Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62

ሶኖስ.. የተራቀቀ እና በአይነቱ የተለየ አዲስ ገመድ አልባ ስፒከር ሰርቶ ለገበያ ማቅረቡ ተገለ፡፡ በአዲሱ የሶኖስ |Pl¤Y: 3.. (Play: 3) ገመድ አልባ ስፒከሮች አንድ ዘፈን በሁሉም የመኖሪያ ቤት ክፍሎቻችን ውስጥ ማጫወት የምንችል ሲሆን በተለያዩ ክፍሎች ውስጥ የተለያዩ ሙዚቃዎችን መክፈትም እንችላለን፡፡

Sunday, 24 July 2011 07:13

ከሃዲ..

ለመሆን በቂ ምክንያት አለን?
..ስሜት.. እና ..ስሌት.. ሁለቱም ከአንዱ ናቸው
ቀደም ባሉት ሣምንታት እምነቴ የምክንያት ጥገኛ ባይሆንም ምክንያት አልቦ ያለመሆኑን አውርቻለሁ፡፡ የእምነቴ ማስረጃ በእጄ ያለው ቅዱስ መጽሐፍና በልቤ ውስጥ የሚላወሰው የባለታሪኩ መንፈስ እንደሆነ ገልጫለሁ፡፡

ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ሰው ወደ አንድ ልብስ ሰፊ ይሄዳል፡፡ ከዚያም፤
..ይሄውልህ ይሄን ምን የመሰለ ሙሉ ሱፍ እንደተሰፋ ገዝቼ እጅጌው ረዘመብኝ፡፡ ስለዚህ ይሄንን
እጅጌትንሽ እንድታሳጥርልኝ እፈልጋለሁ፡፡ ምን ይመስልሃል?.. ሲል ይጠይቀዋል፡፡..
ልብስ ሰፊውም፤ ..የለም ይሄ ማሳጠር ላያስፈልገው ይችላል፡፡ ዝም ብለህ ክንድህን እዚህ እክርንህ ጋ አጠፍ ማድረግ
ነው፡፡ አየኸው እጅጌህ ወደ ውስጥ እንደገባ?.. ይለዋል፡፡

አብዛኛው ኢትዮጵያዊ በኑሮና በመንፈስ ድህነት ውስጥ ተዘፍቆ የስቃይ ህይወትን የሚገፋ መሆኑ
ይዘገንናል፡፡ ነገር ግን፤ የአገሪቱችግር ከዚህም ይከፋል፡፡ በቁጭትተንገብግቦ ህይወትን ለመቀየር
ከመጣጣር ይልቅ፤ የኑሮ ችጋሩንና የመንፈስ ጉስቁልናውን እንደ ..ኖርማል.. ተቀብሎ መደንዘዝ... ከሁሉም የባሰ የጨለማ ህይወት ነው ማለት ይቻላል፡፡ በየአመቱ 200ሺ ገደማ ህፃናት በምግብ እጥረትና በበሽታ የሚሞቱበት አገርኮ ነው፡፡ ከዚህ ጋር ያልተያያዘ ትልቅና አሳሳቢ የኑሮ ወይም የመንፈስ ጥያቄ ሊኖረን አይችልም፡፡

የመንግስት መስሪያቤቶች በበዙበትና የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ በሚገኝበት ህንፃ ትናንት ከሰአት በኋላ በተከሰተ ከፍተኛ ፍንዳታ በርካታ ሰዎች ሳይሞቱ እንዳልቀረ የተሰጋ ሲሆን፤ ብዙም ሳይቆይ ጠ/ሚሩ ንግግር ያሰሙበታል ተብሎ ይጠበቅ በነበረ የፖለቲካ ፓርቲ ስብሰባ ላይ አንድ ታጣቂ በተኩስ እሩምታ በርካታ ወጣቶችን ገደለ፡፡

Saturday, 16 July 2011 12:50

..ስልቻ ተበላሸ..

