Saturday, 19 January 2013 15:04

ጋዜጠኞች ምን ይላሉ?

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(7 votes)

ወደ ደቡብ አፍሪካ ከሚጓዙ 25 ጋዜጠኞች መካከል በአራት አጭር ጥያቄዎች የቀረበ መጠይቅ በማቅረብ የሚከተሉትን ምላሾች አግኝቷል፡፡ አራቱ ጥያቄዎች ከዚህ በታች የቀረቡት ሲሆን የስፖርት ጋዜጠኞቹ ምላሻቸውን በቅደምተከተል እንዲህ መልሰዋል
1. በ29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለጋዜጠኞች የተፈጠረው እድል ምን ምን ስሜት ፈጠረብዎ? 2. የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከ31 ዓመታት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ በማለፉ ምን ተሰማዎት? በቀጣይ የአፍሪካ ዋንጫዎች ለመሳተፍ ምን ይደረግ?

3. በ29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ምን ውጤት ይጠብቃሉ?
4. በምድብ 3 የኢትዮጵያን ውጤት ይገምቱ ሀ. ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ለ.ኢትዮጵያ ከቡርኪናፋሶ ሐ.ኢትዮጵያ ከናይጄርያ
1. የስፖርት ጋዜጠኞች ላደረጉት ጥረት ጥሩ ምላሽ ነው፤ ፊታቸውን አውሮፓ ላይ ብቻ ያደረጉትም ለሀገር ውስጥ ትኩረት እንዲሰጡ የሚያበረታታ ነው፡፡
2. በስፖርት ጋዜጠኝነት ህይወቴ ከገጠመኝ ትልቅ ደስታዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ አሁን ካለው እንቅስቃሴ ጐን ለጐን Grass root level ላይ መስራት ያስፈልጋል፡፡
3. Surprising team ይሆናል፡፡ በእርግጠኝነት ሩብ ፍፃሜ እንደርሳለን፡፡ ሳንታሰብ ግማሽ ፍፃሜም ልንደርስ እንችላለን፡፡
4. ሀ.2 - 1 ለ.1 - 0 ሐ.0 - 1
ምስጋናዉ ታደሰ ከፕላኔት ስፖርት

1. ጋዜጠኛና የዚህን መሠሉ ዕድል ባለቤት ሆነው ማየትን ለዘመናት አጥብቄ እመኝ ነበር፡፡ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ለጋዜጠኞችና ለሙያተኛው ዋጋና ክብር ሠጥቶ የዚህ ዕድል ባለቤት እንዲሆኑ የልምድና የዕውቀት ሽግግር እንደያግዝ ትልቅ በር የሚከፍት ነው፡፡ የፌዴሬሽኑ አመራር ሊመሰገን ይገባል፡፡
2. ስፖርት ወዳዱ ህዝባችን ይሄንን ቀን አጥብቆ ሲናፍቀው ቆይቷል፡፡ ይሄ የዘመናት ህልማችን ዕውን ሆኖ ማየቴ እንደ አንድ ጋዜጠኛ ብቻ ሣይሆን እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ትልቅ ደስታ ተሰምቶናል፡፡ ቁም ነገሩ ለውድድሩ አንድ ጊዜ ማሳያ ብቻ ሣይሆን ቀጣይነቱ እንዲኖረው ብዙ መሥራት ነው፡፡
3. ብሄራዊ ቡድናችን በውድድሩ ጥሩ ተፎካካሪ ከመሆን በዘለለ የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ዙር ያልፋል፡፡
4 .ሀ.1 - 0 ለ.2 - 1 ሐ.1 - 2
ይስሐቅ በላይ ከሀትሪክ የስፖርት ጋዜጣ

1. ከምንም በላይ ኢትዮጵያ ከ31 አመት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ታላቅ ነገር ነው፡፡ ይሄን ሁኔታ ተከትሎ እግር ኳስ ፌዴሬሽኑ በታሪክ ተሰምቶ በማይታወቅ ሁኔታ ለ26 ጋዜጠኞች ሙሉ ወጪያቸውን ሸፍኖ ለመውሰድ የተደረገውን የመጀመሪያ ጥረት በእጅጉ አደንቃለሁ፡፡ አለም ሰገድ ሰይፉ የሊግ ስፖርት ጋዜጣ አሳታሚና ማኔጂንግ ኤዲተር  በቀጣይነትም ለሀገሪቱ ስፖርት ቁልፍ ሚና ያላቸውን ጋዜጠኞች በዚህ አይነቱ ውድድር ላይ እንዲጋበዙ ቢደረግ የተሻለ ነው እላለሁ፡፡

2. በጣም ታላቅ ደስታ ነው የተሰማኝ፡፡ የስፖርት ቤተሰቡን ስሜት ፈንቅሎ የወጣው የሀገሪቱን የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ ለተተኪ ስፖርተኞች የሚፈጥረው ተነሳሽነት የጐላ በመሆኑ የሀገሪቱን ማለፍ የላቀ ትርጉም ይሰጠዋል፡፡ በቀጣይነት ጠንክሮ መስራት ያስፈልጋል፡፡
3. የብሄራዊ ቡድን ተጨዋቾች አሁን ካላቸው ተነሳሽነት አንፃር በደቡብ አፍሪካው ዋንጫ ያልተጠበቀ ውጤት በማስመዝገብ የአፍሪካ የስፖርት ቤተሰብ የሚያስደንቅ ነገር የሚያመጡ ይመስለኛል፡፡
4. ሀ.0 - 0 ለ.1 - 0 ሐ.1 - 1
አለም ሰገድ ሰይፉ የሊግ ስፖርት ጋዜጣ
አሳታሚና ማኔጂንግ ኤዲተር
/*******************************8

