ይኸው ዳግም ተጠርቼ፣
ልቤ ልብህ ውስጥ ተገኘ፡፡
መስቀሌ ብዙ ነው
በመስቀል ብዛት፣
ጌታ እበልጥሃለሁ፡፡
ዕረፍትን አላውቅም፡፡
እስከ ዕውቀቴ ድረስ፣
ዕድሜዬን በሙሉ፣
ተንጠልጥዬ አለሁ፡፡
እንዳንተ ደፍሬ፣
መሞት እያቃተኝ፣
ጐልጐታዬ በዝቶ፣
ሁሌ እሰቀላለሁ፡፡
ነፍሴን አልሰጥ ብዬ፣
እንዳልኖር ቁስሉ፣
እንዳልሞት ድፍረቱ፣
ደስታ እያናጠቡኝ፣
የታመመ ኑሮ፣
ሠርክ እቀጥላለሁ፡፡
መኻልነት ለምዶኝ፣
ሳልደፍር ሳልፈራ፣
ሳይዘልቀኝ ሚስማሩ፣
ትንሣኤ ከየት ይምጣ?
ፈርሠው ካልተሠሩ!
ፍቅር ፈቀደ