Administrator
Monday, 15 September 2025 08:54
የኬንያው ኢኩቲ ባንክ የኢትዮጵያን የባንክ ገበያ ሊቀላቀል ነው
ኢኩቲ ባንክ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ኢንዱስትሪ የሚቀላቀል ሁለተኛው የኬንያ ባንክ ሊሆን ነው፡፡
ኢኩቲ ባንክ ወደ ኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ ለመግባት በሚያደርገው እንቅስቃሴ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር በይፋ ውይይት ጀምሯል፡፡
የኢኩቲ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ጀምስ ምዋንጊ በቅርቡ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ዘለቀ ተመስገን ጋር ተገናኝተው፣ ባንኩ በኢትዮጵያ ሊንቀሳቀስ በሚችልበት የህግ ማዕቀፍ ዙሪያ መወያየታቸው ተጠቁሟል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽነር በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት፤ ባንኩ ኢትዮጵያ ውስጥ በሚያደርገው ኢንቨስትመንት አስፈላጊው ትብብርና ድጋፍ ይደረግለታል።
የኢኩቲ ባንክ ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ጀምስ ምዋናጊ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ መንግስት የፋይናንስ ሴክተሩን ለውጪ ባለሀብቶች ክፍት ማድረጉ ምቹ አጋጣሚ ነው ብለዋል።
አክለውም፤ ባንኩ
የኬንያው ኢኩቲ ባንክ የኢትዮጵያን የባንክ ገበያ ሊቀላቀል ነው
ኢኩቲ ባንክ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ኢንዱስትሪ የሚቀላቀል ሁለተኛው የኬንያ ባንክ ሊሆን ነው፡፡
ኢኩቲ ባንክ ወደ ኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ ለመግባት በሚያደርገው እንቅስቃሴ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር በይፋ ውይይት ጀምሯል፡፡
የኢኩቲ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ጀምስ ምዋንጊ በቅርቡ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ዘለቀ ተመስገን ጋር ተገናኝተው፣ ባንኩ በኢትዮጵያ ሊንቀሳቀስ በሚችልበት የህግ ማዕቀፍ ዙሪያ መወያየታቸው ተጠቁሟል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽነር በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት፤ ባንኩ ኢትዮጵያ ውስጥ በሚያደርገው ኢንቨስትመንት አስፈላጊው ትብብርና ድጋፍ ይደረግለታል።
የኢኩቲ ባንክ ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ጀምስ ምዋናጊ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ መንግስት የፋይናንስ ሴክተሩን ለውጪ ባለሀብቶች ክፍት ማድረጉ ምቹ አጋጣሚ ነው ብለዋል።
አክለውም፤ ባንኩ ኢትዮጵያ ውስጥ በሚያደርገው ኢንቨስትመንት ለሌሎች ኢትዮጵያ ውስጥ በዘርፉ መሰማራት ለሚፈልጉ የውጭ ኩባንያዎች ምሳሌ መሆን እንደሚፈልግ ገልጸዋል።
ኢኩቲቲ ባንክ በኬንያ፣ ኡጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሩዋንዳና ኮንጎ ውስጥ በፋይናንስ ዘርፍ የካበተ ልምድ እንዳለው ይታወቃል፡፡


