Print this page
Saturday, 09 February 2013 12:42

የቼኾቭ 153ኛ የልደት በዓል በሙዚቃ ዝግጅት ይከበራል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የሩሲያዊው ሐኪምና ደራሲ የአንቶን ቼሆቭ 153ኛ የልደት በዓል የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 11 ሰዓት ጀምሮ በፑሽኪን አዳራሽ በሙዚቃ ዝግጅት እንደሚከበር የሩስያ የሳይንስና የባህል ማዕከል አስታወቀ፡፡ በዕለቱ የሩስያ የፒያኖ እና የኦፔራ ሙዚቀኞች ናታሊያ ኮርሹኖቫ እና አሌክሲ ፓርፌኖቭ ሥራዎቻቸውን ለታዳሚው  ያቀርባሉ ተብሏል፡፡“ሥነፅሁፍ ውሽማዬ ሕክምና የሕግ ሚስቴ” ይል የነበረው ሩስያዊው ሐኪምና ደራሲ አንቶን ቼሆቭ፣ ሩስያ ካፈራቻቸውና ሥራዎቻቸው በዓለም ዙርያ ከናኙ የአጭር ልቦለድ ፀሐፍት አንዱ ነው፡፡ የሰኞ አመሻሹ ዝግጅት በሩስያ የባህላዊ ሻይ አፈላል (ሳሞቫር) የሚታጀብ ሲሆን ለታዳሚዎች የሻይ ግብዣ እንደሚኖር የባህል ማዕከሉ ጠቁሟል፡፡

Read 3615 times
Administrator

Latest from Administrator