Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62

የዓለማችንን 25 ከፍተኛ ተከፋይ ሙዚቀኞች ደረጃን የቀድሞው ራፕር፤ የሙዚቃ አሳታሚ ባለቤት እና ነጋዴ ዶ/ር ድሬ በአንደኛ ደረጃ እንደሚመራው ፎርብስ መፅሄት አስታወቀ፡፡ ዶ/ር ድሬ በ2012 በከፍተኛ ክፍያ አንደኛ ሊሆን የበቃው 100 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት ሲሆን “ቢትስባይድሬ” በተባለ የጆሮ ማዳመጫ ምርቱ ገበያው ስለተሟሟቀለት ነው ተብሏል፡፡ ዘንድሮ “ዘ ዎል ላይቭ” የተባለ የሙዚቃ ኮንሰርት በመላው ዓለም ተዘዋውሮ በማቅረብ የተሳካለት ፒንክ ፍሎይድ፤

በዘንድሮ የሆሊውድ ፊልሞች ገቢ በበዓላት ሰሞን ከፍተኛ መሟሟቅ እያሳየ ሲሆን እስከ 11 ቢሊዮን ዶላር ገቢ በማስመዝገብ አዲስ ክብረወሰን ሊመዘገብበት ይችላል ተባለ፡፡ ሰሞኑን ከተከበረው የ”ታንክስጊቪንግ” በዓል ጋር በተገናኘ የቦክስ ኦፊስ የአሜሪካ በታሪክ ከፍተኛው ሪከርድ የሆነ የ290 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መመዝገቡን “ዘ ሆሊውድ ሪፖርተር” አስታውቋል፡፡

የእውቅ ድምፃውያንን የሙዚቃ ቪዲዮ ክሊፖች ሰርቷል - ስንታየሁ ሲሳይ፡፡ በሚሰራቸው ስራዎች ሁሉ ኢትዮጵያዊ ባህልን ማካተትና ማንፀባረቅ ይፈልጋል፡፡ በዚህ የማይስማሙ ዘፋኞች አይስማሙኝም ይላል፡፡ አብዛኞቹ ግን የምላቸውን ስለሚሰሙኝ ምስጋና ይገባቸዋል የሚለው ዳይሬክተሩ ስንታየሁ ሲሳይ፤ በኢትዮጵያ የሙዚቃ ቪዲዮ ክሊፕና ፊልሞች ዙሪያ ከጋዜጠኛ አበባየሁ ገበያው ጋር ያደረገውን ቃለምልልስ እንዲህ አቅርበነዋል፡፡
የሙዚቃ ቪዲዮ ክሊፕና የፊልም ዳይሬክተር ምን ማለት ነው … ሥራው ምንድነው?

በሚያዝያ ወር 1934 ዓ.ም በደብረ ብርሃን ከተማ መግቢያ ጠባሴ በሚባል መንደር በእረኝነት ላይ ተሰማርቶ የነበረ አንድ የስምንት ዓመት ልጅ በቅርብ ርቀት በአስፋልቱ ላይ ባለፈው ሮልስ ሮይስ መኪና መስኮት ውስጥ ያየው ሰው ምስል በቀላሉ ከህሊናው የሚጠፋ አይነት አልሆነበትም፡፡ ማታ ከብቶቹን ሰብስቦ ቤቱ ሲገባ ቀን ስላየው መኪና፣ ስለ አጀቡና በመኪናው መስኮት ውስጥ ስላየው ሰው ለአባቱ ሲነግራቸው፣ ባለ ሮልስ ሮይሱ መኪና አፄ ኃይለሥላሴ መሆናቸው አልጠፋቸውም፡፡ ልጅ አበበ ቢቂላና ጃንሆይ ለመጀመሪያ ጊዜ የተያዩት ያን እለት ነበር፡፡

ወጣት ቢኒያም ነገሱ የድሬቲዩብ ድረገጽ መስራችና ባለቤት ነው፡፡ በድሬዳዋ የተወለደው ቢኒያም፤ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በዚያው ከተማ ክርስቶስ በተባለ ትምህርት ቤት ተከታትሏል፡፡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ አሁን እንጦጦ በሚባለው የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ተምሯል፡፡ በአለማያ ዩኒቨርስቲ በኮምፒዩተር ቴክኖሎጂ በዲግሪ የተመረቀው ቢኒያም፤ በድሬዳዋ ከተማ በሚገኝ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ውስጥ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አስተባባሪነት ለሦስት ዓመት ሰርቷል፡፡ በሶማሊያ አርጌሣ በሚገኘው አድማስ ዩኒቨርስቲም በኮምፒዩተር ሳይንስ ሶፍትዌር ለአራት ዓመት አስተምሯል፡፡

በዓለማችን ሙሉ በሙሉ ከሙስና የፀዱ (100%) አገራት እስካሁን ባይገኙም በንፅፅር ግን እጅግ ከሙስና የራቁ መገኘታቸው አልቀረም፡፡ ለምሳሌ በምዕራቡ ዓለም ሦስት አገራት በአንደኛነት ተቀምጠዋል - ዴንማርክ፣ ፊንላንድ እና ኒው ዚላንድ፡፡ የሚገርማችሁ ግን ዘንድሮ አሜሪካ ከሙስና የራቀች በመሆን 19ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡
ትራንስፓረንሲ ኮራፕሽን ኢንዴክስ ዘንድሮ በ176 አገራት ላይ ባደረገው ጥናት፤ እጅግ የከፋ ሙስና ከተንሰራፋባቸው አገራት መካከል ሶማሊያ፣ ሰሜን ኮሪያና አፍጋኒስታንን የሚስተካከል አልተገኘም፡፡ በናይጀሪያና ካምቦዲያ ደግሞ ከፍተኛ የባለስልጣናት ሙስና ተንሰራፍቷል ተብሏል፡፡ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ አገራት በጉቦና በስልጣን መባለግ ዙሪያ የተሰሩ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከሆነ፤ ጥቂት አገራት ብቻ ናቸው መሻሻል ያሳዩት፡፡ በአንዳንድ አገራትማ ተውት! ግማሽ በግማሽ የሚሆነው ህዝብ እንደ ውሃ፣ ትምህርትና ጤና ያሉ መሰረታዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት እንኳን ጉቦ ይከፍላል ይላል - አዲሱ ጥናት፡፡

