Saturday, 09 March 2013 12:55

ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የሕፃናት መጻሕፍት ያስመርቃል

Written by 
Rate this item
(4 votes)

ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ዛሬ ሁለት የሕፃናት መፃሕፍት እንደሚያስመርቅ አስታወቀ፡፡ ዛሬ በጣይቱ ሆቴል የሚመረቁትን መፃሕፍት ነዋሪነቱን በሩስያ ይኖር የነበረው ኢትዮጵያዊ ደራሲ ዶ/ር ማይክል ዳንኤል አምባቸው ነው፡፡ ሁለቱ መፃሕፍት ሲመረቁ የደራሲው ልደትም እንደሚታሰብ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡ እያንዳንዳቸው አርባ ገጽ የሆኑት የሕፃናት የተረት መጻሕፍት “The Giant pineapple” እና “Muna’s Monkey” ሲሆኑ የመፃሕፍቱ ሥዕሎች በጃፓናዊት አርቲስት እንደተሰሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡

የሁለቱም መፃህፍት ዋጋ 33 ብር ነው፡፡ ደራሲው በሕፃናት ላይ ያተኮሩ አስራ አምስት መፃሕፍትን ጽፏል፡፡ በሌላም በኩል “የአህዛብ ጣዖታት” የተሰኘ የግጥም መጽሐፍ ነገ እንደሚመረቅ የኢትዮጵያ ደራስያን ማህበር አስታወቀ፡፡ በአቶ ዳንኤል መንገሻ የተገጠሙ ግጥሞችን የያዘው መጽሐፍ የሚመረቀው በሀገር ፍቅር ትያትር ትንሿ አዳራሽ ነው፡፡

Read 4261 times