ጀግናው አትሌት ሻምበል ምሩፅ ይፍጠርን ህይወት ለመደገፍ የፊታችን ሐሙስ በሸራተን አዲስ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ተዘጋጀ፡፡
ከመንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎች ከባለሃብቶችና ከተለያዮ ባለሙያዎች የተዋቀረ አንድ ኮሚቴ ከቢ.ኤም.ዲ ፕሮሞሽን ጋር ገቢ ማሰባሰቡን ሲያስተባብር ቆይቷል፡፡ በሸራተን አዲስ ላሊበላ አዳራሽ የሚካሄደውን ፕሮግራም በ450ሺ ብር አቶ አብነት ገ/መስቀል ብር ስፖንሰር ማድረጋቸው ሲገለፅ ከፍተኛ ባለስልጣናት፤ ክቡር ዶ/ር ሼህ መሀመድ አሊአል-አላሙዲን፤ ባለሃብቶች፣ ታዋቂ ሰዎች፣ አትሌቶችና የሚመለከታቸው አካላት በሚገኙበት ልዩ ዝግጅቱ እንደሚካሄድም ታውቋል፡፡
Published in
ስፖርት አድማስ