Monday, 08 April 2013 10:05

“ታይፎይድን በደቂቃዎች ሚመረምር መሣሪያ ለውጥ ያመጣል”

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ዩኒቨርሳል ክሊኒክ የታይፎይድ በሽታን መርምሮ ውጤቱን በ37 ደቂቃዎች ውስጥ ለማረጋገጥ የሚያስችል መሣሪያ ማስመጣቱን የገለፀ ሲሆን፤ በታይፎይድ ህክምና ላይ በመላ አገሪቱ ይታዩ የነበሩ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል መሆኑን የክሊኒኩ ሃኪም ተናግረዋል፡፡ በአገራችን ውስጥ በስፋት ሲያገለግሉ የቆዩ መሳሪያዎች ሁለት ጉድለት እንደነበረባቸው ዶ/ር ምክሩ ጠቅሰው፤ ምርመራው ፈጣንና አስተማማኝ አልነበረም ይላሉ፡፡ የታይፎይድ ባክቴሪያ በሰውነት ውስጥ እንዳለና እንደሌለ በፍጥነት ለማረጋገጥ የሚደረገው ምርመራ አስተማማኝ ስላልነበረ የተሳሳተ ውጤት ያመላክት ነበር ብለዋል፡፡

“ቀድሞ የነበረው መሣሪያ በሽታው ሣይኖር አለ ብሎ የሚያመላክትበት አጋጣሚ ስለነበር፤ ህመምተኛው ተገቢውን የህክምናና የመድሃኒት አገልግሎት በተገቢው መንገድ ጥርት ያለ ምርመራ ለማድረግም “Blood Culture” በሚባል የምርመራ ዓይነት ናሙናዎች ተወስደው ውጤቱን ከሣምንት በላይ መጠበቅ ግድ ነበር የሚሉት ዶ/ር ምክሩ፣ በሽተኛው እስከዚያ ድረስ ጉዳት ይደርስበታል ብለዋል፡፡ ክሊኒኩ አዲስ ያስመጣው መሣሪያ ትክክለኛውን የህክምና ውጤት በደቂቃዎች ውስጥ ከማሣወቁም በላይ በምርመራው ሂደት ይፈጠሩ የነበሩ ስህተቶችን ሙሉ ለሙሉ የማስወገድ አስተማማኝ መሳሪያ ነው ብለዋል - ዶ/ር ምክሩ፡፡

Read 2787 times