Administrator

Administrator

     በአብዛኛው ፓርቲዎች ለብቻቸው አየር ላይ የተንጠለጠሉ ናቸው፡፡ ከዜጎች ተጨባጭ ችግር ተነስተው መፍትሄ ለመፈለግ የመጡ አይደሉም፡፡ መሰረት የሌለው አመለካከታቸውን ዜጎች ላይ የሚጭኑ ናቸው፡፡ ለመመረጥ ብቻ ብሎ የፖለቲካ አስተሳሰብን ከህዝብ ቃርሞ መሄድ ትክክል አይደለም፡፡ እኔ ብመረጥ፤ በምን አገባኝ ስሜት መያዛችን፣ ምን ዋጋ አለው በሚል ተስፋ ቆራጭነት ቁጭ ማለታችን እንዲያበቃ የበኩሌን ድርሻ ለመወጣት እፈልጋለሁ፡፡”
(ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሣ፤ ለፓርላማ የግል ዕጩ ተወዳዳሪ በነበሩ ወቅት ለአዲስ አድማስ ጋዜጣ ከሰጡት ቃለ - ምልልስ የተወሰደ፤
የካቲት 11 ቀን 1992 ዓ.ም)

“አዲስ አበባ መስተዳድር ካለ ቅድመ ዝግጅትና ካለ ውይይት ድንገት በነዋሪው ላይ የሚጭናቸው ህጎችና ሌሎች መሰናክሎች የንግድ እንቅስቃሴውን አዳክመዋል፡፡ መስተዳደሩ በሩን ለውይይት ዘግቶ ለእርምት እድል ነፍጓል፡፡
መስተዳደሩ ራሱን ከነዋሪው አርቋል፡፡ ለማገልገል ሳይሆን በነዋሪው ለመገልገል የፈለገ ይመስላል፡፡”
የቀድሞ የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት (አቶ ክቡር ገና፤ ምክር ቤቱ ባዘጋጀው “ምረጥ አዲስ አበባ” ዘመቻ ላይ  ከተናገሩት የተወሰደ፡፡
አዲስ አድማስ የካቲት 4 ቀን 1992 ዓ.ም)

“ከረጅም አመታት በኋላ ከሚወደኝ የሀገሬ ህዝብ ጋር ለመቀላቀል በመቻሌ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፡፡ ከዚህ የሙዚቃ ትርኢት የሚገኘው ገቢም በድርቅ ለተጎዱ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ የሚውል ይሆናል፡፡
ልዩ ፍቅር ከሚያሳየኝ የኢትዮጵያ ህዝብ ጎን ሆኜ በድርቅ ለተጎዱት ወገኖቼ መርጃ እንዲሆን ማናቸውንም የኪነ ጥበብ ሀብቴን ብሰጥ ለእኔ መታደል ነው፡፡ ዋስትናችንና ኃይላችን የኢትዮጵያ ህዝብ ፍቅር መሆኑን ከልብ አምናለሁ፡፡”
(አስቴር አወቀ፤ ጥር 27 ቀን 1992 ዓ.ም በአገሯ የመጀመሪያ ኮንሰርቷን ስታቀርብ
ለአዲስ አድማስ ከላከችው መልዕክት የተወሰደ)

“አሁን በስራ ላይ ያሉትን ህጎች የሚመለከቱ መሰረታዊ ጉዳዮች ውስጥ ሳንገባ የህጉ አፈፃፀም ሂደት እንዲቀላጠፍ በማድረጉ ስራ ላይ ብዙ መሻሻል የሚገባቸው ነገሮች አሉ፡፡ እነዚህ ነገሮች ግን አክስዮን ገበያውን ከማቋቋም ሊገቱን አይችሉም፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ከዚህ ቀደም በንጉሰ ነገስቱ ዘመን የአክስዮን ገበያ ነበር፡፡ አሁን ያለው የንግድ ህግም ያኔ የነበረው ነው፡፡ በመሆኑም የአክሲዮን ገበያው ሂደት ሙሉ በሙሉ ህጋዊ ነው፡፡ ህጋዊ እስከሆነ ድረስ በመንግስት በኩል ይኖራል ብለን የምንጠብቀው ጣልቃ ገብነት የለም፡፡ መንግስት በአንዳንድ መልኩ የገበያውን ሂደት የሚያቀላጥፉ ሁኔታዎችን ቢያመቻች ደስ ይለናል፡፡ ይህንንም ያደርጋል ብለን እንጠብቃለን፡፡ ከዚህ ውጪ ከመንግስት ጋር የሚያጋጨን ነገር የሚኖር አይመስለኝም፡፡”
(አቶ ኤርሚያስ አመልጋ፤  የአዲስ አድማስ ጋዜጣ የመጀመሪያ እትም ላይ ስለ አክስዮን ገበያ ታህሳስ 29 ቀን 1992 ዓ.ም ከተናገሩት የተወሰደ)

   በሙያዬ የፅንስና የማህፀን ሀኪም ነኝ፡፡ ለመፅሀፍና ለጋዜጣ ልዩ ፍቅር ስላለኝ ላለፉት በርካታ ዓመታት አያሌ መፅሀፍትን እንዲሁም ጋዜጦችን አንብቤአለሁ፡፡ ጋዜጣ ሳነብ አልመርጥም፡፡ በተለይ አዲስ አድማስን አንብቤ ለአዟሪው መልሼ አላውቅም፡፡ መጀመሪያውኑም አዲስ አድማስን ስገዛ ርዕስ እና የፊት ገፅ አልመለከትም፡፡ መግዛት ግዴታዬ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ፡፡ ገና ብርቱካናማውን የጋዜጣውን ሎጐ ስመለከት የሆነ ደስ የሚል ነገር ይሰማኛል፡
አዲስ አድማስ ባለፉት 15 ዓመታት እጅግ በርካታ ቁም ነገሮችን፣ አስተማሪና አዝናኝ ጉዳዮችን ሲያስኮመኩመን ኖሯል፡፡ “የእኛ ሰው በአሜሪካ”፣ “እንጨዋወት”---የመሳሰሉት አምዶች አይረሱኝም፡፡ መስራቹን አቶ አሰፋ ጐሳዬን ነፍሱን በገነት ያኑራት እላለሁ፡፡ እሱ ካለፈም በኋላ የጋዜጣው ህልውና እንዲቀጥል ያደረጉትን ቤተሰቦቹን ማመስገን እወዳለሁ፡  ጋዜጣው ከመነሻው ጀምሮ ቢታይ፤ በዘርፉ ጥናትና ምርምር ለሚያደርጉ፣ ወደ ጋዜጣ አሳታሚነት ለሚገቡ፣ በጋዜጠኝነት በተለይ በህትመት ሚዲያ ላይ ትምህርት ለሚከታተሉ ሁሉ አይነተኛ ግብአት ነው ባይ ነኝ፡፡
የእኛም ማህበር (ኢሶግ) በጋዜጣው ላይ “ላንቺና ላንተ” የተሰኘ ቋሚ አምድ አለው፡ በዚህ ዓምድ በሚወጣ ፅሁፍ በርካቶችን ማስተማር ተችሏል፡፡ በአገራችን እንደ ልብ ጋዜጣ በማይገኝበትና እንደ ልብ መፃፍ በማይቻልበት ሁኔታ እንኳን አዲስ አድማስ ሁሉን ተቋቁሞ፣ ሁሉን እንዳመሉ ችሎ መረጃ ያቀብለናል፡፡ በውስጡ ደግሞ እንደ ገጣሚና ተርጓሚ ነቢይ መኮንን፣ እንደነ አብደላ ዕዝራ፣ እንደነ ኤፍሬም እንዳለ እና መሰል ሳተና ብዕረኞች አሉት፡፡ ቀድሞም በርካታ ብርቱ ብርቱ ፀሐፊዎች ነበሩ፡ ያን ጊዜም አሁንም ጋዜጣውን አነበዋለሁ፡፡ ወንዱ ልጄ ሶፍትዌር ኢንጂነር ቢሆንም የእኔው ዓመል ተጋብቶበት፣ ቅዳሜ ቅዳሜ አዲስ አድማስን ብብቱ ስር ሸጉጦ መምጣት ከጀመረ ረዘም ያለ ጊዜ ሆኖታል፡፡ ታዲያ እሱ ገዛ ብዬ እኔ መግዛቴን አልተውም፡፡ በዚህ ምክንያት ከመጀመሪያው እትም አንስቶ  የአድማስ ኮፒ አለኝ፡፡
አዲስ አድማስ ጋዜጣን ተውሶ የማይመልስልኝ ጠላቴ ነው፡፡ ለስራ ብዙ ጊዜ ወደተለያዩ የአፍሪካና የአውሮፓ አገራት ስሄድ፣ ደንበኛዬ ጋዜጦቹን በጥንቃቄ ያስቀምጥልኛል፡፡ አሁን አሁን ደግሞ ከአገር ስወጣ ዌብሳይቱ ላይ ማንበብ መቻሌ ያስደስተኛል፡፡ ብቻ… በአዲስ አድማስ ደስተኛ ነኝ፡፡ ከአዲስ አድማስ ቀጥሎ የማንበብ ጥሜን የሚያረካልኝ የነበረውና እንደ ሃምሌ ፀሐይ ብልጭ ብሎ የጠፋው “አዲስ ነገር” የተባለ ጋዜጣ ነበር፡፡ ጋዜጣውም ተዘጋ፤ አዘጋጆቹም ኮበለሉ፡፡
ለዚህ ነው ከላይ እንደ ልብ መናገርና መፃፍ በማይቻልባት ኢትዮጵያ፤ ትችቱንም፣ ትዝብቱንም፣ ወቅታዊ ትኩሳቶችንም አለዝቦ በማቅረብና ማህበረሰቡን በማስተማር ሲተጋ 15 አመት መጓዙ አድማስን ያስመሰግነዋል የምለው፡ አሁንም በርካታ 15 ዓመቶችን ያክብር፡ አዘጋጆቹንም ፀሐፊዎቹንም ኢትዮጵያንም ፈጣሪ ይባርክ፡፡
(ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ)

