Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62

በ1973 ዓ.ም. በፈረንሳይ አካባቢ የተወለደው አርቲስቱ፤ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በብሔራዊ ኢትዮጵያ፣ ሁለተኛ ደረጃን በተፈሪ መኰንን እንዲሁም ከእንጦጦ ቴክኒክ ኮሌጅ በቲያትር ዲፕሎማውን አግኝቷል፡፡ ..ገመና ቁ.2.. ላይ ዶ/ር ምስክርን ሆኖ የሚጫወተው አርቲስቱ፤ ከጋዜጠኛ ሰላም ገረመው ጋር አጭር ቆይታ አድርጓል፡፡
እስቲ ዳንኤል ሰውየውና ዳንኤል ተዋናዩ ምን እንደሚመስሉ ግለልኝ . . .  
|ህይወት´ ፊልም ላይ በዳይ አፍቃሪ የነበረና ይቅርታን የሚጠይቅ፣ ..የአውሬው  እርግቦች.. ላይ መቶ አለቃ ሆኖ በሶማሌ ጦርነት ከቤተሰቡ የተለያየ እና እህቱን የሚያፈቅር ወታደር፣ ..እቴጌ.. ላይ ሞኝና በራሱ ያልቆመ አፍቃሪ፣ ..ትስስር.. ላይ የታሪክ መምህር፣ ..ማክቤል.. ላይ ንፁህ አፍቃሪ፣ ..የታፈነ ፍቅር.. ላይ አጭበርባሪ  ..ተስፈኞቹ.. ላይ ለኢትዮጵያ የሚቆረቆር ከሙስና የዳ ሠራተኛ፣ ..ሰውየው.. ላይ  ዱርዬ የሀብታም ሹፌር፣ ..ባቢሎን በሳሎን.. ቲያትር ላይ ቦዘኔ አፍቃሪ፣ ..ገመና ቁጥር 2.. ላይ ዶ/ር ምስክር ነው ዳንኤል ማለት፡፡ የሚገርመኝ ..ባቢሎንን.. ስሠራ ጥሩ ያልሆነ ገ ባህሪ ወክዬ ስለምጫወት ተመልካቹ መጣ ደሞ እንደሚለኝ አውቃለሁ፡፡

ስራችንን የሚያቀላጥፍልን የኮምፒዩተር ቴክኖሎጂ በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ
ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ አገራት ከቴክኖሎጂው ጋር አብረው በመራመድ በራሳቸው ፊደል ለመጻፍ የሚችሉበትን የኮምፒዩተር ሶፍትዌር ማበጀት ከጀመሩ ቆየት ብለዋል፡፡ በአገራችንም እንደ ..ፓወር ግዕዝ.. እና ቪዥዋል ግዕዝ.. ያሉ የአማርኛ መጻፊያ ሶፍትዌሮች ተሰርተው በስፋት ጥቅም ላይ የዋሉ ሲሆን የአገርኛ ቁጥሮች መጻፊያ እና የቃላት ወይም የፊደላት መጠን ማስተካከያዎችም አሉ፡፡ በቃላት አጻጻፍ ዙሪያ የሚታዩ የፊደላት ግድፈቶችን ለማስተካከል የሚያግዘን የቃላት ማረሚያ ግን ይጐድለናል፡፡

SMS አገልግሎት ሰጪ-  ፈረሱ ለመሳቅ የራሱን ብብት መኮርኮር ግድ ሆነበት፡፡ በSMS መልዕክት ለልማት አዋጣ፣ ለማይደርስ ሎተሪ አስበላ፣ . . . ለተመራቂ ተማሪዎች አድናቆትህን በመልዕክት ግለጽ ሲባል ራሱን ኮረኮረ. . . ለካ ፈረስ ሲኮረኮር ይፈረጥጣል እንጂ አይስቅም፡፡ . . . የስልክ ካርድ የሚሸጥለት ቴሌ. . . መልዕክት የሚልከው ለቴሌ፡፡ ፈረሱ ያለቀሰው የመብራት ኃይል ባለሥልጣን በስልኩ ቴክስት ሜሴጅ ልኮለት ሲያነብ ነው፡፡ ..የመብራት አቅርቦትን የኃይል እጥረት ወዳለባቸው ቦታዎች ለማድረግ ከመብራት ካርዷ በመቀነስ እርዳታ ይለግሱ.. የሚል መልዕክት፡፡ እንደተጠየቀው መብራቱን ለእርዳታ ልኮ በጨለማ እየተንሰቀሰቀ ተቀመጠ፡፡

ያልስማው ሲመጣ የሰማው ሲሄድ፡፡
ተግሳም ለፀባይ ካልሆነው አራሚ
መናገር ከንቱ ነው ካልተገኘ ሰሚ..
(ከበደ ሚካኤል)

ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ልዑል ባላጠፋው ጥፋት ይረገማል አሉ፡፡ ትልቅ ጫካ ውስጥ ብቻውን እንዲኖርም
ይደረጋል፡፡ እርግማኑም ..በአንድ ዓመት ውስጥ ያቺን የተፈቀደችለትን አንድ ቃል ሳይናገር ከቀረ በሚቀጥለው
ዓመት አንድ ቃል ይጨመርለታል፡፡ በሁለተኛው ዓመት ላይ ሁለት ቃል መናገር ይችላል ማለት ነው፡፡ በሁለተኛው ዓመት
ምንም ቃል ካልተናገረ በሶስተኛው ዓመት ሶስት ቃል ይናገራል፡፡

