Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 08 October 2011 10:10

ጥሪ አይቀበልም” እና “የማልተኛው “ፊልሞች ይመረቃሉ”

Written by 
Rate this item
(0 votes)

“ጥሪ አይቀበልም” እና “የማልተኛው” ፊልሞች ዛሬ እና ነገ በአዲስ አበባና በሌሎች ከተሞች ይመረቃሉ፡፡
“ጥሪ አይቀበልም” በዩሊያን ተክለማርያም የተፃፈ ሲሆን በሚሊዮን ስዩም ተዘጋጅቶ ፕሮዱዩስ ተደርጓል፡፡ በ99 ደቂቃ ልብ አንጠልጣይ ፊልሙ ላይ መስፍን ኃይለኢየሱስ (ጠጆ)፣ ፊዮሪ ኃይሌ፣ ኤልሳቤጥ ጌታቸው (ቀጮ)፣ ሚካኤል ታምሬ፣ ዳንኤል ወንድወሰን እና እና ሌሎችም ተውነዋል፡፡ ፊልሙን ሰርቶ ለማጠቀቅ አንድ አመት ከስድስት ወር የፈጀ ሲሆን ከሥራ የተፈናቀሉ ወጣቶች በአቋራጭ ለመበልፀግ የሚያደርጉትን ውጣ ውረድ ያሳያል፡፡

“ጥሪ አይቀበልም” በአዲስ አበባ ዮፍታሔ፣ እምቢልታና ሴባስቶፖል ሲኒማዎች እንዲሁም በደብረዘይትና በናዝሬት በነገው እለት የሚመረቅ ሲሆን በዋነኛነት ከቀኑ 8 ሰዓት በሲኒማ ዮፍታሔ እንደሚመረቅ ለማወቅ ተችሏል፡፡ እስኩፒ ፊልም ፕሮዳክሽን ከሆቢላንድ ፒክቸርስ ጋር ተባብሮ በማዘጋጀት ያቀረበው “የማልተኛው” ድራማቲክ ኮሜዲ ፊልም ዛሬ ከቀኑ 8፡30 በአዲስ አበባ ትያትርና ባህል አዳራሽ ያስመርቃል፡፡ ያሬድ ተስፋዬ ጽፎ ባዘጋጀው የ96 ደቂቃ የቤተሰብ ፊልም ላይ እነ ችሮታው ከልካይ፣ ወንድወሰን አውራሪስ፣ ሕይወት ግርማ፣ ትዕግስት ረጋሳ፣ ቢኒያም እሸቱ (ጀቤሳ) ይተውኑበታል፡፡

 

Read 4128 times Last modified on Saturday, 08 October 2011 10:13