በደራሲ ኢንጂነር ግርማይ ኃይል ተፅፎ የተዘጋጀው “ሴት የላከው” የ97 ደቂቃ ፊልም ባለፈው ማክሰኞ የተመረቀ ሲሆን በእለቱ በነበረው የኤሌክትሪክ ሃይል መዋዥቅ የተነሳ ፊልሙ ሙሉ በሙሉ ባለመታየቱ በድጋሚ እንደሚመረቅ ቶኔቶር ፊልም ፕሮዳክሽን አስታወቀ፡፡ በእለቱ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር መሰል ችግር ስላልነበር ሙሉ ፊልሙን አሳይተናል ያሉት የፕሮዳክሽኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ግርማይ ኃይሌ፣ፊልሙ በታየባቸው ሶስት ቦታዎች ግን በኤሌክትሪክ ሃይል መዋዠቅ የተነሳ ለ58 ደቂቃ ብቻ ለማሳየት መገደዳቸውን ተናግረዋል፡፡