  • የእንግሊዝ መንግስት በኢራን፣ በሊቢያና በታሊባን ተተችቷል

የኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን፤ የእንግሊዝን ሁከት ከግብፅ ጋር አያይዘው ዘግበዋል
በለንደን ኧሊንግ በተባለው አካባቢ የተጀመረው ነውጠኛ ሁከት (riot) ፤ ቅዳሜና እሁድ ተባብሶ ሰኞ እለት የከተማዋ ስምንት አካባቢዎችን አዳርሷል፡፡ ሰፈር ውስጥ ያገኙትን መኪና እየከሰከሱና እሳት እየለቀቁበት፤ ያጋጠማቸውን የንግድ ሱቅ ሰብረው እየገቡ ይዘርፋሉ - አይፎንና ብላክቤሪ ሞባይል ስልኮችን፤ ስኔከር ጫማና መነፅር፤ ሻምፑ እና መጠጥ ሳይቀር... ያገኙትን ከዘረፉ በኋላ ያጋዩታል፡፡

በግሪን ማውንት ፊልም ፕሮዳክሽን የቀረበውና ሰፊ ፊልም ፕሮዳክሽን የሰራው ..ያንቺው ሌባ.. ፊልም ሰኞ ማምሻውን በሐርመኒ ሆቴል ይመረቃል፡፡ ኤሪክ ጀንሰን እና ለምለም መኮንን በፕሮድዩሰርነት ያሠሩት ፊልም ደራሲና አዘጋጅ በላይ ጌታነህ ነው፡፡ በፊልሙ አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ፣ ሰይፈ አርአያ፣ ሳሃር አብዱልከሪም፣ ሰሎሞን ገብሬና ሌሎችም ተውነውበታል፡፡ የ108 ደቂቃ ርዝመት ያለው ፊልሙ በአምስት ወራት እንደተጠናቀቀ ማወቅ ተችሏል፡፡ ..ያንቺው ሌባ.. ከሰኞው ምርቃት ለላ ነገ በአዲስ አበባና በክልሎች ይመረቃል፡፡

Saturday, 13 August 2011 11:13

..ቡሄ.. በቶቶት ይከበራል

ቶቶት የባህል ምግብ አዳራሽ የቡሄ በአልን ባህልን በጠበቀ መልኩ እንደሚያከብር አስታወቀ፡፡ በዓሉ ወግና ልማድ ጠብቆ ለትውልድ እንዲተላለፍ የበኩላችንን እናደርጋለን ያለው ቶቶት፤ የቡሄ አጨፋፈር ትርዒት የሚያቀርብ ሲሆን የሙልሙል ገፀ በረከትም ነሐሴ 13 ቀን 2003 ዓ.ም. እንዳዘጋጀ ገልጿል፡፡ በዝግጅቱ ታዋቂ አርቲስቶች፣ ደራስያን፣ አትሌቶችና ሌሎች ታዋቂ ሰዎች ይገኛሉ ተብሏል፡፡

በደሳለኝ ስዩም የተዘጋጀው ..የጠረፍ ህልሞች.. ልቦለድ መሐፍ ታትሞ ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ 184 ገፆች ያሉት መሐፍ በ25 ብር ለገበያ የቀረበ ሲሆን በሦስት ሺህ ቅጂ የታተመው መሐፍ በረከትነቱን ለፀሐፊ ተውኔት ጌትነት እንየው አድርጓል፡፡ አዘጋጁ ካሁን ቀደም ..ደም የተፋ ብእር.. የሚል የግጥም መሐፍ ያሳተመ ሲሆን ባሁኑ ወቅት በአውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ላይ በአምደኝነት ይታወቃል፡፡በአካሉ ቢረዳ የተዘጋጁ ሁለት የትርጉም መፃህፍት ሰሞኑን ለንባብ በቅተዋል፡፡

በጥናት የተመረኮዘ የሬዲዮ ድራማዎችን በማዘጋጀት የሚታወቀው ፖፕሌሽን ሚዲያ ሴንተር ..ሥነ ሁፍ ለማህበራዊ ለውጥና እድገት የፖፕሌሽን ሚዲያ ሴንተር ልምድ.. የሚል መሐፍ አዘጋጅቶ ያሳተመ ሲሆን ይሄንኑ መሐፍ በመጪው ሐሙስ ይመረቃል፡፡ በግዮን ሆቴል አዋሽ አዳራሽ በሚካሄደው የምረቃና የማስተዋወቂያ መርሃ ግብር ካሁን በፊት በተለያዩ መድበሎች ሥራዎቻቸውን ያሳተመላቸው 32 አንጋፋና ወጣት ደራስያን እንዲሁም ሌሎች እንግዶች ይገኛሉ፡፡

በኢትዮጵያ፣ በእስራኤልና በአሜሪካ የሚኖሩ አድናቂዎቹና ወዳጆቹ ድምፃዊ ይርጋ ዱባለን የሚዘክር ኪነጥበባዊ ዝግጅት በጐንደር ከተማ ሊያቀርቡ ነው፡፡ በሚቀጥለው ሳምንት በከተማይቱ በሚቀርበው ዝግጅት የአርቲስቱ መገልገያ ቁሳቁሶች በአዲሱ ራስ ሚካኤል ስሁል ቤተመዘክር የሚቀርቡ ሲሆን ለዚህም የይርጋ ቤተሰቦች እና የጐንደር ከተማ ባህልና ቱሪዝም ህፈት ቤት ፈቃደኛ እንደሆኑ ታውቋል፡፡ በተጨማሪም ዘንድሮ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየውን ከያኒ አስመልክቶ ጥናታዊ ሁፍ፣ የፓናል ውይይትና የቅኔ ውድድር ይካሄዳል፡፡ ድምፃዊው በህይወት ሳለ የከተማዋ የደን መመናመን አሳስቦት ያቀነቀነውን ..ጐንደር እሹሩሩ.. የተሰኘ ዜማን ምክንያት በማድረግ የችግኝ ተከላ ይኖራል ተብሏል፡፡