Print this page
Saturday, 19 January 2013 15:01

የቻይና የአንድ ልጅ ፖሊሲ እጣፈንታ

Written by  ኤልሳቤጥ እቁባይ
Rate this item
(1 Vote)

የቻይና ኮሙኒስት ፓርቲ መስራች ማኦ ዜዱንግ በስልጣን ዘመናቸው መጀመሪያ የማንኛውም አይነት የቤተሰብ ምጣኔ ተቃዋሚ ነበሩ፡፡ የወሊድ ቁጥጥር አገሮችን በማዳከም ለጥቃት እንዲጋለ ለማድረግ በካፒታሊስቶች የተ- ነሰሰ ሴራ ነው የሚል አቋም ነበራቸው ቿ ዜዱንግ፡ ፡ ቻይናውያን በተቻለ መ-ን በብዛት ልጅ እንዲወልዱ ይበረታቱ በነበሩት በማኦ የስልጣን ዘመን የቻይና ህዝብ ቁጥር በእጥፍ ጨምሮ ነበር፡፡ አንድ ህፃን ሲወለድ አፍ ብቻ ሳይሆን ሁለት የሚሰሩ እጆችም አብረውት ይወለዳሉ፣ በምድር ላይ ካሉ ነገሮች በሙሉ የሰው ልጅ ክቡር ነው፡ የሚሉት ማኦማንኛውም አይነት የወሊድ መከላከያ ወደ አገራቸው እንዳይገባም አግደው እንደነበር ይታወቃል፡፡ የህዝብ ብዛትን ለጦርነት መመከቻ አድርገው ይ-ቀሙበት የነበሩት ማኦ ሰሜን ኮሪያ ላይ ያዘመቱት የህዝብ ማእበል በታሪክ ሁሌም ተ-ቃሽ ነው፡፡ በስልጣን ዘመናቸው ማብቂያ ላይ የህዝብ ብዛት ምጣኔ ላይ የፖሊሲ ለውጥ ያመት ማኦ፣ የህዝብ ብዛትን ለመቀነስ ሴቶች ዘግይተው እንዲወልዱ ማበረታታት ጀመሩ፡፡ ቻይና ከማኦ ሞት በኋላ የህዝብ ብዛቷን ለመቀነስ የተለያዩ ሙከራዎችን ስታደርግ የቆየች ሲሆን በመጨረሻም በአንድ ልጅ ፖሊሲ በመናት፣ የህዝብ ቁጥሯን ውታማ በሆነ መልኩ ለመቀነስ ችላለች፡፡ የአንድ ልጅ ፖሊሲ የመጀመሪያዎቹ ልጆች የሰላሳ አራት ዓመት ጎልማሶች የሆኑባት ቻይና የአረጋውያን ቁጥር ከወጣቶቿ ጋር ከፍተኛ ልዩነት በማምጣቱ በያዝነው አመት በፖሊሲው ላይ ለውጥ እንደምታደርግ እየተነገረ ነው፡፡ ከሰሞኑ ቻይና ዴይሊ እንደዘገበው የቻይና አረጋውያን ቁጥር እየጨመረ የወጣቱ ቁጥር ደግሞ በአንድ ልጅ ፖሊሲ በመገደቡ ረታ በሚወጣው እና አዲስ በሚተካው የሰው ሀይል መካከል ከፍተኛ ክፍተት እየተፈ-ረ መጥቷል፡፡ የአንድ ልጅ ፖሊሲውን ተከትሎ ወላጆች ንብረታቸውን ለወንድ ልጆች ማውረስ ስለሚፈልጉ ሴት ልጅ ስትረገዝ በሚፈፀም ውርጃ ምክንያት የፆታ አለመመጣ-ኑም ከፍተኛ ደረጃ ላይ በመድረሱ በያዝነው አመት የአንድ ልጅ ፖሊሲ ላይ ለውጥ ሊደረግ ይችላል ብሏል፡፡ የቻይና የህዝብ የተፈጥሮ እና የአካባቢ ጥበቃ ኮሚቴ ባቀረበው ሀሳብ፣ በተለይ በከተማ የሚኖሩ ወላጆች፣ ሁለተኛ ልጅ እንዲወልዱ ሊፈቀድላቸው ይገባል ብሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት ሁለት ልጅ እንዲወልዱ የሚፈቀድላቸው በአንድ ልጅ ፖሊሲ የተወለዱ ወላጆች ብቻ ናቸው፡፡