“አዲስ አድማስ መስዋዕትነት የከፈለ ጋዜጣ ነው”
ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማርያም
(የአለማቀፍ የህግ ባለሙያና ፖለቲከኛ)
     አዲስ አድማስ እንደሌሎቹ ጋዜጦች በፕሬሱ እንቅስቃሴ ውስጥ መስዋዕትነት የከፈለ፣ ለእውነትና ለሃቅ የታገለ ጋዜጣ አድርጌ ነው የማየው፡፡ እርግጥ እንደ ሌሎቹ የመዘጋት እድል አልገጠመውም፡፡ እንደሚታወቀው አሁን በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ ያዘጋጃቸው የነበሩ ጋዜጦች በሙሉ ተዘግተዋል፡፡
አዲስ አድማስ ጋዜጣም ምናልባት አስቸጋሪ በሆነ ሁኔታ ውስጥ በቀጭን ክር እየተራመደ ዘልቋል ብዬ አስባለሁ፡፡
ለወደፊትም እንደሚዘልቅ ተስፋ አደርጋለሁ። እስካሁን ድረስ ለመዝለቁም የአዘጋጆቹ ጥበብና ብልህነት ነው እንጂ አፈና ሳይደርስበት ቀርቶ አይደለም፡፡
ለወደፊትም ቢሆን አሁን በያዘው ጥበበኛ አካሄድ ቢቀጥል መልካም ነው፤ ባልሆነ መንገድ ሄዶ መዘጋቱ ለሀገርም ጉዳት ነው፡፡
በተቻለ መጠን የሚዘጋበት ደረጃ እንዳይደርስ በጥንቃቄና በአስተዋይነት ቢጓዝ የበለጠ አስተዋጽኦ ይኖረዋል፡፡ ይሄኛው ጥሩ መንገድ ይመስለኛል፡፡  


