Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 15 October 2011 12:14

የብርትኳን ደጀኔ ሥዕሎች ለአውደርእይ ይታያሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በቁም ነገር መጽሔት ላይ በምትስላቸው የገፀ ሰብ ካርቱን ስእሎች ታዋቂነትን ያገኘችው ሰዓሊ ብርትኳን ደጀኔ ሥዕሎች እና ካርቱኖች ለአውደርእይ ቀረቡ፡፡ በመጪው ሐሙስ ከቀኑ 10፡30 በአምስት ኪሎው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተመዘክር የቀረቡት ስእሎች “Reflection” በሚል ርእስ ነው፡፡ አውደርእዩ ለአንድ ሳምንት ለሕዝብ እይታ ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡ 58 ሥዕሎችና ካርቱኖች ለአውደርዕዩ ቀርበዋል፡፡
አምና የአሜሪካ አምባሳደር ዶናልድ ቡዝ በኤምባሲአቸው አማካይነት ባዘጋጁት “አራቱ ነፃነቶች” በሚል ርእስ ባዘጋጁት የሥዕል ውድድር ሰዓሊ ብርትኳን ከአሸናፊዎቹ አንዷ ሆና የገንዘብ ሽልማት መሸለሟ ይታወሳል፡፡ በሌላም በኩል የፎቶግራፈር ሙሉጌታ አየነ 25 ፎቶ ግራፎች አወድርእይ በአልያንስ ኢትዮፍራንሴ ትናንት የተከፈተ ሲሆን እስከ ጥቅምት 18 ለሕዝብ ክፍት ሆነው ይቆያሉ፡፡ ፎቶግራፈሩ “የካፒታል” የእንግሊዝኛ ጋዜጣ ባልደረባ ሲሆን የዘንድሮውን የውጭ ጋዜጠኞች ማህበር ሽልማት ማሸነፉ ይታወቃል፡፡

Read 3408 times