየተፈጸመ ያለ ዘር ማጥፋት ቀጥሏል” ሲል አክሏል።
በተጨማሪም ፓርቲው፣ ዋስትና ሰጪዎቹ ኃላፊነታቸውን መወጣት አለመቻላቸውንም በማውገዝ፤ “የፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ እንዲተገበር፣ ኃይሎች ከያዙት ቦታዎች አስቸኳይ ለቀው እንዲወጡና ተፈናቃዮች በሰላም እንዲመለሱ” ጠይቋል።
አስ-
ቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
May be an image of text
 
 
 
 
Page 5 of 790