Saturday, 16 March 2013 10:54

“የሠራተኞቻችንን ቃለምልልስ ሳታካትቱ በሠራችሁት ዘገባ አዝነናል”

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የካቲት 23 ቀን 2005 ዓ.ም “በኢንዲያን ኢንተርናሽናል ት/ቤት የተማሪዎች ወላጆች ቅሬታ አቀረቡ” በሚል ርዕስ በወጣው የአዲስ አድማስ ዘገባ ላይ ት/ቤቱ ቅሬታውን በደብዳቤ ገልጿል፡፡ ት/ቤታችን ከተመሠረተበት እ.አ.አ ከ2006 ጀምሮ ከተማሪ ቤተሠቦች እና ከባለድርሻ አካላት የተመሠገነ መልካም ስም ያገኘ ሆኖ ሣለ፤ ሚዛን ያልጠበቀ ዘገባ በምናከብረው ጋዜጣችሁ ማቅረባችሁ ሃላፊነት የጐደለው ሆኖ አግኝተነዋል ሲሉ የት/ቤቱ ዳይሬክተር ሃሳባቸውን ገልፀዋል፡፡ በአጠቃላይ የወላጆችን ቅሬታ እንጂ የሠራተኞችን ምላሽ ሳያካትት በወጣው ዘገባ ቅሬታ ተሠምቶናል ይላል ደብዳቤው፡፡

Read 3200 times