እንዴት ሰነበታችሁሳ!
ይሄን ታሪክ መቼም ሳትሰሙት አልቀራችሁም…ሁለቱ ሰዎች ይጣላሉ ይመስለኛል፡፡ እናማ…አንደኛው እንደመጠንቀቅ ሲል ሌላኛው ምን ይለዋል መሰላችሁ…“አይዞህ፣ አልገድልህም፡፡” ያኛው ደግሞ ‘ቆቅ ቢጤ’ ስለነበር “አልገድልህምን ምን አመጣው?” ብሎ ጠየቀ!
እናላችሁ…ብዙ ነገር “…ምን አመጣው?” እየሆነብን ተቸግረናል፡፡ስብሰባ ተቀምጣችኋል፡፡ እና ስብሰባው ሲካሄድ ይቆይና ወደ መጨረሻ አካባቢ ሰብሳቢ እንዲሀ ይላል፡፡ “ስብሰባውን በሚገባ ስለተከታተላችሁ አመሰግናለሁ፡፡ አንዳንዶቻችሁ ግን በልባችሁ የስበሰባው ዓላማ ያልተዋጠላችሁ እንዳላችሁ የታወቀ ነው፡፡” እናማ…ጥያቄው ማንም ሰው አፍ አውጥቶ “አልተዋጠልኝም…” “አልተሰለቀጠልኝም…” ምናምን ነገር ባላለበት እንዲሁ ‘ነገር ፍለጋ’ ነው እንጂ “…ያልተዋጠላችሁን ምን አመጣው?” 

ኤችአይቪ ቫይረስ እ.ኤ.አ በ1981 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ በአሜሪካ አገር መኖሩ ከታወቀ ጀምሮ በዓለም ላይ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሰለባ አድርጐአል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በአለማችን 34 ሚሊዮን ሰዎች ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩ ሲሆን በሽታው እ.ኤ.አ በ2001 ዓ.ም ብቻ 1.7 ሚሊዮን ሰዎችን ለሕልፈት ዳርጓል፡፡ በሀገራችን የቫይረሱ መኖር ከታወቀበት እ.ኤ.አ 1984 ዓ.ም ጀምሮ የበሽታው ስርጭት ቀለም፣ እድሜ፣ ጾታ፣ ሃይማኖት፣ የትምህርት ደረጃ ወዘተ ልዩነት ሳያደርግ ከሕብረተሰባችን አበይት የጤና ችግሮች ወስጥ አንዱ ሊሆን በቅቷል፡፡ በዚህም ምክንየት መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶት የተለያዩ የመቆጣጠር እንቅስቃሴዎችን ሲያደርግ እንደነበር ይታወቃል፡፡ 

ዘንድሮ ወደ 2 ቢሊዮን ብር የውጭ ምንዛሬ እንዲያስገኝ ታቅዶ ነበር
ግን በተቃራኒው ያንን በሚያክል የውጭ ምንዛሬ ከውጭ ማስመጣት የግድ ነው
መንግስት ቢዝነስ ውስጥ ገብቶ አገሪቱን ልማት በልማት ሲያደርጋት ለማየት የሚፈልጉ ሰዎች ጥቂት አይደሉም። ደግሞም ፍላጎታቸውን ለማሟላት ቃል የሚገባ መንግስት አያጡም። በእውን፣ በተጨባጭ ወይም በተግባር ፍላጎታቸውን የሚያረካ ነገር ለማየት ባይታደሉም፤ ቢያንስ ቢያንስ በምኞት ደረጃ የልብ የሚያደርስ እቅድ በሽ በሽ ነው። ልማታዊ መንግስት እቅዶች ያንሱታል ተብሎ አይታማም። በየአቅጣጫው የሚፈበረኩ እቅዶችን ትተን፤ የስኳርን ምርት በብዙ እጥፍ ለማሳደግ የወጡ እቅዶች ብቻ ብናይ እንኳ ያስጎመጃሉ።

የሌለው ድፍን ወንፊት ነው፡፡ ” ያገሬ ባላገር
ከሮበርት ዶድስሌይ ተረቶች አንዱ ይህን ይላል፡፡
ከዕለታት አንድ ቀን፤ አንድ ባህር-ዛፍና የወይን-ዛፍ ጎን ለጐን ይኖሩ ነበር ይባላል፡፡
ወይኑ፤ “የማንም ጥገኛ ሳልሆን ራሴን ችዬ በነፃነት እኖራለሁ፡፡ ስለዚህም አንተ ኖርክም አልኖርክም ምንም አትሠራልኝም” አለው ባህር ዛፉን፡፡
ባህር ዛፍም፤
“የወይን ተክል ሆይ! አንተ በተፈጥሮህ ቀጥ ያለና ወደሰማይ የማደግ ባህሪ የለህም፡፡ ዞሮ ዞሮ እንደማንኛውም የሐረግ ዘር በሌላ ጠንካራ ግንድ መደገፍ አለብህ” ሲል ነገረው፡፡

Page 9 of 163