1. ዕድሉ መፈጠሩ መልካም ነው የስፖርት ጋዜጠኞችም ለሀገር ውስጥ ስፖርት ትኩረት እንዲሰጡም ያበረታታል፡፡ ነገር ግን የጉዞ ሂደቱን ለማሳጠር በፌዴሬሽኑ በኩል ብዙ መሰራት ነበረበት፡ ፡ አሰልቺና መንገላታት የበዛበት ነበር፡፡
2. ለአሁኑ ትውልድ የመጀመሪያ ታሪክ ነው - ከረዥም ጊዜ በኋላ የተገኘ ተሳትፎ መሆኑ ያስደስታል፡ ፡ እግር ኳሳችን አደገ ለማለት ግን ተሳትፎው ተከታታይነት ያለው እንዲሆን ያስፈልጋል፡፡ ለተሳትፎም የዘለለ ውጤት ያስፈልጋል፡፡ ፌዴሬሽኑም ለዚህም የሚያበቃ የእግር ኳስ ልማት መስራት፣ ፕሮጀክቶችና ክለቦችን ማጠናከር ተገቢ ይመስለኛል ፡፡
3.ከረዥም ጊዜ በኋላ የመጣ ተሳትፎ እንደመሆኑ ሩብ ፍፃሜ መግባት መቻልን እንደ ትልቅ ውጤት እቆጥረዋለሁ፡፡ ምድቡን ነጥብ ይዞ ማጠናቀቀ መቻልም መልካም ነው እላለሁ፡፡ ሀ.1-1 ለ.2 - 1 ሐ.0 - 1
ሰለሞን ያለው ከሬድዮ ፋና  
/**********************88

1. በርካታ የስፖርት ጋዜጠኞች ውድድሩን እንዲዘግቡ ዕድል መመቻቸቱ ጥሩ ነው፡፡ ሆኖም በሂደቱ ላይ በተለይ በቪዛ ላይ ጋዜጠኞቹ ብቻቸውን መከታተላቸው አሰልቺና ተስፋ አስቆራጭ ነበር፡፡ በዚህ በኩል ፌዴሬሽኑም ሆነ መንግስት ሊያግዛቸዉ ይገባል፡፡
2. በዚህ ትውልድ ይህ ዕድል መገኘቱ ሁሉንም ያስደሰተ ነው፡፡ መታሰብ ያለበት ግን ስለቀጣይነቱ መሆን አለበት፡፡ በአጭር ማጣሪያ ለዚህ መድረስ ቢቻልም ቀጣዮቹ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያዎች ከባዶች ይሆናሉ፡፡ ዘለቄታና ከስር መሰረቱ የጠነከረ ስራ መስራት አለበት፡፡
3. ሩብ ፍፃሜ ድረስ ይዘልቃል የሚል ግምት አለኝ፡፡
4. ሀ.1 – 0 ለ.0 - 0 ሐ.0 - 2 ታምሩ አለሙ ከዛሚ አገሬ ስፖርት

/********************

1. በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ አንደኛ ምዕራፍ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን ጋዜጠኛውም ላለፉት አመታት ያላገኘውን ወርቃማ ዕድል በማግኘቱ ወርቃማ አጋጣሚ ነው፡፡
2. ባላዝንም ብዙ አልተደሰትኩም፡፡ ምክንያቱም በቅተን፤ አውቀን ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብናልፍ በነገው ጨዋታ ስጋት አይገባንም ነበር፡፡ በቀጣይ አድምቶ ከሥር ጀምሮ መሥራት ያስፈልጋል፡፡ 3. የመጀመሪያውን ዙር የማለፍ አቋም ያለው ይመስላል፡፡ ካልሆነ ግን የሊቢያው የ1974 ውጤት ይደገማል ብዬ እገምታለሁ፡፡ በተለይ ከዛምቢያ የምናደርገው ጨዋታ ለቀጣይ ውጤት አመላካች ይሆናል፡፡
 4. ሀ.1 - 1 ለ.2 - 1 ሐ.0 - 3
ማንደፍሮ ለማ ከኢቴቪ ስፖርት
/*****************
1. ዕድሉ በጣም የሚበረታታና በተለይ ለስፖርት ጋዜጠኞቹ ወደፊት ለሚሰሩት ሥራም ከፍተኛ መነቃቃት የፈጠረ ነው፡፡
2. እንደ ዜጋ ደስታ እንደ ባለሙያ ደግሞ ባለፉት ጥቂት ወራት በተሰሩት ሥራዎች እዚህ ከተደረሰ ወደፊት የበለጠ ነገሮች ሊመጡ እንደሚችሉ ያሳየ ነው፡፡ ለወደፊቱም እንቅስቃሴው በተጠናከረ መልኩ ከቀጠለ የአህጉር የየጊዜው ተሳታፊ መሆናችን አይቀርም፡፡
3. የመጀመሪያውን ምድብ ማጣሪያ ማለፍ በቂ ነው!
4. ሀ.1 - 1 ለ.2 - 1 ሐ.1 - 2
ሙሉነህ ተስፋዬ ከዘ-ገነርስ የስፖርት ጋዜጣ

/*********************
1. እድሉ በጣም ጥሩ ነው ግን ውጣ ውረዱ በሙሉ ወደ ጋዜጠኛው ስለመጣ ትንሽ አድካሚ ሆኗል፡፡
2. በጣም ደስታ ፌሽታ
3. ግማሽ ፍፃሜ 4. ሀ.1 - 0 ለ.2 - 1 ሐ.0 - 0
ፍስሐ ይድነቃቸው ከኢቢኤስ ቴሌቭዥን

Read 5204 times Last modified on Saturday, 19 January 2013 15:30