..ምኑጋ..
..ሲነፋ..
..ሲነፋ አይደለም፤ መጀመሪያ ሲገፈፍ ነው!..
አንድ ሰውዬ ሚስቱ የመስማት ችሎታዋ ከቀን ቀን እየደከመ በመምጣቱ በጣም ይጨነቃል፡፡ ስለዚህ ወደሀኪም
ሄዶ ምክር መጠየቅ አስፈላጊ መሆኑን ያምንበታል፡፡
አንድ ቀን ወደ ሐኪም ይሄድና እንዲህ ሲል ÃSrÄL-
..ዶክተር፤ አንድ ትልቅ ችግር ገጥሞኝ ነው የመጣሁት..
ዶክተሩም፤
..ምን ችግር ገጠመህ?..
ሰውዬው፤
..ባለቤቴ የመስማት ችግር እንዳለባት አውቅ ነበር..
..እሺ?.. ዶክተሩ በጥሞና ያዳምጣል፡፡

የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ESOG የእናቶችን ሞት ለመቀነስ የሚረዱ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ነድፎ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ ከዚህም መካከል አፋጣኝ የሆነ እና ሁሉንም አገልግሎት ያካተተ የማህጸን ሕክምና በመላው አገሪቱ ከትላልቅ ሆስፒታሎች ራራቅ ባሉ አካባቢዎች እንዲሰጥ የሚያስችለው (Comprehensive Emergency Obstetric and New Born care)  የተሰኘው ፕሮጀክት አንዱ ነው፡፡

አቶ ተስፋዬ ታሪኩ፤ የመኢአድ ዋና ፀሐፊ
4.5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ህዝብ ተጨማሪ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልገው በመንግስት ቢነገርም፤ ቁጥሩ ይህ ብቻ ነው የሚል እምነት የለኝም፡፡ አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ በብልሹ የኢኮኖሚ ፖሊሲ፣ በሙስናና በአላስፈላጊ ወጪዎች ለችግር ተዳርጓል፡፡ ተጨማሪ የምግብ እርዳታ የሚባለው መጀመሪያ ምን ተገኝቶ፣ ምን ተበልቶ ነው? አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ የእለት ጉርስ አጥቶ፤ በሃገሪቱ ታሪክ እጅግ የከፋ ድህነት ላይ ደርሷል፡፡

አቶ ተመስገን ዘውዴ፤ የአንድነት የፋይናንስ ጉዳይ ኃላፊ
ዜጎች ለረሃብ የሚጋለጡት፣ በአጋጣሚና በአንድ ሌሊት በተፈጠረ ችግር ሰበብ አይደለም፡፡ ባለፈው ዓመት የተከሰተው ርሃብ ከዘንድሮው ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ ዘላቂ መፍትሔ ሊያገኝ የሚገባው ነገር ነው፡፡ ድርቅን ለመቋቋምና ወገኖቻችን በረሃብ አደጋ ላይ እንዳይወድቁ ለማድረግ መንግስት ዘላቂ መፍትሔ የማመቻቸት ኃላፊነት አለበት፡፡ ያለፈው ዓመት ሁለት ሚሊዮን ህዝብ ተጨማሪ የምግብ እርዳታ እንደ¸ÃSfLgW ተነግሮ ነበር፡፡ ዘንድሮ ቁጥሩ ጨምሯል፤ ወደ 4.5 ሚሊዮን፡፡ ከዚህም በተጨማሪ 8 ሚሊዮን ህዝብ በሴፍቲ ኔት እርዳታ እየታቀፈ እንደሆነ ተነግሮናል፡፡ ዘላቂ መፍትሄ ያስፈልጋል፡፡

አቶ ሙሼ የኢዴፓ ሊቀመንበር
ድርቅ የተፈጥሮ ጉዳይ ነው፤ ይሁን እንጂ ድርቅ በተከሰተበት አገር ሁሉ ረሃብ ይፈጠራል ማለት አይደለም፡፡ በቂ ክትትልና ዝግጅት ቢኖር ኖሮ፤ ድርቅ የዜጎችን ህይወት እንዳይፈታተን ማድረግ ይቻላል፡፡ በአገራችን ግን፤ በድርቅ ምክንያት ብዙ ወገኖቻችን የረሃብ ተጠቂ ሆነዋል፡፡ መንግስት ከመናገሩ በፊት፤ ከተለያዩ የውጭ መገናኛ ብዙሃን ድርቅና ረሃብ እንደተከሰተ ስንሰማ ቆይተናል፡፡ ይህም፤ በመንግስት በኩል ትኩረት ሳይሰጠው እንደቆየ የሚያሳይ ነው፡፡ የችግሩ ምንነት ቀድሞ እንዲታወቅ በማድረግ፤ ችግር ሳይባባስ መፍታት ይገባ ነበር፡፡