Published in
ዜና
Tagged under
Monday, 15 September 2025 08:33
አንጋፋው ዲፕሎማት ዶ/ር ምናሴ ኃይሌ በ95 ዓመታቸው ሕይወታቸው ማለፉ ተሰምቷል
ኢትዮጵያዊው ዲፕሎማት በ95 ዓመታቸው ሕይወታቸው አለፈ
በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዘመን በማስታወቂያ ሚኒስትርነት፣ እንዲሁም ከአብዮቱ በፊት የመጨረሻው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በመሆን ሀገራቸውን ያገለገሉት አንጋፋው ዲፕሎማት ዶ/ር ምናሴ ኃይሌ በ95 ዓመታቸው ሕይወታቸው ማለፉ ተሰምቷል፡፡
በ1922 ዓ.ም የተወለዱት ዶክተር ምናሴ፤ ከአሜሪካው ዊስኮንሰን ማዲሰን ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዲግሪያቸው ካገኙ በኋላ፣ ከኮሎምቢያ የሕግ ዩኒቨርስቲ ዶክትሬታቸውን አግኝተዋል።
በተለይ የአፍሪካ ሕብረት ዋና መሥሪያ ቤት ከአዲስ አበባ እንዲነሳ በተጠየቀ ወቅት በሠጡት ምላሽ የሚታወቁት አንጋፋው ዲፕሎማት፣ በሚኖሩበት ሰሜን አሜሪካ ሕይወታቸው ማለፉ ተነግሯል፡፡
Published in
ዜና
Tagged under
Monday, 15 September 2025 08:28
የቀድሞ የግብጽ ወታደራዊ አዛዥ እስራኤልን አስጠነቀቁ
"የእስራኤል ጄቶች ግብፅን ቢያጠቁ መመለሻ አያገኙም"
የቀድሞ የግብጽ ወታደራዊ አዛዥ ኮሎኔል ሃተም ሳበር፣ የእስራኤል አውሮፕላኖች በግብፅ ላይ ጥቃት ቢሰነዝሩ "መመለሻ ቦታ እንደማያገኙ" በቴሌቪዥን ባደረጉት ቃለመጠይቅ ግልጽ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል፡፡
"የእስራኤል አየር ሃይል ግብፅን ቢያጠቃ፣ ከእስራኤል ለጥቃት የሚነሱ አውሮፕላኖች የሚመለሱበት መንገድ አያገኙም" ሲሉ ሳበር አስጠንቅቀዋል፡፡
አዛዡ ይህን የተናገሩት በቅርቡ እስራኤል በኳታር ዋና ከተማ ዶሃ ከፍተኛ የሃማስ መሪዎች ላይ ያነጣጠረ የአየር ድብደባ መፈጸሟን ተከትሎ ነው።
በአንድ ወቅት በግብፅ ጦር ውስጥ ካሉት ልዩ የፀረ-ሽብር ክፍሎች አንዱን የመሩት ሳበር፤ ምንም ተጨማሪ ማብራሪያ ባይሰጡም፣ መልዕክታቸው ከወትሮው በተለየ መልኩ ቀጥተኛ እንደነበር ዴይሊ ኒውስ ኢጂፕት ዘግቧል፡፡
ተንታኞች፤ የአዛዡ ማስጠንቀቂያ የእስራኤል ወታደራዊ እንቅስቃሴ ከተለመደው አድማስ እየተስፋፋ መምጣቱ፣ ካይሮ ላይ የፈጠረውን ሰፊ ስጋት እንደሚያንጸባርቅ ጠቁመዋል፡፡
የግብፅ መንግስትና ወታደራዊ ሃይሎች ለሳበር የቴሌቪዥን ማስጠንቀቂያ አዘል አስተያየቶች እስካሁን ምላሽ አልሰጡም ተብሏል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
የሰሞኑ አጀንዳ
Tagged under
Monday, 15 September 2025 08:27
"ስርቆትና ማጭበርበር ከሞላ ጎደል የጠፋበት ዓመት ነው" ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ
የትምሕርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ በ2017 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ስርቆትና ማጭበርበር በአመዛኙ እንዳልተስተዋለ ተናገሩ። ሚኒስትሩ አክለውም፣ መካከለኛ ገቢ የሚያገኘው ዜጋ ልጆቹን ከግል ወደ መንግስት ትምሕርት ቤቶች መልሶ እንዲያስተምር የተለያዩ እርምጃዎች እንደሚወሰዱ ገልጸዋል።