Tuesday, 03 March 2015 14:38

አዲስ አድማስ

የእርግዝናዬን ግዜ ሳስበው እጅግ ይዘገንነኛል፡፡ ልጄ አሁን ሁለተኛ አመቱን ይዞአል፡፡ በባለቤቴም በኩል ይሁን በእኔ በኩል ያሉ ቤተሰቦች አንድ ልጅ መደገም እንዳለበት     ሲነግሩኝ...በሁኔታው ባምንም ...ሳስበው ግን እጅግ ይመረኛል፡፡ ከክብደት ጀምሮ ገጽታዬ በሙሉ እንዲሁም የቆዳ ቀለሜ የእኔ አልነበረም፡፡ ጭራሽ ነበር የተበለሻሸሁት፡፡ እኔነቴ     ተመልሶ ይመጣል የሚል እምነት አልነበረኝም፡፡ አሁን ደግሞ ተመልሼ ባረግዝ ...ልክ አንደበፊቱ ልበላሽ ነው ብዬ በጣም እጨነቃለሁ፡፡ ለመሆኑ ሐኪሞቹ ምን ይላሉ?
ይህን ጥያቄ ያቀረበችው እናት በእድሜዋ ወደ ሀያ አምስት አመት ስትሆን የምትኖረውም በአዲስ አበባ ነው፡፡ ስሙዋ ደግሞ ቆንጂት ብርሀኔ ይባላል፡፡ ዶ/ር ታደሰ ኡርጌ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስት በዚህ ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በእርግዝና ወቅት በእያንዳንዱ የእናቶች የሰውነት ክፍል የሚከሰቱ ለውጦች ይኖራሉ፡፡ የሰውነት anatomic የምንለው ለውጥ ብቻ ሳይሆን በውስጣቸው የሚሰሩት ነገሮች በሙሉ የሚለወጡበት ሁኔታ ነው የሚኖረው፡፡ ይህም physiologic changes of pregnancy  ወይንም ከእርግዝናጋር በተያየዘ የሚከሰት ጤናማ የሆነ ለውጥ ማለት ነው፡፡ ይህ ለውጥ እንግዲህ በተለያዩ ሴቶች ላይ የሚኖረው ሁኔታ ይለያይ እንጂ ሁሉም ሴቶች ላይ የማይቀር ለውጥ ነው፡፡ በእያንዳንዱ የሰውነታችን ስርአት ውስጥ የተለያዩ ለውጦች ይካሄዳሉ፡፡ በዚህ ወቅት የሚታዩት አካላዊ ለውጦች በዋናነት ከኪሎ መጨመር ጋር ተያይዘው የሚመጡ ለውጦች ናቸው፡፡  ክብደት ሲጨምር የትኞቹ ክፍሎች ናቸው የሚለወጡት ያልን እንደሆን ሰውነት ውስጥ ከሚከማቸው ፈሳሽ ጀምሮ የሚወፍሩ አካላት ይኖራሉ፡፡ ልጅ እና የእንግዴ ልጅ ሌላውን ክፍል ይይዛል፡፡ የማህፀን እድገት የራሱን የሆነ ክፍል ይይዛል፣ የሽርት ውሀ የራሱ አስተዋፅኦ ይኖረዋል፡፡ ሌሎች ሰውነት ውስጥ የሚከማቹ  ስብን ጨምሮ የሰውነት ቅርፅ ለውጥ እንዲመጣ የሚያደርጉ ናቸው፡፡ እነኚህ ለውጦች ከምን የተነሳ ነው የሚመጡት ብለን ያየን እንደሆነ በዋናነት በእርግዝና ወቅት የሚቀየሩት ወይንም የእናቶች ሰውነት ውስጥ የሚመነጨው የሆርሞን መጠን ነው፡፡ ይህ የሆርሞን መጠን መጀመሪያ እርግዝናው እንደተከሰተ የዘር ፍሬ ከሚመረትበት ወይንም እንቁላሏ ከወጣችበት ቦታ የሚቀረው ክፍል Corpus luteum  ከምንለው የሚወጣው ነው የመጀመሪያው የሆርሞን ለውጥ፡፡ በመቀጠልም የእንግዴ ልጅ የሚያመነጨው እጅግ በጣም ብዙ የሆነ የሆርሞን መጠን ይኖራል፡፡ እነኚህ ሆርሞኖች በእርግዝና ወቅት ለሚከሰቱ ለውጦች ወይንም physiologic changes of pregnancy
ለምንለው ምንጭ ናቸው፡፡ ሰውነት ውስጥ ፈሳሽ እንዲከማች፣ ስብ እንዲከማች፣ ልጅ እንዲያድግ የጠቀስኳቸው አካላት በሙሉ እድገት እንዲያሳዩ የሚያደርጉት እነኚህ ሆርሞኖች ናቸው፡፡ ስለዚህ የለውጡ ምንጭ ከእርግዝናው ጋር የተያያዘ ነው፡፡
ከክብደት መጨመር በተጨማሪም ቆዳ ላይ የሚከሰቱ ለውጦች ይኖራሉ፡፡ ፊት ላይ፣ በእናቶች ሆድ ላይ፣ በጡት ላይ፣ የቆዳ (መልክ) መቀየር አይነት ሁኔታዎች ሊኖሩ ይችላሉ እና በተለያየ ቦታ በቆዳ ላይ የሚከሰቱ ለውጦች ይኖራሉ፡፡ እነኚህ  በቆዳ ላይ የሚታዩት ለውጦችም ቢሆኑ ከሆርሞኖች የተነሳ የሚመጡ ናቸው፡፡ አንዳንዶቹ እናቶች በሁለቱም ጎናቸው ላይ የመጥቆር አይነት ሁኔታ ይኖራል፡፡ mealasma ወይንም colasma  ወይንም mask of pregnancy የሚሉት ነገር ነው፡፡ ይህም ኢስትሮጂን የሚባለው ሆርሞን ሰውነት ውስጥ ከመብዛቱ የተነሳ ቆዳ ላይ የሚከሰተው ለውጥ ነው ማለት ነው፡፡ የእናቶችን ሆድ ደግሞ ያየን እንደሆነ መሀል ላይ የመጥቆር ሁኔታ ይኖራል፡፡ ይህም ከዛ ጋር የተያያዘ ነው  linea nigra  ነው የምንለው፡፡ ሌሎች ደግሞ ሸንተረሮች ይኖራሉ ሆድ፣ ጡት፣ እግር አካባቢ፣ እነኚህም ምንድነው በዋናነት የእነዚህ ሆርሞኖች መኖርና ሰውነት ክብደት እየጨመረ ሲሄድ ስብ እየተከማቸ ሲሄድ ወይንም ፈሳሽ እየተከማቸ ሲሄድ የመለጠጥና ከስር ያለው ቆዳ ወይም dermis የምንለው ቆዳ መሰነጣጠቅ ከዛም የመዳን ሁኔታዎች ናቸው እነኚህን ለውጦች የሚፈጥሩት ማለት ነው፡፡
አንዳንድ ግዜ ጤናማ ባልሆነ ሁኔታ ፈሳሽ ሰውነት ውስጥ የሚከማችበት ወይንም ከቆዳ ስር የሚከማችበት edema የምንለው ነገር ማለት ነው በብዛት የሚከማችበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል፡፡ ይህ ጤነኛ ባልሆነ ሁኔታ ብዙዎቹ እናቶች ከሰማኒያ % በላይ የሚሆኑት ላይ edema የምንለው ነገር ሊኖር ይችላል፡፡ ግን በጣም ከልክ ያለፈ አይደለም፡፡ ከልክ ያለፈ የሚሆነው ጤነኛ ባላሆነ ሁኔታ በአንዳንድ ከእርግዝና ጋር ሊመጡ በሚችሉ ችግሮች ለምሳሌ በደም ግፊት የተነሳ በጣም ብዙ ፈሳሽ ከቆዳ ስር ሊከማች ይችላል፣ ሆዳቸው ላይም ሊከማች ይችላል፣ እግራቸው ላይ ሊሆን ይችላል፣ እጃቸው ሊያብጥ ይችላል፣ ፊታቸው ሊያብጥ ይችላል፡፡ እነኚህ ጤነኛ ባልሆነ ሁኔታ የተከሰቱ ሁኔታዎች ናቸው ፡፡ ግን normally ጤነኛም ሆኖ የአንዱ ክብደት መጨመርና የሰውነት ቅርፅ መለዋወጥ ዋናው ምክንያት የዚህ የፈሳሽ መጠራቀምና የስብ ሰውነት ውስጥ መከማቸት ሁኔታዎች ናቸው፡፡ እንግዲህ እነኚህ ሰውነት ውስጥ ከእንግዴ ልጅ በብዛት በሚመነጩ ቅመሞች ወይንም ሆርሞኖች የተነሳ የሚከሰቱ ናቸው ማለት ነው፡፡
ጥ/ በእርግዝና ግዜ የሚወሰድ ቫይታሚን ለክብደት መጨመርና ለቆዳ መበለሻሸት ምክንያት ይሆናልን?
መ/ እንግዲህ በአጠቃላይ በእርግዝና ወቅት የእናቶችን አመጋገብ ወይንም የምግብ ሁኔታ ያየን እንደሆን በተመጣጠነ ሁኔታ እናቶች ምግብ ማግኘት አለባቸው፡፡ ምግብ ስንል በዋናነት macronutrient  እና micronutrient  ብለን ነው የምንከፍላቸው፡፡ macronutrient
በዋናነት የምንመገባቸው ለሰውነት ግንባታና ለሀይል የሚያገለግሉ ምግቦች ናቸው፡፡ ይህ እንግዲህ ካርቦሀይድሬት፣ ፋት እና ፕሮቲን እያልን የምንጠራቸው ዋናዎቹ ምግቦች ናቸው ማለት ነው፡፡ ከዛ በተጨማሪ  micronutrient  የምንላቸው ቫይታሚንና ሚንራሎች ለሰውነት አስፈላጊ የሆኑ ንጥረ ነገሮች ናቸው፡፡ እነኚህ በዋናነት ጉልበት የመስጠትና ሰውነት መገንባት ቀጥተኛ የሆነ ተሳትፎ ባይኖራቸውም ሰውነት ውስጥ የሚካሄዱት የተለያዩ አይነት ሂደቶች በእነኚህ ሚንራሎችና ቫይታሚኖች በመታገዝ ነው፡፡ እነኚህ ለእናቲቱ ብቻ ሳይሆን እያደገ ላለው ፅንስ የሁለቱም የmacronutrient  እና  micronutrient  ምግቦች ምንጭ እናቲቱ ጋር ሲኖር ነው ወደ ልጁ ሊሄድ የሚችለው ማለት ነው፡፡ ስለዚህ የተመጣጠነ ምግብ የሚመገቡ እናቶች እነኚህ አስፈላጊ የሆኑት ንጥረ ነገሮች ከምግብ ውስጥ በቀን የሚያስፈልገውን ያክል ያገኛሉ ተብሎ ይታሰባል፡፡ ግን በቀን የሚያስፈልገውን ቫይታሚንና ፕሮቲን የምንላቸውን ንጥረ ነገሮች ከምግብ ውስጥ ብቻ የማይገኝባቸው ወይንም በቂ የማይሆኑበት ሁኔታዎች አሉ፡፡ አንዱ ምንድነው ምግባችን እነዛን ሚንራሎች ወይንም ቫይታሚኖች በበቂ ሁኔታ ያልያዘ ሊሆን ይችላል፡፡ ቢይዝም እንኳን በእርግዝና ወቅት የበለጠ  እነዚህን ቫይታሚንና ሚንራል አይረንና ፎሊክ የምንላቸው ነገሮች አስፈላጊ ይሆናሉ፡፡ ስለዚህ እነኚህ አስፈላጊ ንጥረ ነገሮች ናቸው እንጂ ከሚፈጠሩት የሰውነት ለውጦች ጋር በምንም መንገድ የማይገናኙ ናቸው፡፡ ቫይታሚኖቹና ሚንራሎቹ በእርግዝና ወቅት አስፈላጊ የሆኑ ንጥረ ነገሮች ናቸው፡፡ አንዲት እናት በትክክል ማግኘት የሚገባት ንጥረነገር ነው፡፡
    በእርግዝና ወቅት ያለው የአመጋገብ ሁኔታን በተመለከተ አንዲት እናት እርጉዝ ካልሆነችው እናት የበለጠ ምግብ መመገብ አለባት፡፡ በእርግዝና ወቅት የሰውነቷ የካሎሪ ፍላጎት ይጨምራል፡፡ ይህ የሚሆነው ለምንድነው? አንዱ ለሰውነት ግንባታ ነው፣ ሁለተኛ ፅንሱ ጤናማ ሆኖ ለማደግ የሚያስፈልጉ ንጥረ ነገሮች የሚገኙት ከእናቲቱ በመሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ metabolic rate  የምንለው ነገር በእግዝና ወቅት ይጨምራል፡፡ ስለዚህ በእርግዝና ወቅት አንዲት እናት ቀድሞ ከምትመገበው የበለጠ መመገብ አለባት፡፡ የሰውነቷም ፍላጎት እያደገ ያለውም ፅንስ ይህንን ነው የሚፈልገው፡፡ ስለዚህ በምግብ ደረጃ ያየን እንደሆነ አንዲት እናት በእርግዝናዋ ወቅት ቢያንስ አንድ ተጨማሪ ምግብ መመገብ አለባት ተብሎ ነው የሚታሰበው፡፡ ይህ እንግዲህ ምንድነው አንዲት እናት በእርግዝናዋ ወቅት ወደ 300/ ኪሎ ካሎሪ ተጨማሪ ምግብ ትፈልጋለች ማለት ነው፡፡ ስለዚህ የምግብ ፍላጎት መጨመሩ የመጀመሪያዎቹን ሶስት ወራት ይሄ የማቅለሽለሹ፣ የማስመለሱና ምግብ የማስጠላቱ ነገር ከመኖሩ በስተቀር በተለይ ሁለተኛው ግማሽ የእርግዝና ወቅት እነኝህ ፍላጎቶች እየጨመሩ የሚሄዱበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ ስለዚህ ይሄ ጤናማ የሆነው በእርግዝና ወቅት የሚኖረው የምግብም ሆነ የካሎሪ ወይንም የጉልበት መጠን ፍላጎት የሚጨምርበት ወቅት ነው ማለት ነው፡፡ ይህ በእርግዝና ወቅት ሲሆን የምታጠባ እናት ደግሞ የምትፈልገው የምግብ ወይንም የጉልበት ወይንም የካሎሪ መጠን ከእርጉዝ ሴት በተሻለ ነው፡፡ ይህም አንዲት የምታጠባ እናት ወደ 500/ ኪሎ ካሎሪ ተጨማሪ ምግብ የምትፈለፍግበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ ስለዚህ ይህ በምግብ ሲሰላ ድሮ ከምትመገበው ሁለት ተጨማሪ ምግብ መመገብ አለባት፡፡ ስለዚህ ይሄ ለውጥ ከቫይታሚኖቹ የተነሳ አይደለም፡፡ በእርግጥ ቫይታሚኖች ሰውነታችን ውስጥ እያንዳንዱን metabolism የምንለውን ነገር የማመቻቸት ወይም facilitate የማድረግ ጠቀሜታ ነው ያላቸው፡፡
እያንዳንዱ ሰው የሚያመጣው ለውጥ ሊለያይ ይችላል፡፡ ግን በሰውነት ውስጥ የሚፈጠሩት ሆርሞኖች ለእነኚህ ልዩነቶች ወይም ለእነኚህ ለውጦች ዋናዎቹ ምክንያቶች ናቸው፡፡ ለምን አንዳንድ እርጉዝ ሴቶች ይህን ቀለም ያዙ? ለምን ሌሎቹ ይህን አልያዙም? ለሚለው ይህ በተለያዩ ምክንያቶች ሊሆን ይችላል፡፡ ለምሳሌ በአንፃራዊነት የእነኚህ ሆርሞኖች መጠን ምን ያክል ነው? በተጓዳኝ በእርግዝና ወቅት የሚመነጩ ሌሎች ነገሮች ይኖራሉ ወይ? አንዲት እናት ቆዳዋ ለፀሀይ ብርሀን ያለው sensitivity  ምን ያህል ነው? የሚሉት ነገሮች ይኖራሉ፡፡ melanosite  የምንላቸው ወይም የቆዳ ቀለምን ሊያመነጩ የሚችሉ ህዋሶች ምላሻቸው ምንድነው? ይህ በተለያዩ ምክንያቶች ሊለያይ ይችላል፡፡ ለምሳሌ እንዳንድ እናቶች ፊታቸው ላይ የመጥቆር ሁኔታ ይኖራል አንዳንዶቹ ምንም አይነት ለውጥ አይኖራቸውም፡፡ በእርግዝና ብቻም ሳይሆን አንዳንድ የወሊድ መቆጣጠሪያ መድኒት የሚወስዱ እናቶች ፊታቸው ላይ የመጥቆር ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል ፡፡ አንዳንዶቹ ላይ ምንም ላይፈጠር ይችላል፡፡ ይህ የሚያሳየው በዋናነት ሆርሞኖቹ ተፅእኖ ቢኖራቸውም ሆርሞኖቹ ብቻቸውን ሳይሆን ሌሎች ተጓዳኝ ወይም ያንን ነገር ሊገልፁ የሚችሉ ከ genetic ከመሳሰሉት environmental factors
ሊሆን ይችላል፡፡ የለውጦቹ ዋና ምንጮች ሆርሞኖቹ ቢሆኑም ለውጡ ግን እንደየ ሰዉ ሊለያይ ይችላል፡፡




