Saturday, 27 April 2013 11:56

“ፔን ኢትዮጵያ” በትርጉም ሚና ዙሪያ ይወያያል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ሥነ ጽሑፍን፣ ነፃ የሀሳብ መንሸራሸርንና የንባብ ባሕልን በማጐልበት የሚንቀሳቀሰው ፔን ኢትዮጵያ፤ ሁለተኛውን የፀሐፍት ጉባዔ ዛሬ በጣሊያን የባሕል ማዕከል ሊያካሂድ ነው፡፡
የጉባኤው ጭብጥ “የትርጉም ሚና ለኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍ እድገት” በሚል ሲሆን፤ ምሁራን ጥናታዊ ጽሑፎቻቸውን እንደሚያቀርቡና ውይይት እንደሚደረግባቸው ተገልጿል፡፡
በጉባኤው ላይ የፔን አባላት የሆኑ ገጣሚያን፣ ፀሐፊ ተውኔቶች፣ ልብወለድ ፀሐፊዎች፣ ጋዜጠኞችና ሌሎች የሥነ ጽሑፍና የሚዲያ ቤተሰቦች ታዳሚ ሲሆኑ የኖርዌይና የጣሊያን ፔን ፕሬዚዳንቶችን በእንግድነት ይገኛሉ፡፡

 

Read 2434 times