Saturday, 04 May 2013 11:16

የህክምና ማስረጃ - ፍትህን ለማግኘት

Written by  ፀሐይ ተፈረደኝ (ከኢሶግ)
Rate this item
(3 votes)

የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ለተፈጸመባቸው ሴቶች የህክምና ማስረጃ መስጠት እና በመረ ጃው የህግ ተጠቃሚነት ምን ይመስላል በሚል ዶ/ር ብርሀኑ ከበደ ያደረጉት አንድ ጥናት እን ደሚጠቁመው አስገድዶ መድፈር የወሲብ ጥቃትን ማድረስ እንደመሆኑ ለስነተዋልዶ ጤና መጉ ዋደል የሚያደርስ ነው፡፡ ዶ/ር ብርሀኑ ጥናቱን ያደረጉት በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለከ ከተማ ዎች ሲሆን ለናሙና ጥናት የተመረጡትም ወደ 244 የሚሆኑ ሰዎች ናቸው፡፡

አዲስ አበባ 10 ክፍለከተማዎች ያሉዋት ሲሆን የህዝቡዋም ቁጥር 2739551 እንደሚደርሰ በ2007 እንደአው ሮፓውያኑ አቆጣጠር የተደረገ ጥናት ያስረዳል፡፡ በጥናት ወረቀቱ ላይ እንደተመለከተው ፡- 44 በመቶ የሚሆኑ ሴቶች በሕይወት ዘመናቸው የወሲብ ጥቃት ይፈጸመባቸዋል፡፡ ከአምስት ሴቶች አንዱዋ በ21 አመት እድሜ ለዚህ ጥቃት ልትጋለጥ እንደምትችል ያስረዳል፡፡ በወሲብ ከተጠቁት ሴቶች መንከል 50 በመቶ ያህል ለህግ ሪፖርት የተደረገላቸወ ናቸው፡፡

ምንም አንኩዋን በተናጠል የሚወሰድ እርምጃ ወደ ውጤት የማያደርስ ቢሆንም ጥቃቱን ያደረሱ ሰዎች በህግ እርምጃ ሲወሰድባቸው ተጎጂዎቹ እንደሚረኩ ሁኔታዎች ያስረዳሉ፡፡ የወሲብ ጥቃት ከደረሰባቸው ከ10-30 በመቶ የሚደርሱት ሴቶች ጉዳይ በህግ ሽፋን ተሰጥቶታል፡፡ ተገዶ መደፈር በሚያጋጥምበት ጊዜ ከህግ ክፍሎች ለሚቀርበው ጥያቄ የህክምና ማስረጃ መስጠት ግድ ሲሆን ከዚህም ባለፈ በአንል ቀርቦ የማስረዳት ግዴታም ከህክምናው ባለሙያ ይጠበቃል፡፡ የወሲብ ጥቃት የተፈጸመባቸው ሴቶች የሚደርስባቸው ጉዳት አንላዊ ብቻ ሳይሆን ስነልቡናዊና አእምሮአዊ ችግርም ሊደርስባቸው ይችላል፡፡ ነገር ግን ጥቃት አድራሹ በህግ ፊት ቀርቦ የጥፋቱን ያህል ብይን ሲያገኝ ማየት ለተጠቂዎቹ እርንታን እንደሚሰጥ አያጠራጥርም፡፡

በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በሌሎችም አገሮች እንደሚታየው ተገደው ለተደፈሩ ሴቶች የሚሰጠወ የህክምና ማስረጃ ብዙ ጊዜ አጠያያቂ የሚሆንት አጋጣሚ ይስተዋላል፡፡ በተለይም ጥቃቱ የተፈጸመባቸው ሕጻናት ሲሆኑ በፍጥነት መረጃውን ወደሐኪም የሚያደርሰው ሰው ስለማይኖር በመታጠብ እንዲሁም ቀናትን በመቁጠር ምክንያት ሊታይ የሚገባው መረጃ ስለሚጠፋ ለፖሊስ የሚሰጠው ምላሽ የቆየ የሚል ይሆናል፡፡ በዚህም ምክንያት ቤተሰብም ሆነ የህግ ክፍሉ ግልጽ የሆነ ምላሽን ስለማያገኙ ለውሳኔው እንደሚቸገሩ እሙን ነው፡፡ ነገር ግን የወንድ የዘር ፈሳሽ ከአቸውም ይሁን ከልብሳቸው ላይ ሳይጠፋ የደፈረው ሰው ማን እንደሆነ ሊታወቅ ይችላል፡፡

Read 3679 times