አንጋፋና ወጣት ከያንያን የግጥም፣ የቅንጭብ ትያትር፣ የወግና ሌሎች የኪነጥበብ ሥራዎቻቸውን በጃዝ ሙዚቃ ታጅበው የሚያቀርቡበት “ግጥም በጃዝ” ሃያ አንደኛ ዝግጅት የፊታችን ረቡዕ ከቀኑ 11፡30 ሰዓት እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ ገለፁ፡፡ ባሁኑ ዝግጅት ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ፣ ሞገስ ሀብቱ፣ ምስራቅ ተረፈ፣ በረከት በላይነህ፣ ግሩም ዘነበ ግጥሞቻቸውን ሲያቀርቡ፣ ወ/ሮ ሰሎሜ ታደሰ ዲስኩር እንዲሁም ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ወግ ያቀርባሉ፡፡