Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 15 October 2011 12:15

የወጋየሁ ልጅ ፍርድ ቤት ልትሄድ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ከጋብቻ ውጭ ተወልጄአለሁ የምትለው የታዋቂው ተዋናይ ወጋየሁ ንጋቱ ልጅ አንጋፋው አርቲስት ከሞተ ከ21 ዓመታት በኋላ የወጋየሁ ንጋቱ ልጅነቴ በሕግ ይረጋገጥልኝ በማለት ፍርድ ቤት ልትሄድ ነው፡፡ ልጅነቴን የብሔራዊ ትያትር የሥራ ባልደረቦቹ ያረጋግጡልኛል፤ የዘረመል (DNA) ምርመራ ለማድረግም ዝግጁ ነኝ ስትል አስተያየቷን ለዝግጅት ክፍላችን የሰጠችው ዲያና ወጋየሁ ንጋቱ የሕግ ባለሙያ እያማከረች መሆኑን ገልፃ፤ የፍርድ ቤት ቅድመ ሁኔታዎች እስኪሟሉ በመገናኛ ብዙሃን የተቻላትን ጥረት በማድረግ የአርቲስቱ ልጅነቷን እንደምታስተዋውቅ ተናግራለች፡፡ ባለትዳር የሆነችው ወ/ሮ ዲያና የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤት የጠቅላላ አገልግሎት ክፍል ባልደረባ ስትሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር ባልደረባ ከሆነችው እናቷ ወ/ሮ ማሜ ኃይለስላሴና ከአርቲስት ወጋየሁ መወለዷን ገልፃ አሁን በሕይወት የሌሉት እናትየው አባትነቱን ለማረጋገጥ በሕግ ከመጠቀማቸው በፊት አሁን በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ባልረቦቻቸው እንደከለከሏቸው እንደነገሯት ጠቅሳ፤ ይህ ግን መቆም አለበት ብላለች፡፡ ወጋየሁ በሞተበት ወቅት የወራሽነት ተቃውሞ እናትየው ለፍርድ ቤት እንዳታቀርብ እነዚሁ ባልደረቦች ሥምና ዝናውን እንጠብቅለት በማለት እንደተከላከሉ የነገረችን ዲያና፤ አሁን ልጅነቴ ይታወቅልኝ እንጂ ውርስ አልጠይቅም ብላለች፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር ባልደረባ የሆነው አርቲስት ወጋየሁ ንጋቱ፤ ከዚህ ዓለም በሞት የለየው ሕዳር 6 /1982 ዓ.ም ሲሆን ወ/ሮ ማሜም በ1997 ዓ.ም አርፈዋል፡፡
የአርቲስቱን ቤተሰቦች አስተያየት ለማካተት ያደረግነው ጥረት ስልኮቻቸው ጥሪ ባለመቀበላቸው አልተሳካም፡፡

Read 4761 times Last modified on Saturday, 15 October 2011 12:17