Saturday, 20 April 2013 12:31

“ግጥም በጃዝ” ረቡዕ ይቀጥላል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ባለፈው ሚያዝያ 2 መቅረብ የነበረበትና ታዳሚዎች በሥፍራው ከተገኙ በኋላ የተቋረጠው “ግጥም በጃዝ” በመጪው ረቡዕ እንደሚቀጥል አዘጋጆቹ አስታወቁ፡፡ ቅድመ ዝግጅት አጠናቀን ልናቀርብ ከተዘጋጀን በኋላ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ተቆጣጣሪ አካል ፈቃድ የላቸውም በማለቱ ስለሌላቸው አያቀርቡም በሚል ለራስ ሆቴል ዝግጅቱ መቋረጡን ተናግረዋል፡፡ ረቡዕ ከቀኑ 11 ሰዓት በሚቀጥለው “21ኛው ግጥምን በጃዝ” ዝግጅት ላይ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ፣ ሞገስ ሀብቱ፣ ምስራቅ ተረፈ፣ በረከት በላይነህ፣ ግሩም ዘነበ በግጥም፤ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በወግ ይሳተፋሉ፡፡

Read 2421 times