በሀገራችን ያለው የሙያ ማህበራት ቁጥር ከጊዜ ወደ ግዜ እየጨመረ መጥቷል፡፡ እነዚህ የሙያ ማህበራት ከአባላቱ ባሻገር ለሙያ ዘርፉ ብሎም ለሀገር እድገት የሚጫወቱት ሚና እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡ በህክምናው ዘርፍ ከተቋቋሙ የሙያ ማህበራት መካከል የኢትዮፕያ ፅንስና ማህፀን ሀኪሞች ማህበር አንዱ ነው፡፡ ማህበሩ ባለፈው ሳምንት ሀያ ሶስተኛ መደበኛ ጉባኤውን ደረጃውን የጠበቀ የማህፀንና ፅንስ ህክምና ስልጠናን ማሳደግ በሚል መሪ ቃል በጅማ ዩንቨርሲቲ አካሂዷል፡፡
ዶክተር ደረጄ ንጉሴ የማህበሩ ፕሬዝዳንት ናቸው። የዚህ አመት ጉባኤ ደረጃውን የጠበቀ የማህፀንና ፅንስ ህክምና ስልጠናን ማሳደግ የሚለው መሪ ቃል የተመረጠበትን ምክንያት ሲናገሩ፡-
“የዚህን አመት ጉባኤ ደረጃውን የጠበቀ የማህፀንና ፅንስ ህክምና ስልጠናን ማሳደግ በሚል አካሂደናል። ይህን መሪ ቃል የመረጥንበት ዋናው ምክንያት የያዝነው አመትየምእተ አመቱ     የልማትግቦች ማብቂያ እንደመሆኑ በጤናውም ዘርፍ እየተሰራ ያለውን ስራ ለማስቀጠል የባለሙያውን አቅም መገንባት አስፈላጊ ነው ብለን ስለምናምን ነው፡፡
የምእተአመቱ ግብ ከተጠናቀቀ በኋላ የሚኖረው የጤና አገልግሎት በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄድ ደረጃቸውን     የጠበቁ ባለሙያዎች ማፍራት አስፈላጊ ስለሆነ ከዚህ ጋር በተያያዘ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ምክክር ለማድረግ ይህን መሪ ቃል መርጠን የዚህን አመት ስብሰባ አካሂደናል ነው፡፡
ለሶስት ቀናት በተካሄደው ጉባኤ ላይ አስራ ሁለት ያህል ጥናታዊ ፀሁፎች የቀረቡ ሲሆን ፅሁፎቹ በተለያዩ የስነተዋልዶ ጤና ችግሮች እንዲሁም ከማህፀንና ፅንስ ጋር ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በገራችን ያለውን ሁኔታ መሰረት በማድረግ የተሰሩ ናቸው፡፡ እያንዳንዱ ፅሁፎች ከቀረቡ በኋላም አባላቱና ለሌሎች የስብሰባው ተሳታፊዎች ተወያይተውበታል፡፡   
በጉባኤው ላይ የክብር እንግዳ ነበሩት በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የሰው ሀብት ልማት አስተዳደር ዳይሪክተር የሆኑት ዶክተር ወንድምአገኝ እምቢ አለ፣፣ ‘’Ministry of  Health’s plans and issues in light of scaling up quality Obstetrics and Gynecology training’’ በሚል እርእስ ደረጃውን የጠበቀ የማህፀንና ፅንስ ህክምና ስልጠናን ለማሳደግ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በኩል የተያዘውን እቅድ ለተሰብሳቢዎች አቅርበዋል፡፡
ማህበሩ ከጤና ጥበቃ ጋር በመተባበር በእናቶች ጤና ላይ በተለይ በእርግዝናና በወሊድ ግዜ የሚከሰትን የእናቶች ሞት ለመቀነስ በትብብር እየሰራ እንደሆነና እንዲህ አይነት የሙያ ማህበራት በጤናው ዘርፍ የሚጫወቱት ሚና እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከማህበሩ ጋር ያለውን ግንኙነት ከምንግዜውም በላይ አጠንክሮ እንደሚሰራ ዶ/ር ወንድማገኝ ገልፀዋል። ከጽንስና ማህጠን ሐኪሞች ማህር ጋር ባለው የስራ ግንኙነትም የሚከተሰለውን ተናግረዋል።
“የኢትዮጵያ ፅንስና ማህፀን ሀኪሞች ማህበር ከተመሰረተበት ከፈረንጆቹ 1992/ አመተ ምህረት ጀምሮ የእናቶችና ህፃናትን ሞት ለመቀነስ እየሰራ ያለ ማህበር ነው፡፡ ከጤና ጥበቃም ጋር በመተባበር የሚሰራቸው የተለያዩ ትልልቅ ፕሮጀክቶች አሉ፡፡ በቅርቡም የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በጤናው ዘርፍ ከእርግዝናና ከወሊድ ጋር በተያያዘ ለእናቶች ሞት ትልቅ ምክንያት የሆነውን የክህሎት ችግር ለመቅረፍ የድንገተኛ የፅንስ ህክምና ባለሙያዎችን እያሰለጠንን ነው፡፡ ይህን ስልጠና ከጀመርን አምስት አመት ቢሆንም በበቂ ሁኔታ እየተተገበረ አይደለም። ስለዚህ ይህን ስልጠና በሀገር አቀፍ ደረጃ ተደራሽ ለማድረግ ከእነዚህ ባለሙያዎች ጋር በትትብር እየሰራን ነው፡፡”