የፔኪንግ ዩኒቨርሲቲ የሶስዮሎጂ ፕሮፌሰር እና የቤተሰብ ምጣኔ ኮሚሽነር ሉ ጂዮሀ እንደሚሉት፣ በቻይና እየጨመረ የመጣው የአረጋውያን ቁጥር በአዲስ የሰራተኛ ኃይል ሀይል ካልተተካ የኢኮኖሚ እድገቱ አደጋ ላይ ይወድቃል፡፡ በሁለቱ ፆታዎች መካከል ያለው ከፍተኛ ክፍተትና ከጊዜ ወደ ጊዜ እጅግ እየጨመረ የመጣው የሌላ አገር ዜጋ፣ ቻይና የአንድ ልጅ ፖሊሲዋ ላይ ለውጥ እንድታደርግ አስገድዷታል፡፡ ተንታኞች እንደሚሉት፣ የወጣቶች ቁጥር መቀነስ ኢኮኖሚውን ክፉኛ ይጎዳዋል፡፡ ቻይና ይህን ፖሊሲ ካልለወ-ች ጫናውን በቅርቡ ታየዋለች፡፡ በቻይና የሚገኙ የትላልቅ ፋብሪካ ባለቤቶች ከፍተኛ የሰው ሀይል እጥረት እየገ-ማቸው እንደሆነ ሪፖርት ማድረግ ከጀመሩ ሰነባብተዋል፡፡ የፖሊሲ ለውጥ ስለመኖሩ ቁርጥ ያለ አስተያየት ያልሰት የአገሪቱ ፕሬዚዳንትፖሊሲው እንደሚላላ -ቁመዋል፡፡ የቻይና የልማት እና የምርምር ፋውንዴሽን ደግሞ ከ2015 ጀምሮ አገሪቱ ወደ ሁለት ልጅ ፖሊሲ እንድትገባ ሀሳብ አቅርቧል፡፡ በመላው ቻይና የአንድ ልጅ ፖሊሲን የሚያበረታቱ ማስታወቂያዎች አሁንም ጎላ ብለው እንደተሰቀሉ  ናቸው -ቻይና የቤተሰብ ምጣኔ ያስፈልጋታል፣ ዘግይቶ መውለድ አስፈላጊ ነው (ሽበታም ሴት አዲስ የተወለደ ህፃን ታቅፋ ከሚያሳይ ምስል ጋር)፣ የቤተሰብ ቁጥርን በመመ-ን ለቀጣይ ትውልድ ያስተላልፉ፡ ወዘተ የሚሉ፡፡ በተደጋጋሚ የህዝብ ቁጣ በመቀስቀሳቸው ምክንያት እንዲወርዱ የተደረጉ ማስታወቂያዎችም አሉ፡፡ጥቂት ህፃናት በዛ ያሉ አሳማዎችን ያሳድጉ፡ የሚለውናአንድ ልጅ ማለት አንድ ተጨማሪ መቃብር ማለት ነው፡ የሚሉት ይገኙበታል፡፡ የቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎት ሀላፊዎች የኮሚኒስት ፓርቲ ሀላፊዎች ሲሆኑ ከአንድ በላይ ልጅ በወለዱም ሆነ ባረገዙ ሰዎች ላይ የፈለጉትን ውሳኔ ማሳለፍ ይችላሉ፡፡

