Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62

የኦስካር ሽልማት ከወር በኋላ የሚካሄድ ሲሆን ለሽልማት የሚፎካከሩት እጩዎች ሰሞኑን እንደሚገለፁ ይጠበቃል፡፡የስቴቨን ስፒልበርግ ፊልም “ሊንከን” እና የቤን አፍሌክ ፊልም “አርጎ” በዘንድሮው የኦስካር ሽልማት በበርካታ ዘርፎች የመታጨት እድላቸው ሰፊ መሆኑን ዩኤስኤ ቱዴይ ዘግቧል፡ በሌላ በኩል 70ኛው የጎልደን ግሎብ አዋርድ ከሳምንት በኋላ በካሊፎርንያ ቤቨርሊ ሂልስ በሚገኘው የቤቨርሊ ሆቴል ይከናወናል፡፡ ለዚሁ ሽልማት የቀረቡ እጩዎች ከወር በፊት ይፋ የተደረጉ ሲሆን የሽልማት ስነስርዓቱ የኦስካር አሸናፊዎችን ፍንጭ ሊሰጥ ይችላል ተብሏል፡፡

ኪም ካርዴሽያን ከራፐር ካናዬ ዌስት የመጀመርያ ልጇን መፀነሷ እያነጋገረ ነው፡፡ ለስምንት ወራት በፍቅረኝነት ለቆዩት ሁለቱ ዝነኞች ግንኙነት መቀጠል የ12 ሳምንት እድሜ እንዳለው የተነገረው ፅንስ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ተብላል፡፡ ኪም ካርዴሽያን ከእርግዝናዋ ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ዝና ያገኘችበት የሪያሊቲ ሾው እና የፋሽን ንግስትነቷ አደጋ ላይ ይወድቃል የሚል ስጋት እንዳለ ኤምቲቪ ሲጠቁም፤ “ዘ ሃፊንግተን ፖስት” በበኩሉ በአወዛጋቢነቱ የሚታወቀው ካናዬ ዌስት መልካም አባትነት ጥርጣሬ እንደፈጠረ ዘግቧል፡፡ ፎርብስ መፅሄት በቲቪ ኢንዱስትሪው ከፍተኛ ክፍያ በማግኘት በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀመጣት ኪም ካርዴሽያን፤ በፋሽን እና በኮስሞቲክስ ንግዷ 65 ሚሊዮን ዶላር ሃብት ማካበት እንደቻለች ታውቋል፡፡

በዘንድሮ የፈረንጆች ዓመት የኮንሰርት ገቢ የፖፕ ሙዚቃ ንግስቷ ማዶና በአንደኝነት እንደምትመራ ፎርብስ መፅሄት አስታወቀ፡፡ ሊጠናቀቅ ሁለት ቀናት ብቻ በቀረው 2012 ዓ.ም ሙሉ ለሙሉ ትኬታቸው የተሸጡ 72 ኮንሰርቶችን በመላው ዓለም ያደረገችው ማዶና፤ በአጠቃላይ 1ሚ.635ሺ176 ታዳሚዎችን በማዝናናት 228.4 ሚ. ዶላር ገቢ አድርጋለች፡፡

የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር በአገሪቱ በሚረቀቀው አዲስ ህገ መንግስት ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሙሉ እንዲሳተፉ ጥሪ አቀረቡ፡፡ አልበሽር ሰሞኑን ለተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ መሳሪያ ለታጠቁ ሃይሎች እና የሲቪል ማህበር ድርጅቶች ባቀረቡት ጥሪ፣ “አሁን መተባበር ያቃተን በውስጣዊ ችግሮቻችን ላይ ነው፣ አገራችን በጣም ሰፊ ናት፣ ለሁላችንም ትበቃለች፣ ስለዚህ መሳሪያ መሸከም አያስፈልግም፣ አገራችን እንዴት መመራት እንዳለባት በጋራ እንወስን” ብለዋል፡፡ በህገ መንግስት ማርቀቅ ሂደቱ ላይ ማንም ወገን አይገፋም ያሉት አልበሽር፣ ህገመንግስቱ የሁሉንም ወገኖች ይሁንታ የሚያገኝ እንደሚሆንም ገልፀዋል፡፡

Saturday, 05 January 2013 11:14

ጨረቃ እንደ ፀሐይ

ጥልቅ የሆነ የንባብ ፍቅር ያደረበት ልጅ እያለ ነው። ቤተሰቦቹም ቀለም ቀመስ ስለሆኑና ኑሯቸውም የተደላደላ ስለነበር የንባብ ጥማቱን ለማርካት ችግር አልገጠመውም፡፡ በሀገሪቱ ውስጥ ለሚታተሙ ሳምንታዊ እና እለታዊ ጋዜጦች እንዲሁም መጽሔቶች አመታዊ ክፍያቸው ተከፍሎ ቤቱ ድረስ ይመጡለታል። መጽሐፍቶችማ ትልቁን የቤታቸውን መደርደሪያ ተርፈው በየቦታው ነው ተዝረክርከው የተቀመጡት፡፡
አነበበ፣ አነበበ፣ አነበበና … ጭንቅላቱ በእውቀት ተወጠረበት፡፡ እውነትም ጭንቅላቱ ይከብደው ነበር፡፡

