Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62

ባለፈው ሰሞኑን በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ የኖህ ዘመን ታሪክን በተመለከተ የሚወጡ መጣጥፎችን ስመለከት
እኔም በዚህ ሃሳብ ዙሪያ የምለው     ነገር ካለ ብዬ ማውጠንጠን ጀመርኩ፡፡ በተለይ የኖህ መርከብማረፊያዋ በአገራችን መሆኑን የሚገል የታሪክ መሐፍ መታተሙን ስሰማ፣ ነገሩ ግርም አለኝና ..ለመሆኑ የታሪኩ እውነታነት ባልተረጋገጠ ትረካ ላይ የባለቤነት ጥያቄ ማንሳቱ ፋይዳው ምንድን ነው?.. ብዬ አሰብኩ፡፡

ነባር የግዕዝ ቅኔ (በስማ በለው) ልጥቀስሽ፡-
..እመ ተናገርኩ ድቅ ሰብአዛቲ ዓለም ይፀልዑኒ
ወከመ ኢይ ንብብ ሐሰተ ኩነኔ ዘአከ ያፈርሃኒ፤..
በዚያው በስማበለው ሲተረጐም፣
..እውነትን እንዳልናገር የዚህ ዓለም ሰዎች ይጠሉኛል
ሐሰትንም እንዳልናገር ፍርድህ (የእግዚአብሔር) ያስፈራኛል..
የዚህ ቅኔ መድፊያ እኔን አይመለከተኝምና ነው የቆረጥኩት፡፡ እንዲህ ይላል ..ወእምኩሉስ አርምሞ ይኀኄይስ ወይሣኔ.. (ከሁሉ ግን ዝም ማለት ይሻለኛል) ይሄ ነባር ቅኔና አመለካከቱ ተጋግዘው ኢትዮጵያውያን በሌለን የታሪክ ቁመና ለመዘናከት እንድንሞክር አድርገውናል፡፡

ከዕለታት አንድ ቀን አንድ አባት ልጁን አስከትሎ አህያ ሊሸጥ ወደ ገበያ ይወጣል፡፡
መንገድ ላይ እየተጫወቱና እየተሳሳቁ የሚመጡ ሴቶች ያገኛሉ፡፡ ሴቶቹ አባትና ልጁን እያዩ፤
..በዚህ በኮረኮንች መንገድ አህያ እያላቸው በእግራቸው የሚሄዱ ጅሎች አይታችሁ ታውቃላችሁ?.. አሉ፡፡
አባት፤ ሴቶቹ የሚሉት ትክክል ነው አለና አሰበ፡፡ ስለዚህም ልጁን አህያ ላይ ጭኖ እሱ እየተከተለ መንገድ ቀጠለ፡፡ መንገድ ላይ ሽማግሌ ጓደኞቹን አገኘ፡፡ እነሱም ..ልጅህን እንዴት እያባለግኸው እንደሆነ ታውቆሃል? አንተ ሽማግሌው በደከመህ ሰዓት ልጅህ በአህያ አንተ በእግርህ እንዴት ትሄዳለህ?.. አሉት፡፡

ከያንያን ከሞቷ ይልቅ በመጨረሻ ሕይወቷ አዝነዋል
በክራር ዜማዎቿ ይበልጥ የምትታወቀውና ሐሙስ ማለዳ በ78 ዓመቷ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየችው አንጋፋ አርቲስት አስናቀች ወርቁ ሥርዓተ ቀብር ትናንት ተከናወነ፡፡ በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ሥላሴ ደብር እኩለ ቀን ላይ በተከናወነው ሥርዓተ ቀብር የሙያ አጋሮቿ፣ አድናቂዎቿና ቤተሰቦቿ ተገኝተዋል፡፡ ከቀብር ሥነሥርአቱ በፊት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር በተከናወነላት የመታሰቢያ ዝግጅት የተገኙ አርቲስቶች ከሞቷ ይልቅ ካለፉት አስር ዓመታት ወዲህ በነበረው የመጨረሻ ሕይወቷ አዝነዋል፡፡ በዝግጅቱ የመጨረሻ ዘመኗ የሕመምና የሰቆቃ ነበር ብለዋል፡፡ አንጋፋዋ አርቲስት ሰላማዊት ገብረሥላሴ ..ሞተች አይባልም እረፍት ነው ሕመም ቆይቶባታል.. ብላለች፡፡

