Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 12 January 2013 10:04

“የእማዋዬ እንባ” ረዥም ልብወለድ ለንባብ በቃ “አነበብካት” እየተነበበ ነው

Written by 
Rate this item
(19 votes)

የደራሲ ገስጥ ተጫኔ ስድስተኛ የልቦለድ ሥራ የሆነው “የእማዋዬ እንባ” ለንባብ በቃ፡፡ “የመከራ ዘመን ወግ” የሚል ስያሜ የነበረው መፅሃፉ፣ባለሙያዎች አስተያየት ከሰጡ በኋላ ያሁኑ ርዕስ እንደተሰጠው ለማወቅ ተችሏል፡፡
በኢትዮጵያ ደራስያን ማህበርና በብርሃንና ሰላም ድርጅት የሕትመት ተዘዋዋሪ ሂሳብ የጋራ አስተዳደር የታተመው መጽሐፉ፣278 ገፆች ያሉት ሲሆን በ45 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

ደራሲ ገስጥ ተጫኔ ካሁን ቀደም ዘነበ ፈለቀ በሚል ርእስ “ነበር” የተሰኘ ባለ ሁለት ክፍል መጽሐፍ፣ እንዲሁም “የናቅፋው ደብዳቤ”፣ “እናት ሀገር”፣ “የፍቅር ቃንዛ”፣ “የማክዳ ንውዘት” እና “የረገፉ ቅጠሎች” የተሰኙ መጻሕፍት ለንባብ አብቅተዋል፡፡ ደራሲው ከአዲስ አድማስ ጋር ባደረጉት የስልክ ቃለ ምልልስ ለሕትመት ዝግጁ የሆኑ ሌሎች መጻሕፍት እንዳሉዋቸውና በማሳተሚያ ገንዘብ እጥረት ሊያሳትሙት እንዳልቻሉ ገልፀዋል፡፡
በሌላ በኩል ደራሲ አብዱልበር ነስሮ የፃፈው “አነበብካት” የረዥም ልቦለድ መጽሐፍ ታትሞ ሰሞኑን ለንባብ ቀረበ፡፡
በፒስ ፕሪንቲንግ ፕሬስ ታትሞ ለንባብ የበቃው ባለ 166 ገፅ መጽሐፍ ዋጋ 49.99 ብር ነው፡፡
አብዱልበር ካሁን ቀደም “የቼዝ ምድር” የተሰኘ የግጥም እና የአጭር ልቦለድ መድበል አሳትሟል፡፡

Read 16983 times