ዛሬ መስከረም 4 ቀን 2017 ዓ.ም. ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፣ መሰረታዊ የትምሕርት ዘርፍ ለውጥ የመተግበር ዕንቅስቃሴ ከተጀመረ አራት ዓመት ማስቆጠሩን ጠቅሰው፣ የመጀመሪያው ዙር በ2017 ዓ.ም. መጠናቀቁን አመልክተዋል። የፈተና አሰጣጥ ሂደቱን መለወጥ የዚሁ ዕንቅስቃሴ አንድ አካል መሆኑንና "ተጨባጭ መሻሻሎች" እየተስተዋሉ እንደሚገኙ አንስተዋል።
"በፈተና አሰጣጥ የተጋረጠብን ችግር ከአጠቃላይ የማሕበረሰብ የሞራል ክስረት ጋር የተያያዘ ነው" ያሉት ሚኒስትሩ፣ ስኬትን በአቋራጭ መንገድ የማግኘት አስተሳሰብ በትምሕርት ዘርፉ ላይ ፈተና መጋረጡን ተናግረዋል። ይህን እና መሰል ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ እርሳቸው የሚመሩት ሚኒስቴር መስሪያ ቤት የፈተና አሰጣጥ ሂደቱን "በየደረጃው" የመለወጥ ስራዎችን በመስራቱ ሳቢያ፣ የፈተና ስርቆትና ማጭበርበር ተግባራት "በጉልሕ" መቀነሳቸውን አስረድተዋል።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ፣ "ስርቆትና ማጭበርበር ከሞላ ጎደል የጠፋበት ዓመት ነው" በማለት ባሳለፍነው ዓመት በመላ አገሪቱ ለሚገኙ 585 ሺሕ 882 ያህል ለሚሆኑ ተማሪዎች በተሰጠው የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ላይ የኩረጃ ተግባራት ቀንሰው መታየታቸውን ጠቅሰዋል።
ሚኒስትሩ ከዚሁ ጋር የተገናኙ አሕዛዊ መረጃዎችን ሲያብራሩ፣ ባለፉት ሶስት ዓመታት 29 ሺሕ 100 የማጭበርበር ተግባራት መመዝገባቸውን፤ በ2016 ዓ.ም. 379 ተመሳሳይ ተግባራት ሲስተዋሉ፤ በዘንድሮ ዓመት ግን 120 የኩረጃ እና ማጭበርበር ድርጊቶች መገኘታቸውን አብራርተዋል።
"ተፈታኝ ተማሪዎች በራሳቸው አቅም ብቻ ፈተናውን ማለፍ እንደሚችሉ ያወቁበት ዓመት ነው" ያሉት ፕሮፌሰሩ፤ ለአጠቃላይ የውጤት "መሻሻል" የተማሪ ወላጆች ለትምሕርት የሚሰጡት ትኩረት መጨመር እና በቅርቡ መሰጠት የተጀመረው የመምህራን ስልጠና አስተዋጽዖ ማድረጋቸውን አልሸሸጉም።
ከዚህም ባለፈ፣ በመጪው ጊዜያት መካከለኛ ገቢ የሚያገኙ ኢትዮጵያውያን ልጆቻቸውን ከግል ወደ መንግስት ትምሕርት ቤቶች እንዲመልሱ በትምሕርት ሚኒስቴር በኩል የተለያዩ ዕርምጃዎች እንደሚወሰዱ ተናግረው፣ በተለይ የመንግስት ትምሕርት ቤቶች የመማር ማስተማር ሂደትን የማሻሻል ስራ ቅድሚያ እንደሚሰጠው አስታውቀዋል።


Published in
ዜና
Tagged under
Monday, 15 September 2025 07:06
ዳንጎቴ በናይጄሪያ የነዳጅ ዋጋ ላይ ቅናሽ ሊያደርግ ነው
ዳንጎቴ የነዳጅ ማጣሪያ ኩባንያ በመላ ናይጄሪያ ነፃ የነዳጅ ማጓጓዝ አገልግሎት ሊሰጥ መሆኑ ተዘግቧል፡፡
ኩባንያው ከመስከረም 5 ጀምሮ በአቡጃ፣ ኤዶ፣ ሪቨርስ፣ ዴልታ፣ ክዋራ፣ ሌጎስ እና በደቡብ ምዕራብ አካባቢዎች የነዳጅ ችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ቅናሽ እንደሚያደርግም አስታውቋል፡፡
"በሀገሪቱ ያሉ ሁሉም የነዳጅ ማደያ ጣቢያ ባለቤቶች ለነፃ ማጓጓዣውና ለሌሎችም ጥቅማ ጥቅሞች መመዝገብ ይችላሉ" ሲል ኩባንያው መግለጹን ስፑትኒክ ዘግቧል፡፡
Published in
ዜና
Tagged under
Monday, 15 September 2025 07:05
ጃማይካ ከ10 ዓመት በኋላ በ100 ሜትር ወርቅ አገኝች
ዛሬ በተደረገው የወንዶች 100 ሜትር ፍጻሜ ጀማይካውያኑ 1ኛ እና 2ኛ ወጥተዋል፡፡
ኦብሊኬ ሴቪሊ በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ የገባበት 9 ሰከንድ 77 ማይክሮ ሰከንድ የግል ምርጥ ሰዓቱም ሆኖ ተመዝግቧል፡፡
ለመጨረሻ ጊዜ በ2015 የቤጂንግ ዓለም ሻምፒዮና በአትሌት ዩሲያን ቦልት የወርቅ ሜዳልያ ያገኝችው ጃማይካ፤ ከ10 ዓመት በኋላ ከወርቅ ሜዳልያው ጋር ተገናኝታለች፡፡
ሌላኛው ጃማይካዊ ኪሻኒ ቶምሰን 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቋል፡፡ አሜሪካዊው ኖህ ላይስ 3ኛ ደረጃን አግኝቷል፡፡
በሴቶች 100 ሜትር ፍጻሜ ደግሞ አሜሪካዊቷ ጀፈርሰን ውድን አሸንፋለች፡፡
Ebc sport-
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ስፖርት አድማስ
Tagged under
Monday, 15 September 2025 07:04
አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ የብር ሜዳልያ አስገኘ
በጃፓን ቶክዮ እየተካሄደ ባለው 20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሁለተኛ ቀን ዉሎ ኢትዮጵያ ሁለት የብር ሜዳሊያዎች አገኘች።
ዛሬ ከሰዓት በኋላ ላይ በተደረገው የወንዶች የ10 ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ሁለተኛ በመሆን የብር ሜዳሊያ አስገኝቷል፡፡
ዮሚፍ ቀጀልቻ 50 ሜትር እስከሚቀር ድረስ ሲመራ ቢቆይም፣ በፈረንሳዊው አትሌት ጂሚ ግሬሰር ተቀድሞ 2ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል፡፡
አትሌት ሰለሞን ባረጋ 6ኛ ደረጃን ይዞ ሲያጠናቅቅ፣ በሪሁ አረጋዊ 12ኛ ደረጃን ይዞ ውድድሩን አጠናቋል፡፡
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ስፖርት አድማስ
Tagged under
Monday, 15 September 2025 07:03
በ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና 8.4 በመቶ ተማሪዎች 50 በመቶና ከዚያ በላይ ውጤት ማምጣታቸው ተገለጸ
• ከ585ሺ 882 ተፈታኞች 48,929 ተማሪዎች አልፈዋል
• 1 ሺህ 249 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም
በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና 8.4 በመቶ ተማሪዎች 50 በመቶና ከዚያ በላይ ውጤት ማምጣታቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታወቁ፡፡
ሚኒስትሩ ይህን ያስታወቁት በዛሬው ዕለት ከ9 ሰዓት ጀምሮ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ነው፡፡
585 ሺህ 882 ተማሪዎች ፈተናውን መፈተናቸውን የጠቆሙት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፤ ፈተናውን ከወሰዱት ውስጥ 48,929 ተማሪዎች ፈተናውን ማለፋቸውን ገልጸዋል፡፡
50 በመቶና ከዚያ በላይ ውጤት ካስመዘገቡት መካከል የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች 5.2 በመቶ፣ የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ደግሞ 11.4 በመቶ እንደሆኑ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ጠቅሰዋል፡፡
ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡም በተፈጥሮ ሳይንስ ከ600 ፦ 591 ወንድ ተማሪ ከዶዶላ ኢፋ ቦሩ ትምህርት ቤት፤ 579 ሴት ተማሪ ከብስራተ ገብርኤል ትምህርት ቤት ሲሆኑ፤በማህበራዊ ሳይንስ ፦562 ወንድ ከአምቦ ቦርዲግ ትምህርት ቤት ፤ 548 ከሴት ከሴንት ጆሴፍ ትምህርት መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡
በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና 1 ሺህ 249 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ተናግረዋል። 50 ትምህርት ቤቶች ደግሞ ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን አሳልፈዋል ብለዋል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ዜና
Tagged under
Monday, 15 September 2025 07:02
ኢትዮጵያ ባለ 62 ፎቅ ሰማይ ጠቀስ ህንጻ ልትገነባ ነው
• 445 ሚሊዮን ዶላር እንደሚፈጅ ተገምቷል
ኢትዮጵያ ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ አገራት ረጅሙን ባለ 62 ፎቅ ሰማይ ጠቀስ ህንጻ ለመገንባት እንዳቀደች የተዘገበ ሲሆን፤ ይህም የአገሪቱን የዝመና ጥረት አጉልቶ ያሳያል ተብሏል።
በዓለማቀፉ አማካሪ ቡድን ዳር አል-ሃንዳሳህ የተነደፈው ህንጻው እስከ 1,074 ጫማ ከፍታ ያለው ሲሆን፤ ከጆሃንስበርጉ ሊዮናርዶ ህንጻ በመላቅ በክልሉ ከሚገኙ ህንጻዎች ረጅሙ ያደርገዋል ሲል ግሬት አፍሪካ ዲጂታል ሚዲያ ዘግቧል፡፡
445 ሚሊዮን ዶላር እንደሚፈጅ የተገመተው ፕሮጀክቱ፣ ጥብቅ የጨረታ ሂደትን ያካተተ ሲሆን፤ ይህም ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ኮንትራክተሮችን እንደሚፈልግ ማሳያ ነው ተብሏል።
በአዲስ አበባ ቂርቆስ ወረዳ ውስጥ የሚገነባው ሕንፃው፤ የሰማይ ላይ መናፈሻና ሬስቶራንት የሚያካትት ሲሆን፣ ቢዝነስን ከመዝናኛ ጋር የሚያጣምር እንደሚሆን ተጠቁሟል፡፡
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ዜና
Tagged under
Monday, 15 September 2025 07:00
ኢትዮጵያ ድምጸ ተዓቅቦ አድርጋለች
ኢትዮጵያ፣ የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ለእስራኤል ፍልስጤም ግጭት የኹለት አገራት መፍትሄ ተፈጻሚ እንዲኾን ባለፈው አርብ ምሽት በአብላጫ ድምጽ ባጸደቀው ውሳኔ ላይ ድምጸ ተዓቅቦ አድርጋለች።
አስገዳጅነት የሌለውን ውሳኔ 142 አገራት ሲደግፉት፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ 12 እገራት ድምጸ ተዓቅቦ አድርገዋል። እስራኤልና ፍልስጤም ኹለት አገራት እንዲኾኑ የሚያስችሉ "ተጨባጭ"፣ "በጊዜ ገደብ የታሠሩ" እና "የማይቀለበሱ" ርምጃዎች እንዲወሰዱ በውሳኔው የጠየቀው ጠቅላላ ጉባኤው፣ የፍልስጤሙን ሐማስንም ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ አውግዟል።
አሜሪካና እስራኤል ጠቅላላ ጉባኤው ይህን ውሳኔ ማሳለፉን አውግዘዋል።
ጠቅላላ ጉባኤው ይህን ውሳኔ ያሳለፈው፣ ብሪታንያ፣ ፈረንሳይ፣ ቤልጂዬም፣ ካናዳና አውስትራሊያ በተያዘው ወር ለፍልስጤም አገርነት በይፋ እውቅና ለመስጠት እየተዘጋጁ ባሉበት ዋዜማ ላይ ነው።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ዜና
Tagged under
