የንባብ ባህልን ማበረታታት ዓላማው አድርጎ መጋቢት 7 ቀን 2002 ዓ.ም ፕሮግራሙን የጀመረው “ብራና” የሬዲዮ ፕሮግራም ሦስተኛ ዓመቱን ነገ በ8 ሰዓት በጣይቱ ሆቴል ጃዝ አምባ አዳራሽ ሲያከብር፣የሙዚቃ ተመራማሪው አርቲስት ሠርፀ ፍሬስብሃት “ለንባብ ባህል መዳበር የመንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ሚና” በሚል ርእስ ጥናቱን ያቀርባል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት “የኢትዮጵያውያን የንባብ ልምድ በሀገር ውስጥና በባህር ማዶ” በሚል ርእስ አስተውሎቶቹን በቃለ ምልልስ መልክ እንደሚያቀርብ ይጠበቃል፡፡ በ “እናት ማስታወቂያ” እየተዘጋጀ በኤፍ ኤም አዲስ 97.1 የሚቀርበው የሬዲዮ ዝግጅት ዘወትር እሁድ ከምሽቱ 2 ሰዓት እስከ 4 ሰዓት በሚተላለፈው እያንዳንዱ ዝግጅት ላይ ጥያቄ ለሚመልሱ 10 አድማጮች መፃሕፍት እየሸለመ መሆኑን አዘጋጆቹ አስታውቀዋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል