Saturday, 20 April 2013 12:42

“ጋይድ መጋዚን” በነፃ እየተሰራጨ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ኢትዮጵያን ለሚጐበኙ የውጭ ሀገር ጐብኚዎች የሚያገለግል የመምሪያ መጽሐፍ አሳትሞ ማሰራጨት መጀመሩን “ኬር ኤዢ ኢትዮጵያ” አስታወቀ፡፡ በእንግሊዝኛ እና በእስፓኒሽ ቋንቋ የታተመው የጐብኚዎች መምሪያ መጽሐፍ ግማሽ ሚሊዬን ብር ወጥቶበታል ያሉት አዘጋጆቹ፤ መጽሐፉ ኢንዱስትሪውን ቢያነቃቃም በውጭ ሀገር ታትሞ ወደሀገር ሲገባ የመንግስት ተቋማት አላበረታቱንም ብለዋል፡፡ አብዛኞቹን ማስታወቂያዎችም በነፃ ያሳተሙ መሆናቸውን ለዝግጅት ክፍላችን ተናግረዋል፡፡

በwww.ker_ezhiethiopia.com የሚገኘው መጽሔት 20ሺህ ቅጂ የታተመ ሲሆን ቅጂው ከራስ ሆቴል እና ሌሎች ትልልቅ ሆቴሎች በነፃ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 2727 times