Saturday, 09 March 2013 12:57

ለአቡነ ማትያስ አራት ክፍለ ዘመን ያስቆጠረ መጽሐፍ ተበረከተላቸው

Written by 
Rate this item
(3 votes)

ባለፈው እሁድ በዓለ ሲመታቸውን አከናውነው ስድስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን ፓትርያርክ የሆኑት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፤ አራት ክፍለ ዘመን ያስቆጠረ የኢትዮጵያ ታሪክ መጽሐፍ ተበረከተላቸው፡፡ ለፖርቱጋል መንግስት ይሰራ በነበረው ስፔናዊ ፔድሮ ፓያሽ በ1622 ዓ.ም በፖርቱጋልኛ ታትሞ በቅርቡ ወደ እንግሊዝኛ የተተረጎመውን የግእዝ አንቀፆች ያሉት መጽሐፍ፤ በቅድስት ሥላሴ ቤተክርስትያን ተገኝተው ለፓትርያርኩ በስጦታነት ያበረከቱት በኢትዮጵያ የፖርቱጋል አምባሳደር አንቶኒዮ ሉዊስ ኮትራም ናቸው፡፡

በሁለት ጥራዝ የተካተተውን የታሪክ መጽሐፍ ከፖርቱጋልኛ ወደ እንግሊዝኛ ለመተርጎም ስምንት አመታት የፈጀ ሲሆን በለንደን የታተመው መጽሐፍ ዋጋ 100 ፓውንድ ነው፡፡ መጽሐፉ ወደ እንግሊዝኛ ሲመለስ የፖርቱጋል ኤምባሲ የባህል አታሼና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፖርቱጋሊኛ አስተማሪዎች ዶር. ኢዛቤል ቦቫዲያ፣ ማኑኤል ዣዎ ራሞስ እና ሄርቭ ፔናክ የአርትኦት ሥራውን ሠርተዋል፡፡ በሁለት ጥራዝ 900 ገፅ ያለው መጽሐፍ የወቅቱን የኢትዮጵያ አስተዳደር፣ ሃይማኖት፣ አለባበስ፣ እንስሳት … የያዘ ኢትዮግራፊክ መጽሐፍ ነው፡፡ የመጽሐፉ አዘጋጅ ፔድሮ ፓየዝ በአፄ ሱሱንዮስ እና አፄ ፋሲል ዘመነ መንግስት የመጣ የካቶሊክ ሐይማኖት ቄስ ነው፡፡

Read 3983 times