የያዝነው የፈረንጆቹ 2015 የምእተ አመቱ የልማት ግቦች ወይም millennium development goals ማብቂያ አመት እንደ መሆኑ በጤናው ዘርፍ እስከአሁን የታዩት እመርታዎች ምን ይመስላሉ ተብሎ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ ዶ/ር ወንድማገኝ ምላሽ ሲሰጡም፡-
የምእተ አመቱን የልማት ግቦችን በማሳካት እረገድ የጤናው ዘርፍ ትልቅ እመርታ አሳይቷል ማለት ያቻላል። የዛሬ ሁለት አመት የህፃናትን ሞት በመቀነስ ኢትዮጵያ በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ተሰጥቷታል፡፡ የእናቶችን ሞት በተመለከተም ለውጡ በጣም ትልቅ ነው፡፡ ሆኖም ግን አሁንም እየተሰሩ ያሉ ስራዎች አሉ፡፡ ለምሳሌ ለእናቶች ሞት ትልቁ ምክንያት የሆነው የግንዛቤ እጥረት ነው፡፡ ይህንን በተመለከተ የጤና አገልግሎቱ ተጠናክሮ እያንዳንዷ እናት አገልግሎቱን ፈላጊ እንድትሆንና በጤና ተቋም እንድትወልድ ማድረግ በጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች እየተሰራ ያለ ስራ ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ከዛሬ አምስት አመት በፊት 6% የነበረው በጤና ተቋም የሚወልዱ እናቶች ቁጥር አሁን ወደ 20% አድጓል፡፡ ስለዚህ በበቂ ሁኔታም ባይሆን የምእተ አመቱን ግብ ማሳካት ችለናል።” ብለዋል፡፡ በጉባኤው ከነበሩ ክንውኖች መካከል የደም ልገሳ ፕሮግራም አንዱ ነበር፡፡ የስብሰባው ተሳታፊዎች በበጎፈቃደኝነት ደም ለግሰዋል፡፡ የደም ልገሳ ፕሮግራሙ ባለሙያዎቹ ከህክምና ስራቸው በተጓዳኝ ለህብረተሱ አለኝታ መሆናቸውን ለማሳየት ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነ የማህበሩ ፕሬዝዳንት ዶክተር ደረጀ ይገልፃሉ፡፡
“ይህ የደም ልገሳ ፕሮግራም የተዘጋጀው ባለሙያዎች ከህክምና ስራው ባሻግር ለህብረተሰቡ አለኝታ መሆናቸውን ለማሳየት ሲባል ነው፡፡ ህብረተሰቡም ይህንን በማየት የደምን አስፈላጊነት ተረድቶ ህይወትን ለማዳን ሲባል ደም መስጠት እንዳለበት ለማስተማር ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡”
ዶክተር ሙኸዲን አብዶ የማህፀንና ፅንስ ሀክምና እስፔሻሊስትና የማህበሩ የቦርድ አባል ናቸው፡፡ የህክምና ባለሙያዎች በእንዲህ አይነቱ የደም ልገሳ ፕሮችራሞች ላይ መሳተፋቸው ለሌላው የህብረተሰብ ክፍል የሚሰጠው የተለየ ትርጉም እንዳለ ይገልፃሉ?፡፡
“ባለሙያ እንደዚህ አይነት የደም ልገሳ ፕሮግራም ላይ መሳተፍ ተገቢ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ ምክንያቱም ከእኛ ከባለሙያዎች የበለጠ የደም እጦት የሚያደርሰውን ጉዳት የሚያውቅ የለም፡፡ ለእናቶች ሞት ምክንያት ከሆኑት ነገሮች መካከል የደም መፈሰስ ትልቁን ድርሻ ይይዛል፡፡ ስለዚህ በተለይ እንደኛ የማህፀንና ፅንስ ህክምና ላይ ያሉ ባለሙያዎች በደም መፍሰስ ምክንያት የሚሞቱ እናቶችን ቁጥር ለመቀነስ ደም መለገስ ከምንም በላይ አስደሳችና ሊዘወተር የሚገባው ነው፡፡”
በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የማህፀንና ፅንስ ሀኪም የሆኑት ዶክተር ባላካቸው ንጋቱም የዶክተር ሙኸዲንን ሀሳብ ይጋራሉ፡፡“እንደሚታወቀው የማህፀንና ፅንስ ሀኪሞች በአብዛኛው ከደም ጋር የተያያዘ ስራ ላይ ነው ያለነው። እናቶች በተለያየ ምክንያት ደም ይፈሳቸዋል ለዚህም ከየደም ባንኩ ብዙ ደም እንጠይቃለን፡፡ የምንጠይቀውን ደም እራሳችንም በተወሰነ መልኩ አስተዋፅኦ ማድረግ እንዳለብን ሁልግዜም አስብ ነበር፡፡ ስለዚህ ዛሬ እድሉን አግኝቼ ደም በመስጠቴ እጅግ ደስተኛ ነኝ፡፡ ከምንሰጠው የህክምና አገልግሎች በተጨማሪም ማህበራዊ ግዴታችን ነው ብዬ አስባለሁ ተምሳሌትነቱም ለማህበራችን አባላት ብቻ ሳይሆን ሌላውም የህብረተሰብ ክፍል ነው፡፡”