ሰሞኑን 30ኛ ዓመት የልደት በዓሏን ያከበረችው የቢዮንሴ እርግዝና ይፋ ከሆነ በኋላ ከቢላደን ግድያ ወሬ የላቀ ትኩረት ማግኘቱን የተለያዩ ዘገባዎች አመለከቱ፡፡ በሙዚቃ፤ በአልባሳት፤ በሽቶና በቮድካ መጠጥ ንግዶች በከፍተኛ ገቢ እየተተኮሰች ያለችው ቢዮንሴ፤ የ5 ወራት ንስ መያዟ በይፋ ከታወቀ በኋላ አንዳንድ ዘገባዎች የፖፕ ንግስቷ ወርቃማ ዘመን የመጨረሻ ምእራፍ ሲሉ g””ቢዮንሴ ማርገዟን ይፋ ያደረገችው ከ2 ሳምንት በፊት በተደረገው የኤምቲቪ የሙዚቃ ቪድዮ አዋርድ ላይ ነበር፡፡

በጣሊያኗ ከተማ ቬኒስ በተደረገው 68ኛው የቬኒስ ፊልም ፌስቲቫልና ሰሞኑን በተከናወነው የቶሮንቶ ፊልም ፌስቲቫል ላይ ከቀዩ ምንጣፍ እስከ ግዙፎቹ ስክሪኖች አንጋፋ የፊልም ባለሙያዎች በተዋናይነትና በዲያሬክተርነት የደመቁበት ሲሆን አንጋፋ ተዋናዮች ፊልሞችን ዲያሬክት በማድረግና ሲኒማን በመተው ወደ ቲቪ ኢንዱስትሪ የመግባት ዝንባሌ እያሳዩ መምጣታቸውን ..ዘ ሆሊውድ ሪፖርተር.. ዘግቧል፡፡

ጄኒፈር ሎፔዝና ካሜሮን ዲያዝ በመሪ ተዋናይነት በሚሳተፉበት ..ዋት ቱ ኤክስፔክት ዌን ዩአር ኖት ኤክስፔክቲንግ.. የተባለ ፊልም ቀረፃ ላይ ..ትራንስ ኢትዮጵያ.. የተባለ አየር መንገድ በልቦለድ መፈጠሩን ተገለፀ፡፡ በፊልሙ አንድ ትእይንት ቀረፃ ላይ በሂውተን ካውንቲ ኤርፖርት ከሚገኙ አውሮፕላኖች አንዱ ላይ ..ትራንስ ኢትዮጵያ.. በሚል መታተሙን የሚገልፀው ዘገባው፤ በአየር ማረፊያው ደጃፍ ላይ የኢትዮጵያ ባንዲራ ተሰቅሎ ሲውለበለብ መታየቱን አመልክቷል፡፡

የ21 ዓመቱ የአርኤንድቢ ሙዚቃ አቀንቃኝ አቤል ተስፋዬ በካናዳና በአሜሪካ በሥራው እየገነነ መምጣቱን ..ሃፊንግተን ፖስት.. ዘገበ፡፡ አቤል ሰሞኑን በአሜሪካ ሊያቀርበው የነበረውን የሙዚቃ ኮንሰርት ባልታወቀ ምክንያት ሰርዞታል፡፡ ..ዘዊከንድ.. በተሰኘ ስሙ በቶሮንቶ ከፍተኛ እውቅና እያገኘ የመጣው አቤል፤ ኢትዮጵያዊ የዘር ግንድ ቢኖረውም በዜግነቱ ካናዳዊ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በኦንቶናርዮ ካናዳ ስካርድ ብሮው በተባለ አካባቢ የሚኖረው አቤል ተስፋዬ፤ ከ2008 ጀምሮ በድምፃዊነት እየሰራ ሲሆን ኤክስኦ በተባለ የሙዚቃ ኣሳታሚ ..ሃውስ ኦፍ ባሉንስ..

Saturday, 17 September 2011 09:50

..በሃበሻ ጀብዱ.. ላይ ውይይት

የሚዩዚክ ሜይ ዴይ ኢትዮጵያ የመፃህፍት ንባብና የውይይት ክለብ አዶልፍ ፓርለሳክ በፃፈውና ተጫነ ጀብሬ መኮንን በተረጎመው ..የሀበሻ ጀብዱ.. መሐፍ ላይ ሊወያይ ነው፡፡ ነገ ከቀኑ 8 ሰዓት በአምስት ኪሎው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተመዘክር አዳራሽ ውይይት መነሻ ሀሳብ በማቅረብ የሚያወያዩት ደራሲ አበረ አዳሙ ናቸው፡፡   
የከያኒዎች የቲቢ ውይይት

ከሁለት ሚሊየን ብር በላይ የወጣበትና ደረጃውን የጠበቀ የተባለለት ሙአለ ሕፃናት በምዕራብ ሸዋ ጊንጪ ከተማ ተከፈተ፡፡ “World Together Ethiopia” በተባለ የደቡብ ኮርያ በጐ አድራጊ ድርጅት በሁለት ሚሊየን አንድ መቶ ዘጠና ብር ወጪ የተቋቋመው ሙአለ ሕፃናት በአንድ ጊዜ ዘጠና ሕፃናት ተቀብሎ ያስተናግዳል፡፡