Sunday, 20 January 2013 12:45

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና እነ አንዱዓለም አራጌ በድጋሚ ተቀጠሩ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(1 Vote)

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና እነ አንዱዓለም አራጌ በድጋሚ ተቀጠሩ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት በሽብርተኝነት ወንጀል ተከሰው የዕድሜ ልክ፣ የ25 ዓመትና የ18 ዓመት እስራት የተፈረደባቸው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ አንዱአለም አራጌ፣ ናትናኤል መኮንን እና ክንፈ ሚካኤል አበበ የይግባኝ ክርክራቸውን አጠናቀው ለትናንት ተቀጥረው የነበረ ቢሆንም ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውሳኔውን ለአንድ ወር አራዝሞታል፡፡

ውሳኔው ለአንድ ወር የተራዘመበትን ምክንያት የዕለቱ ዳኛ አቶ ዳኜ መላኩ ሲገልፁ፤ በአንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት) የባህርዳር አመራር የሆኑት አቶ አንዱአለም አያሌውና ሻምበል የሺዋስ ይሁንዓለም በስር ፍ/ቤት የተከሰሱበትና የተቀጡበት መዝገብ ከእነ አንዷለም አራጌ ጋር አንድ ቢሆንም ይግባኝ የጠየቁት ግን በተለያየ መዝገብ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡ በዚህም ምክንያት በሌላ መዝገብ የይግባኝ ጥያቄያቸውን ያቀረቡት እንደ አንዱዓለም አያሌውም ባለፈው ሰኞ ታኅሣሥ 6 ቀን ቀርበው ለየካቲት 8 መቀጠራቸውን ገልፀዋል፡፡ በመሆኑም ሁሉንም የይግባኝ አቤቱታዎች መርምሮ በአንድ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ይቻል ዘንድ ለየካቲት 8 ቀን 2005 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥተዋል፡፡

 

Read 3047 times Last modified on Sunday, 20 January 2013 13:28