12ኛው የአፍሪካ ወጣቶች አትሌቲክስ ሻምፒዮና  በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት  በሚቀጥለው ሳምንት ይጀመራል፡፡ ሻምፒዮናውን በብቃት ለማካሄድ አንጋፋው የአዲስ አበባ ስታድዬም በ5 ሚሊዮን ብር  ወጭ ሙሉ እድሳት ተደርጎለታል፡፡ እድሳቱ የስታዲየሙ አጥር፣ የመጸዳጃ ቤቶች ማስፋፋት፣ የመብራት፣ የተመልካቾች መቀመጫዎች፣ የትንሿን ስታዲየም የአስፓልት ንጣፍ፣ የፖውዛ መብራቶች ያካተተ ነው፡፡ ኢትዮጵያ አህጉራዊ የአትሌቲክስ ሻምፒዮናውን በማስተናገድ ወደፊት ትልልቅ ውድድሮችን የማዘጋጀት ፍላጎቷን ታነቃቃለች፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ፅሕፈት ቤት በሚመራ ብሔራዊ ኮሚቴ እና 12 ንዑሳን ኮሚቴዎችን በማንቀሳቀስ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል፡፡ የአዲስ አበባ ስታድዬም ሙሉ እድሳትና ለውድድሩ አጠቃላይ መስተንግዶ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ  ለበጀት እንደተመደበም ታውቋል፡፡
በሻምፒዮናው ላይ ለመሳተፍ  33 የአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌደሬሽን አባል አገራት ማረጋገጫ ልከዋል፤ 618 የአፍሪካ ወጣት አትሌቶች በሜዳ እና በትራክ ላይ በሚካሄዱ 40 የስፖርት ውድድሮች ይሳተፋሉ፡፡ በመካከለኛ እና የረጅም ርቀት ውድድሮች የምስራቅ አፍሪካ አትሌቶች በተለይ የኢትዮጵያ እና የኬንያ በፍፁም የበላይነት ፉክክር እንደሚገቡ  ሲጠበቅ፤ የምእራብ አፍሪካ አገራት አትሌቶች በአጭር ርቀት ውድድሮች እንዲሁም ደቡብ አፍሪካ እና ግብፅ በሜዳ ላይ ስፖርቶች ብልጫ እንደሚኖራቸው በመገለፅ ላይ ነው፡፡ በ12ኛው የአፍሪካ ወጣቶች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ለመሳተፍ ኢትዮጵያ 100፣ ናይጀሪያ 97 ፣ ሴራሊዮን 37፣ ሞሮኮ 35፣ ሱዳን 33፣ዚምባቡዌ 31፣ ካሜሮን 28፣ ቱኒዚያ 26፣ ቡርኪናፋሶ 23፣ ኮንጎ ብራዛቢል 19፣ ኡጋንዳ 19፣ ሴኔጋል 16፣ዛምቢያ 14፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ 13፣ ሩዋንዳ 7 ፣ ሲሼልስ 17፣አንጎላ 14  ፣ሶማሊያ 13፣ ኬንያ 12፣ ማሊ 11፣ ማዳጋስካር 8፣ አልጀሪያ 8፣ናምቢያ 8 ፣  ጋቦን 6 ግብፅ 6፣  ሌሴቶ 5፣፣ኮትዲቯር 5፣  ኬቬርዴ አይስላንድ 3፣ ፣ ስዋዚላንድ 3 እና  ጊኒ ቢሳው 1፣  ስፖርተኞችን አስመዝግበዋል፡፡
ከሁለት ዓመት በፊት ሞሪሽዬስ፤ ባምቦስ በተባለች ከተማዋ ባስተናገደችው 11ኛው የአፍሪካ ወጣቶች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ከ29 አገራት የተውጣጡ 223 አትሌቶች በ40 የስፖርት ውድድሮች ተሳትፈው ነበር፡፡  15 አገራትአንድና ከዚያም በላይ ሜዳልያ በማግኘት የደረጃ ሰንጠረዥ ውስጥ ገብተው 119  ሜዳልያዎችን ሰብስበዋል፡፡ ናይጄርያ በ19 ሜዳልያዎች (9 የወርቅ፤ 7 የብርና 3 የነሐስ) አንደኛ ደረጃ ነበራት፡፡ ደቡብ አፍሪካ በ24 ሜዳልያዎች  (7 የወርቅ፤ 9 የብርና 8 የነሐስ) ሁለተኛ ደረጃ ስትወስድ 41 አትሌቶችን አሳትፋ የነበረችው ኢትዮጵያ በ22 ሜዳልያዎች (7 የወርቅ፤ 7 የብርና 8 የነሐስ) ሶስተኛ ደረጃ አግኝታ ነበር፡፡ ግብፅ በ11 ሜዳልያዎች (5 የወርቅ፤ 4 የብርና 2 የነሐስ)፤ ኬንያ በ17 ሜዳልያዎች፤(4 የወርቅ፤ 9 የብርና 4 የነሐስ) እንዲሁም ኡጋንዳ በ4 ሜዳልያዎች (2 የወርቅ፤ 1 የብርና 1 የነሐስ) እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ አከታትለው ወስደዋል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት በ11ኛው የአፍሪካ ወጣቶች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ካገኘቻቸው 7 የወርቅ ሜዳልያዎች 6 ስድስቱን ያስመዘገቡት ሴቶች ሲሆን በወንዶች የተገኘው 1 የወርቅ ሜዳልያ ብቻ ነበር፡፡ እነሱም በ800 ሜትር ወንዶች በረከት ካህሳይ አዳነ፤ በ800 ሜትር ሴቶች አለም ገብረእግዚአብሄር፤ በ1500 ሜትር ሴቶች ዳዊት ስዩም፤ በ3000 ሜትር ሴቶች ሃፍታምነሽ ተስፋዬ ሃይሉ፤ በ5000 ሜትር ሴቶች ሩቲ አጋ ሶራ፤ በ3ሺሜትር መሰናክል ወየንሸት አንሳ ወልደፃዲቅ እንዲሁም በ5000ሜትር የርምጃ ውድድር አስካለ ቲካሳ በንቲ ናቸው፡፡