በሠሜን ሸዋ ዞን መርሃቤቴ ወረዳ ልዩ ስሙ ጭራሮ ማርያም በተባለ ቦታ የቀድሞ ባለቤቱን ጨምሮ የባለቤቱን ወላጅ እናት፣ ወንድም እና የትዳር ጓደኛዋን በጥይት ደብድቦ የገደለው ተጠርጣሪ እስካሁን እንዳልተያዘ ተገለፀ፡፡ ተጠርጣሪው ታህሳስ 11 ቀን 2005 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡30 ገደማ ነው ግድያውን የፈፀመው ተብሏል፡፡ በእለቱ በተፈፀመው ግድያ ወላጅ እናታቸውን ወ/ሮ ዘነበች አደፍርስን፣ ወንድማቸውን አቶ ችሮታው መኮንንን እንዲሁም እህታቸውን ወ/ሮ አበሬ መኮንን እና ባለቤቷን አቶ ተጫነን በአንዲት ጀንበር ያጡት አቶ አሻግሬ መኮንን፤ ይህን ሁሉ ሠው የገደለው ግለሠብ እስካሁን በፖሊስ ቁጥጥር ስር አለመዋሉ የፈጠረባቸውን ስጋት በመግለፅ ወደግድያ ላመራው ጠብ መነሻ የሆነው የንብረት ክፍፍል ጉዳይ መሆኑን ገልፀውልናል፡፡

አንድ መቶ የሚሆኑ የዲላ ዩኒቨርስቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ክፍል ተማሪዎች ከትላንት በስቲያ ካዛንቺስ የሚገኘውን የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል ጎበኙ፡፡ የጉብኝቱ ዓላማ ተማሪዎቹ በዩኒቨርስቲው ውስጥ ስለጋዜጠኝነት በንድፈ ሃሳብ ደረጃ የተማሩትን በተግባር ለማየትና እያንዳንዱን የስራ ሂደት ቦታው ድረስ ተገኝቶ ለመመልከት እንደሆነ የጉብኝት ቡድኑ ሃላፊዎች ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡ አዲስ አድማስን  ከመጎብኘታቸው በፊት የኦሮሚያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት፣ ፋና ብሮድካስቲንግ፣ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅትንና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ድርጅትን (ኢዜአ) እንደጎበኙ የጠቆሙት ከቡድን ሃላፊዎቹ አንዱ የሆኑት መምህር ኃይለመስቀል ዘውዴ፤ በትላንትናው ዕለት ዋልታን እንደጎበኙና ዛሬ ወደ ዲላ ዩኒቨርስቲው እንደሚመለሱ አስታውቀዋል፡፡

በመጪው ዓመት መስከረም ወር መጨረሻ ላይ የሥልጣን ዘመናቸውን የሚያጠናቅቁት የኢፌዲሪ ፕሬዚደንት የተከበሩ ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የ89 ዓመት ልደትና የስልሳ ዓመት የስራ ዘመን አገልግሎት በዓል የፊታችን ማክሰኞ ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እንዲሁም አምባሳደሮችና ታዋቂ ሰዎች በተገኙበት በሸራተን አዲስ እንደሚከበር ተገለፀ፡፡ከአፄ ኃ/ሥላሴ ዘመን ጀምሮ እስካሁን ድረስ በሶስት መንግስታት በተለያዩ የስራ ኃላፊነቶች ላይ እያገለገሉ የቆዩት ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ፤ ‹‹ለሃገር መስራትን የመሰለ ክብር ያለው ነገር የለም›› ይላሉ፡፡

ሃዊ ቴክኖሎጂ ኢትዮጵያ የተባለው የቻይና ኩባንያ የገና በዓልን አስመልክቶ የፊታችን ሰኞ ለመቄዶኒያ የአዛውንቶች እንክብካቤ ማዕከል የምሳ ዝግጅትና ልዩ ስጦታ እንዳዘጋጀ ገለፀ፡፡ የሃዊ ቴክኖሎጂ ሰራተኞች የገና በዓልን ከማዕከሉ አዛውንቶች ጋር እንደሚያከብሩ የገለፀው ኩባንያው፤ ከምሳ ግብዣው በተጨማሪ ለአዛውንቱ ፍራሽ፣ ብርድ ልብስ፣ የልብስ ማጠቢያ ማሽን፣ ጤፍና የአዋቂ ዳይፐር እንደሚበረከትላቸው ለማወቅ ተችላል፡፡ መቄዶኒያ የአዛውንቶች እንክብካቤ ማዕከል ጧሪ የሌላቸውንና ታመው በየመንገዱ የወደቁ አዛውንትን ሰብስቦ ድጋፍ የሚያደርግ የበጎ አድራጎት ተቋም ነው፡፡

“ሕዝቦች የስልጣን ባለቤቶች ናቸው፡፡ የምርጫው ውጤትም በእጃቸው ላይ ነው፡፡ እናም ሁላችንም የምርጫ ካርድ እንውሰድ፡፡ ምርጫው ሰላማዊ፣ ነጻና ፍትሐዊ እንዲሆን የበኩላችንን ጥረት እናድርግ፡፡ ምርጫ ዘጠና ሰባት ያሳየንን የሕዝብ ጉልበት በተግባር ላይ እናውለው፡፡ አሁንም ከተደራጀንና በነቂስ ለምርጫ ከወጣን----ማሸነፍ በእጃችን ያለ አማራጭ መሆኑን አንዘንጋ---”
ከሙሼ ሰሙ (የኢዴፓ ፕሬዚደንት)
በአንድ ወቅት ወደ ሰሜን ሸዋ ለቅስቀሳ ከተላከው የቅንጅት አመራር ቡድን ጋር ተመድቤ ቅስቀሳውን ካጠናቀቅን በኋላ፣ ከአካባቢው አርሶ አደሮች ጋር የመወያየት እድል ገጥሞኝ ነበር፡፡ በቅስቀሳው እጅግ ደስተኛ የነበሩት አርሶ አደሮችን ማንን ትመርጣላችሁ ለሚለው ጥያቄ የሰጡኝ መልስ “ቅንጅትን” የሚል ነበር፡፡

Page 3 of 163