Monday, 08 April 2013 11:42

“የጥበብ ዋርዲያ” ሥራ ሊጀምር ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ፊልሞች በህገወጥ መንገድ እንዳይገለበጡና እንዳይሰረቁ የሚከላከል “የጥበብ ዋርድያ” የተሰኘ ሶፍትዌር መስራቱን የገለፀው ሴባስቶፖል ሲኒማ፤ ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ ሥራ ላይ እንደሚውል ሰሞኑን አስታወቀ፡፡ ሶፍትዌሩ ፊልም ሰሪዎች ፊልም በሚያሳዩ ወቅት “ይሰረቅብኛል” ከሚል ስጋት ያድናቸዋል ተብሏል፡፡

ባለፈው ረቡዕ በሴባስቶፖል ሲኒማ መግለጫ የሰጡት ሶፍትዌሩን ያዳበሩ ባለሙያዎች እንዳሉት፤ ሶፍትዌሩ አንድ ፊልም በሕገወጥ መንገድ ሳይገለበጥ በአንድ ጊዜ ብዙ ቦታ እንዲታይ ያስችላል ብለዋል፡፡ ፊልሙ ስንት ጊዜ እንደታየ ጭምር ለማወቅ ያስችላል የተባለው ሶፍትዌር፤ ፊልሞቹን በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ በማስቆለፍ ከስርቆት ስጋት ነፃ እንደሚያወጣ ተገልጿል፡፡

Read 2813 times