በ2015 የአፍሪካ ክለቦች ውድድር ቅድመ ማጣርያ ደደቢትና ቅዱስ ጊዮርጊስ   ዛሬ እና ነገ በባህርዳር ስታድዬም የመልስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡ ከ2 ሳምንት በፊት የመጀመርያ ጨዋታቸውን ከሜዳ ውጭ ያደረጉት ሁለቱ ክለቦች ወደ 1ኛ  ዙር ማጣርያ ለመግባት  እድል አላቸው፡፡ 50 ሺህ ተመልካች የማስተናገድ አቅም ያለው የባህርዳር ስታድዬም   ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲያስተናግድ ከአፍሪካ እግር ኳስ  ኮንፌዴሬሽን እውቅና አግኝቷል፡፡ስታዲየሙ  የእግር ኳስ  ሜዳን ጨምሮ ሌሎች ሁለገብ ሩጫ፣ውርወራን፣ዝላይን ያካተተ የስፖርት ማዘውተሪያ እንዲኖረው ተደርጎ ተሰርቷል፡፡ 21 ሜትር ከፍታ ያለው ይህ ግዙፍ ስታዲየም በ2ኛ የግንባታ ምእራፉ 27ሄክታር ቦታ ላይ የሚያርፍ ግዙፍ የስፖርት መንደር  ይሰራለታል፡፡ አጠቃላይ ወጪው ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚደርስ ይጠበቃል፡፡
የኢትዮጵያ ክለቦች በአህጉራዊ ውድድሮች ከቅደመ ማጣርያ አንስቶ በ1ኛ እና በሁለተኛ ዙር ማጣርያዎች ውጤታማ በመሆን ወደ የምድብ ማጣርያዎች ለመግባት ከባድ ፈተና ገጥሟቸው ቆይቷል፡፡በተለይ በቅድመ ማጣርያ ጨዋታዎች ተጋጣሚዎቻቸውን ማለፍ ከቻሉ በኋላ ወደ አንደኛ ዙር የማጣርያ ውድድር ሲሸጋገሩ ከሰሜን  እና ምዕራብ አፍሪካ ክለቦች በጥሎማለፍ ለደርሶ መልስ ጨዋታዎች እየተደለደሉ በዚህ ምእራፍ የሚገጥማቸውን ፉክክር ማለፍ ይከብዳቸዋል፡፡ ደደቢት በአፍሪካ የክለቦች ውድድር ሲሳተፍ ዘንድሮ አራተኛው ነው፡፡
በአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግ ብቸኛውን ተሳትፎ በ2014 እኤአ ላይ እንዲሁም ለሁለት ጊዜያት ደግሞ በ2011 እና በ2013 እኤአ ላይ በኮንፌደሬሽን ካፕ በመሳተፍ ውጤቱ በ1ኛው ዙር ማጣርያ ላይ በመሰናበት ተወስኖ ቆይቷል፡፡ አንጋፋው የኢትዮጵያ ክለብ ቅዱስ ጊዮርጊስ በአፍሪካ ክለቦች ውድድር ከ20 በላይ የውድድር ዘመናትን ተሳትፎ አድርጓል፡፡ በአዲስ መዋቅር መካሄድ ጀምሮ ዘንድሮ ለ19ኛ ጊዜ በአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግ ዘንድሮ ሲሳተፍ 10ኛው ተሳትፎ ይሆናል፡፡ ባለፉት 9 የአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎው ለ3 የውድድር ዘመናት ተሳትፎው በቅድመመማጣርያ ላይ ሲወሰን በ6 የውድድር ዘመናት እስከ 1ኛ ዙር ማጣርያ ብቻ ተጉዟል፡፡
በ8ኛው የአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ካፕ ደደቢት ከሜዳው ውጭ የሲሸልሱን ኮት ዲ ኦርን በስታደ ደ አሚቴ 3ለ2 በሆነ ውጤት አሸንፎ ነበር፡፡ ዛሬ በባህርዳር በሚያደርገው የመልስ ጨዋታ  በማንኛውም ውጤት አቻ መለያየት እና ማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ያሳልፈዋል፡፡ ደደቢት በአሰልጣኝ ዮሃንስ ሳህሌ የሚመራ ሲሆን የሲሸልሱን ክለብ ኮትዲኦር ባሻነፈበት ጨዋታ ሁለት ጎሎችን ዳዊት ፍቃዱ ከመረብ ሲያሳርፍ ናይጄሪያዊው 3ተኛውንና የማሸነፊያ ጎል አስቆጥሯል፡፡  ዛሬ ደደቢት የሲሸልሱን ኮት ዲኦር ጥሎ ካለፈ ከቡርኪናፋሶው አርሲ ሮቦ ወይም ከናይጄርያው ዋሪ ዎልቭስ አሸናፊ ጋር በ1ኛ ዙር ማጣርያ የሚገናኝ ይሆናል፡፡በሁለቱ ክለቦች የቅድመ ማጣርያ  ጨዋታ የናይጄርያው ክለብ በሜዳው 1ለ0 እንዳሸነፈ ታውቋል፡፡
በ19ኛው የአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግ የሚሳተፈው ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሜዳው ውጪ በኤምሲ ኤል ኡልማ የተሸነፈው 1ለ0 በሆነ ጠባብ ውጤት ነበር፡፡ ነገ በባህርዳር በሚያደርገው የመልስ ጨዋታው ቅዱስ ጊዮርጊስ በ2 ንፁህ ጎሎች ካሸነፈ ወደ ቀጣዩ የአንደኛ ዙር ማጣርያ ያልፋል፡፡ በአንደኛ ዙር ማጣርያ ከጋናው አሻንቲ ኮቶኮ ጋር ሊገናኝ እንደሚችልም ታውቋል፡፡ የጋናው ክለብ በቅድመማጣርያው ከኢስት ላንድስ ጋር ተደልድሎ የነበረ ቢሆንም የሴራልዮኑ ክለብ ከውድድሩ በመውጣቱ በፎርፌ ሊያልፍ ችሏል፡፡
የፖርኩፒን ጦረኞች ተብሎ የሚጠራው የጋናው ክልብ አሻንቲ ኮቶኮ፤ ከተመሰረተ ከ82 ዓመታት በላይ ሆኖታል፡፡ አሻንቲ ኮቶኮ በጋና ፕሪሚዬር ሊግ ለ24 ጊዜያ ሻምፒዮን በመሆን የከፍተኛ ውጤት ክብረወሰን ያስመዘገበ ሲሆን ከአፍሪካ የኛው ክፍለዘመን ምርጥ ክለቦች አንዱ ሆኖ የተመዘገበ እንዲሁም በአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግ ለሁለት ጊዚያት አሸናፊ በመሆን በውድድሩ  የከፍተኛ ውጤት ታሪክ በ7ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

12ኛው የአፍሪካ ወጣቶች አትሌቲክስ ሻምፒዮና  በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት  በሚቀጥለው ሳምንት ይጀመራል፡፡ ሻምፒዮናውን በብቃት ለማካሄድ አንጋፋው የአዲስ አበባ ስታድዬም በ5 ሚሊዮን ብር  ወጭ ሙሉ እድሳት ተደርጎለታል፡፡ እድሳቱ የስታዲየሙ አጥር፣ የመጸዳጃ ቤቶች ማስፋፋት፣ የመብራት፣ የተመልካቾች መቀመጫዎች፣ የትንሿን ስታዲየም የአስፓልት ንጣፍ፣ የፖውዛ መብራቶች ያካተተ ነው፡፡ ኢትዮጵያ አህጉራዊ የአትሌቲክስ ሻምፒዮናውን በማስተናገድ ወደፊት ትልልቅ ውድድሮችን የማዘጋጀት ፍላጎቷን ታነቃቃለች፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ፅሕፈት ቤት በሚመራ ብሔራዊ ኮሚቴ እና 12 ንዑሳን ኮሚቴዎችን በማንቀሳቀስ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል፡፡ የአዲስ አበባ ስታድዬም ሙሉ እድሳትና ለውድድሩ አጠቃላይ መስተንግዶ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ  ለበጀት እንደተመደበም ታውቋል፡፡
በሻምፒዮናው ላይ ለመሳተፍ  33 የአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌደሬሽን አባል አገራት ማረጋገጫ ልከዋል፤ 618 የአፍሪካ ወጣት አትሌቶች በሜዳ እና በትራክ ላይ በሚካሄዱ 40 የስፖርት ውድድሮች ይሳተፋሉ፡፡ በመካከለኛ እና የረጅም ርቀት ውድድሮች የምስራቅ አፍሪካ አትሌቶች በተለይ የኢትዮጵያ እና የኬንያ በፍፁም የበላይነት ፉክክር እንደሚገቡ  ሲጠበቅ፤ የምእራብ አፍሪካ አገራት አትሌቶች በአጭር ርቀት ውድድሮች እንዲሁም ደቡብ አፍሪካ እና ግብፅ በሜዳ ላይ ስፖርቶች ብልጫ እንደሚኖራቸው በመገለፅ ላይ ነው፡፡ በ12ኛው የአፍሪካ ወጣቶች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ለመሳተፍ ኢትዮጵያ 100፣ ናይጀሪያ 97 ፣ ሴራሊዮን 37፣ ሞሮኮ 35፣ ሱዳን 33፣ዚምባቡዌ 31፣ ካሜሮን 28፣ ቱኒዚያ 26፣ ቡርኪናፋሶ 23፣ ኮንጎ ብራዛቢል 19፣ ኡጋንዳ 19፣ ሴኔጋል 16፣ዛምቢያ 14፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ 13፣ ሩዋንዳ 7 ፣ ሲሼልስ 17፣አንጎላ 14  ፣ሶማሊያ 13፣ ኬንያ 12፣ ማሊ 11፣ ማዳጋስካር 8፣ አልጀሪያ 8፣ናምቢያ 8 ፣  ጋቦን 6 ግብፅ 6፣  ሌሴቶ 5፣፣ኮትዲቯር 5፣  ኬቬርዴ አይስላንድ 3፣ ፣ ስዋዚላንድ 3 እና  ጊኒ ቢሳው 1፣  ስፖርተኞችን አስመዝግበዋል፡፡
ከሁለት ዓመት በፊት ሞሪሽዬስ፤ ባምቦስ በተባለች ከተማዋ ባስተናገደችው 11ኛው የአፍሪካ ወጣቶች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ከ29 አገራት የተውጣጡ 223 አትሌቶች በ40 የስፖርት ውድድሮች ተሳትፈው ነበር፡፡  15 አገራትአንድና ከዚያም በላይ ሜዳልያ በማግኘት የደረጃ ሰንጠረዥ ውስጥ ገብተው 119  ሜዳልያዎችን ሰብስበዋል፡፡ ናይጄርያ በ19 ሜዳልያዎች (9 የወርቅ፤ 7 የብርና 3 የነሐስ) አንደኛ ደረጃ ነበራት፡፡ ደቡብ አፍሪካ በ24 ሜዳልያዎች  (7 የወርቅ፤ 9 የብርና 8 የነሐስ) ሁለተኛ ደረጃ ስትወስድ 41 አትሌቶችን አሳትፋ የነበረችው ኢትዮጵያ በ22 ሜዳልያዎች (7 የወርቅ፤ 7 የብርና 8 የነሐስ) ሶስተኛ ደረጃ አግኝታ ነበር፡፡ ግብፅ በ11 ሜዳልያዎች (5 የወርቅ፤ 4 የብርና 2 የነሐስ)፤ ኬንያ በ17 ሜዳልያዎች፤(4 የወርቅ፤ 9 የብርና 4 የነሐስ) እንዲሁም ኡጋንዳ በ4 ሜዳልያዎች (2 የወርቅ፤ 1 የብርና 1 የነሐስ) እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ አከታትለው ወስደዋል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት በ11ኛው የአፍሪካ ወጣቶች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ካገኘቻቸው 7 የወርቅ ሜዳልያዎች 6 ስድስቱን ያስመዘገቡት ሴቶች ሲሆን በወንዶች የተገኘው 1 የወርቅ ሜዳልያ ብቻ ነበር፡፡ እነሱም በ800 ሜትር ወንዶች በረከት ካህሳይ አዳነ፤ በ800 ሜትር ሴቶች አለም ገብረእግዚአብሄር፤ በ1500 ሜትር ሴቶች ዳዊት ስዩም፤ በ3000 ሜትር ሴቶች ሃፍታምነሽ ተስፋዬ ሃይሉ፤ በ5000 ሜትር ሴቶች ሩቲ አጋ ሶራ፤ በ3ሺሜትር መሰናክል ወየንሸት አንሳ ወልደፃዲቅ እንዲሁም በ5000ሜትር የርምጃ ውድድር አስካለ ቲካሳ በንቲ ናቸው፡፡