ሴቶች በግድ እንዲያስወርዱ ወይም መካን እንዲሆኑ የመወሰን ስልጣንም አላቸው፡ ፡ ከባድ ቅ-ትም መጣል ይችላሉ፡፡ ፖሊሲው ተግባራዊ ከተደረገ ከሰማኒያዎቹ ዓመታ ጀምሮ ባሉት አመታት የቻይና መንግስት በቅጣት የሰበሰበው ገንዘብ ከ314 ቢሊዮን ዶላር በላይ መሆኑ ይነገራል፡፡ ጥንዶች ከማርገዛቸው በፊት የነሱን ፈቃድ ማግኘት አለባቸው፡፡ ለዚህም የጋብቻ ሰርተፊኬታቸውንና የመኖሪያ ፈቃዳቸውን እንዲሁም ሴቷ ቢያንስ ሀያ ወንዱ ደግሞ ሀያ አራት አመት እንደሞላቸው ማሳየት አለባቸው፡፡ ከሀላፊዎቹ የተጣለባቸውን ቅጣት ያልፈፀሙ ሰዎች አሳማዎቻቸውን፣ ከብቶቻቸውንና ቤታቸውን እንዲሁም ልጆቻቸውን ሊነ-ቁ ይችላሉ፡፡ ሀላፊዎቹ ፖሊሲው መጣሱን ለማየት በየጊዜው ያለመታከት ይቆጣ-ራሉ፡፡ ፖሊሲውን መተግበር የተለያዩ ጥቅማጥቅሞችን ያስገኛል፡፡ የተወለደው ህፃን አስራ አራት አመት እስኪሞላው የደሞዝ +ማሪ፣ ከወለድ ነፃ ብድር፣ የረታ ፈንድ፣ ማዳበሪያ በርካሽ ዋጋ፣ የተሻለ ቤት፣ የና አገልግሎት እና ትምህርትን የመሳሰሉት ማበረታቻዎች ሲሰጥ ከሀያ አምስት አመት እድሜያቸው በኋላ ለሚወልዱ ሴቶች ደግሞ ረዘም ያለ የወሊድ ፈቃድ በተጨማሪ ይሰጣቸዋል፡፡ የጥቅማጥቅሞቹ ተ-ቃሚዎች ፖሊሲውን ከጣሱ ያገኟቸውን መብቶች ይነ-ቃሉ፡፡ እ.አአ በ2008 . በሲችዋን ግዛት በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ልጆቻቸው የሞቱባቸው ወላጆች በ2011. ነው ልጆች እንዲወልዱ የተፈቀደላቸው፡፡ ጥናቶች እንደሚያመለክቱት፣70.7 በመቶ የሚሆኑ የቻይና ሴቶች ተጨማሪ ልጆች መውለድ ይፈልጋሉ፡፡ ፖሊሲው የህዝብ ብዛትን በመቀነስ ከፍተኛ ሚና የተጫወተ ቢሆንም አካላዊ መንፈሳዊ እና ማህበራዊ ቀውሶችን ማስከተሉ አልቀረም፡፡ ሁለተኛ ልጅ አርግዛ የተገኘች ለመውለድ የተቃረበች ሴት ሳትቀር ንሱን በግድ እንድታስወርድ መገደዷና ሴቶችን ያለፍላጎታቸው መካን እንዲሆኑ ማድረግ ከፍተኛ የና እና የስነልቦና ቀውስ በሴቶቹ ላይ መፍ-ሩ ከሴቶች መብት ጋር የተያያዙ በፖሊሲ ማስፈፀም ስም እየተተገበሩ ያለ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ናቸው፡፡ ፆታን መሰረት ያደረገ ውርጃም በተመሳሳይ ከሴቶች መብት ጋር ተያይዞ ጥያቄ ውስጥ የሚገባ ሲሆን የዩኒሴፍ የቻይና ተወካይ እንዳሉት፣ የአንድ ልጅ ፖሊሲ ለህፃናት ሴቶች ብዙ ለውጦችን አምጥቷል፡፡ ነገር ግን ሴቷ መጀመሪያ ከተወለደች ብቻ ነው፡፡ በገ-ራማ ቻይና የሚኖሩ ቻይናውያን ለእርሻ ስራ ወንድ ልጅ የግድ ስለሚያስፈልጋቸው የመጀመሪያ ልጃቸው ሴት ከሆነች ሁለተኛ ልጅ መሞከር ይችላሉ፡፡

አንድ ሴት መንትዮች ካረገዘችና ማሳደግ የምትችል ከሆነም ከቅጣት ነፃ ናት፡፡ ሁለቱም ወላጆች ወንድም እና እህት ከሌላቸውም ሁለት ልጆች መውለድ ይፈቀድላቸዋል፡፡ የሚጣልባቸውን ቅጣት መክፈል የሚችሉ ጥንዶች ደግሞ ፖሊሲውን ይጥሳሉ፡፡ ምንም እንኳን የኮሚኒስት ቻይና ፓርቲ አባል የሆኑ ባለስልጣናት ፖሊሲውን ሲተላለፉ ሊቀ ቢችሉም ባለስልጣን በማወቅ ብቻም ከአንድ በላይ ልጅ ሊወልዱና ለከፋ ችግር ላይዳረጉ ይችላሉ፡፡ ለባለስልጣናት ጉቦ መስ-ት እና በህክምና ከአንድ በላይ ልጅ መውለድም ሌሎቹ ፖሊሲውን በመተላለፍ ከአንድ በላይ ልጅ ለመውለድ የሚያስችሉ መንገዶች ናቸው፡፡ በአለማችን በህዝብ ብዛት ቀዳሚ የሆነችው ቻይና፣ ከሰላሳ አመት በላይ የተከተለችው የአንድ ልጅ ፖሊሲ፣ ለሰው ሀይል እጥረት ሊዳርጋት እንደሚችል መረጃዎች እያመለከቱ ባሉበት በአሁኑ ሰአት፣ የፖሊሲ ለውጥ ማድረጓ አይቀሬ እንደሆነ እየተነገረ ነው፡፡ ብዙ ውዝግቦችን ያስተናገደውና ቀላል የማይባል ወጪ የወጣበት የአንድ ልጅ ፖሊሲ እጣ ፈንታ ምን ይሆን? ቻይናውያን በወንድምና እህት፣ በአክስትና አጎት ይንበሸበሹ ይሆን?

Read 7142 times