ከ19 ወራት በኋላ በብራዚሏ ከተማ ሪዮ ዲጄኔሮ  በሚደረገው 31ኛው ኦሎምፒያድ  ኢትዮጵያ በብስክሌት 2  ኦሎምፒያን ፍቅረኛሞችን ታሳትፋለች፡፡ ከ1940ዎቹ መጨረሻ እስከ 1980ዎቹ አጋማሽ ኢትዮጵያ በብስክሌት ስፖርት አምስት ኦሎምፒኮችን የተሳተፈች ሲሆን ሁለቱ ኦሎምፒያኖች ፅጋቡ ግርማይ እና ሃድነት አስመላሽ ለኢትዮጵያ በብስክሌት ስፖርት ስድስተኛው የኦሎምፒክ ተሳትፎ ማሳካት ችለዋል፡፡ ሁለቱ ኦሎምፒያኖች በኦሊምፒክ ለመካፈል የሚያበቃቸውን ሚኒማ ያስመዘገቡት  ከ2 ሳምንት በፊት ደቡብ አፍሪካ አስተናግዳ በነበረው የአፍሪካ የብስክሌት ሻምፒዮና ላይ ነው፡፡ በኦሊምፒክ መድረክ ኢትዮጵያን ለመወከል የበቁት ሁለቱ የብስክሌት ኦሎምፒያኖች ፅጋቡ ገብረማርያምና ሐድነት አስመላሽ በትዳር ለመጣመር ከጫፍ የደረሱ ፍቅረኛሞች መሆናቸው ስኬታቸውን አስደናቂ አድርጎታል፡፡
ፕሮፌሽናል ብስክሌተኛ የሆነው ፅጋቡ ግርማይ፣ በስፖርቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የፉክክር ደረጃ ያሳደገ እና የቀየረ የመጀመሪያው ብስክሌተኛ ሲሆን በደቡብ አፍሪካ ተካሂዶ በነበረው የአፍሪካ የጎዳና ላይ የብስክሌት ሻምፒዮና ላይ በመጀመርያው  በግሉ የወርቅ ሜዳልያ በመጎናፀፍ በአፍሪካ ብስክሌት ሻምፒዮና በታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን የወርቅ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያና ለምስራቅ አፍሪካ አስመዘገበ፡፡ ከዚህ ስኬቱ በኋላ ደግሞ በ48 ኪሎ ሜትር የነጠላ ውድድር  ርቀቱን 1 ሰዓት 03 ደቂቃ 05 ሰከንድ በማጠናቀቅ አምስተኛ ደረጃ ቢያገኝም ለኦሊምፒክ የሚያበቃውን ሚኒማ አሳክቷል፡፡  ስለሆነም ኢትዮጵያ በወንድ ብስክሌተኛ በኦሎምፒክ መድረክ ለመሳተፍ ስትበቃ ከ44 ዓመታት  በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ የ23 ዓመቱ ፅጋቡ ባለፉት ሁለት ዓመታት በኢትዮጵያ የብስክሌት ሻምፒዮና ለሁለት ጊዜያት አሸንፏል፡፡ ፅጋቡ የፕሮፌሽናልነት ዕድል አግኝቶ የመጀመርያ ዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ክለብ ለመቀላቀል  ወደ ደቡብ አፍሪካ ከመሄዱ በፊት የትራንስ ኢትዮጵያ ክለብ ተወዳዳሪ ነበር፡፡በፕሮፌሽናል ብስክሌተኛነት  ከ2012 እኤአ ጀምሮ ለሶስት ዓመታት በደቡብ አፍሪካው ኤምቲኤን ኩቤካ ስር ሲወዳደር ቆይቶ ላምፕሬ ሜሪዳ ለተባለ ክለብ ኮንትራት የፈረመው ከሁለት ወራት በፊት ነበር፡፡ አሁን አባል በሆነበት የጣሊያኑ የብስክሌት ክለብ ሳምፕሪ ሜሪዳ ፅጋቡ በዓመት እስከ 40,000 ዩሮ ክፍያ የሚፈፀምለት ፕሮፌሽናል ብስክሌተኛ ሆኗል፡፡ ከዓመት በፊት በቱር ዴ ታይዋን የጎዳና ላይ የብስክሌት ውድድር በማሸነፍ በዓለም አቀፍ ውድድር በኢትዮጵያ ብስክሌተኛ ለመጀመርያ ጊዜ የተመዘገበ ውጤት ሲያገኝ፤ በታላቁ የዓለማችን የብስክሌት ውድድር «ቱር ዴ ፍራንስ» ላይ በመሳተፍ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ብስክሌተኛ ለመሆን ችሏል፡፡
በሴቶች ምድብም ደግሞ ሃድነት አስመላሽ የኦሎምፒክ ሚኒማ ያመጣችው 3ኛ ደረጃ ባገኘችበት የጎዳና ላይ የብስክሌት ሽቅድምድም ሲሆን ውጤቱ ኢትዮጵያ በኦሎምፒክ ታሪክ ለመጀመርያ ጊዜ በሴት ብስክሌተኛ እንድትሳተፍ አድርጓል፡፡ ሃድነት  ተወልዳ ያደገችው በአክሱም ከተማ ሲሆን  የብስክሌት ስፖርትን ከጀመረች 10 ዓመታትን አስቆጥራለች፡፡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ በነበረችበት ወቅት ለሜታ አቦ ቢራ ክለብ ስትወዳደር ቆይታ ከዚያም ትራንስ ኢትዮጵያን ተቀላቅላለች፡፡ሐድነት አስመላሽ በስፖርት ሳይንስ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዲግሪዋን ይዛለች፡፡ በብስክሌት ስፖርት የሚሳተፉ የኢትዮጵያ ሴቶች ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ማድረግ የጀመሩት ባለፈው ዓመት ሲሆን በአገር ውስጥ በሚካሄዱ ውድድሮች ለተከታታይ ስምንት ዓመት የኢትዮጵያ ሻምፒዮን የነበረችው ሃድነት አስመላሽ የኦሎምፒክ ተሳትፎን በማግኘቷ ከፍተኛ መነቃቃት ትፈጥራለች፡፡
በኢትዮጵያ የስፖርት ታሪክ በኦሎምፒክ መድረክ ኢትዮጵያ በፈርቀዳጅነት ከተሳተፈችባቸው  ውድድሮች አንዱ የብስክሌት ስፖርት እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ከ60 ዓመታት በላይ እድሜ ላስቆጠረው የብስክሌት ስፖርት ኢትዮጵያ በኦሎምፒክ መድረክ የሚወክሏትን ሁለት ኦሎምፒያኖች ማግኘቷ ከፍተኛ መነቃቃት እንደሚፈጥር ታምኖበታል፡፡