Saturday, 18 May 2013 11:37

የወንድ የዘር ፍሬ ... ሊታጠብ ይችላል

Written by 
Rate this item
(21 votes)
  • በሰብ ሰሃራ አፍሪካ በጥንዶች መካከል በአማካኝ እስከ 15ኀ በመቶ የሚሆኑት የኤችአይቪ ውጤታቸው የተለያየ ሆኖ ይገኛል፡፡
  • በብዙ ጥናቶች እንደሚታየው ሴቶች 60 ወንዶቹ 40 ኤችአይቪ ፖዘቲቭ ሆነው ይገኛሉ፡፡
  • ሳይንቲስቶችንም ግራ በሚያጋባ ሁኔታ ጥንዶች ውጤታቸው አንዳቸው ፖዘቲቭ አንዳቸው ደግሞ ኔጌቲቭ ይሆናሉ፡፡

በዚህ እትም ለንባብ የበቃው የአንድ ተሳታፊን ጥያቄ መሰረት ያደረገ ጉዳይ ነው፡፡ ለጥያቄው ማብራሪያ እንዲሰጡ የጋበዝናቸው ዶ/ር እያሱ መስፍን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሕክምና ፋክልቲ መምህር እና የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስት ናቸው፡፡ ቀጥሎ የምታነቡት ተሳታፊዋ የላኩትን ጥያቄ ነው፡፡ ውድ ኢሶጎች... .....እኔ ኤች አይ ቪ ፖዘቲቭ ስሆን ባለቤ ግን ኔጌቲቭ ነው፡፡እኔ እስከአሁን ድረሰ ምንም የኤችአይቪ መድሀኒት ተጠቃሚ አይደለሁም ፡፡ የግብረስጋ ግንኙነት የምንፈጽመውም በኮንዶም ነው፡፡ ነገር ግን ልጅ ለመውለድ በጣም ስላማረኝ አንድ ነገር አሰብኩ፡፡ ይኼውም ከግንኙነት በሁዋላ በኮንዶም ውስጥ ያለውን የዘር ፈሳሽ ባለቤ ወደእኔ ማህጸን ውስጥ እንዲያፈሰው እና ማርገዝ እንድችል ነው፡፡

ነገር ግን የፈለግነውን ነገር ከማከናወናችን በፊት መጠየቅ የምፈልገው... በጠቆምኩት መንገድ ሙከራ ብናደርግ ልጅ ማርገዝ እችላለሁ? ልጅ ማርገዝ ብችልስ ምን ያህል ጤናማ ይሆናል? ልጅ ከአረገዝኩ በሁዋላ የፀረ ኤችአይቪ መድሀኒት ተጠቃሚ መሆን ይጠበቅብኛል? ለእነዚህ ጥያቄዎች እና ተያያዥ ለሆኑት ሁሉ መልስ እንደማገኝ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ .. ዶ/ር እያሱ መስፍን ከአሁን ቀደም ለዚሁ እትም የባለትዳሮችን በኤችአይቪ ቫይረስ ውጤት መለያየት በሚመለከት መልስ ሰጥተዋል፡፡ .....ከጥንዶች ወይም ከባለትዳሮች መካከል አንዳቸው ፖዘቲቭ ሌላኛው ደግሞ ኔጌቲቭ በመሆን የኤችአይቪ ውጤት መለያየት ሲኖር በእንግሊዝኛው ዲስኮርዳንስ ይባላል፡፡ይህ በአሁኑ ጊዜ በጥንዶች መካከል ቁጥሩ እየጨመረ የመጣ ነው፡፡

በተለይም በሰብ ሰሃራ አፍሪካ በጥንዶች መካከል በአማካኝ እስከ 15ኀ በመቶ የሚሆኑት የኤችአይቪ ውጤታ ቸው የተለያየ ሆኖ ይገኛል፡፡ ጥንዶች በጋር እየኖሩ የተለያየ ውጤት የሚኖርበት ምክን ያት የተለያየ ነው፡፡አንዱ በቅርብ ጊዜ የተጋቡ ከሆኑ ወይንም አንዱ ፖዘቲቭ ሆኖ ገና ወደሌላው እስኪተላለፍ በሚወስደው ጊዜ ምክንያት ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ለረጅም ጊዜ በትዳር አብረው እየኖሩም አንዱ ፖዘቲቭ ሌላው ደግሞ ኔጌቲቭ የመሆን ነገር ይታያል፡፡ በኤችአይቪ የመያዝ ሁኔታ ከሰው ሰውም ይለያያል፡፡ አንዳንዶች በቫይ ረሱ ያለመያዝ ሁኔታ ሲታይባቸው ሌሎች ደግሞ ቶሎ የመያዝ ሁኔታ ይኖራቸዋል፡፡ እንደገናም በደም ውስጥ ያለው የቫይረስ መጠንም ቁጥሩ ከፍ ያለ ከሆነ ወይንም ብዙ ቆይቶ ብዙ የተጎዳ ከሆነ ለመተላለፍ ከፍ ያለ እድል ይኖረዋል፡፡

የኤችአይቪ መድሀኒት ሙሉ በሙሉ በትክክል የሚወስዱ ሆነው ነገር ግን ሳይከላከሉ ወይንም በኮንዶም ሳይ ጠቀሙ የወሲብ ግንኙነት የሚያደርጉ ከሆነ አሁንም ቫይረሱ የመተላለፍ እድል ይኖረ ዋል፡፡ ነገር ግን በተለያዩና በማይታወቁ ምክንያቶች ለሳይንቲስቶችም ግራ በሚያጋባ ሁኔታ ጥንዶች አንዳቸው ፖዘቲቭ አንዳቸው ደግሞ ኔጌቲቭ ሆነው አብረው ይኖራሉ፡፡ አብረው በሚኖሩ ጥንዶች በአማካኝ ከአንድ መቶ እስከ ሁለት መቶ ግንኙነት ውስጥ በአንዱ ኤችአይቪ ቫይረስ እንደሚተላለፍ ይገመታል፡፡ ስለዚህም ጥንዶች ምንም ኮንዶም የማይጠቀሙ ከሆነ በአመቱ መጨረሻ ከመቶው አስሩ በቫይረሱ ሊያዙ ይችላሉ፡፡ ይህን ንም ለመከላከል በማንኛውም ጊዜ በወሲብ ግንኙነቱ ወቅት ኮንዶም እንዲጠቀሙ ግድ ነው፡፡..... ኢሶግ፡ የዘር ፈሳሽን ከኮንዶም ወደማህጸን በማስገባት ማርገዝ ይቻላልን? ዶ/ር ኢያሱ፡ ይህ ጥያቄ የብዙዎች ከኤችአይቪ ጋር የሚኖሩ ሰዎች ጥያቄ ነው፡፡

የወንድ የዘር ፍሬ መቅስቈቂ ሰስቁቁ በተፈጥሮው ጭራ ያለው መዋኘት ወይንም መንቀሳቀስ የሚችል ነው፡፡ ስለዚህም ምቹ ሁኔታ ከተፈጠረለት ካለበት ስፍር ዋኝቶ በመንቀሳቀስ እርግዝና እንዲፈጠር ያስችላል፡፡ ለምሳሌ ሙሉ በሙሉ ወሲባዊ ግንኙነት ሳይፈጸም ወይንም ክብረንጽህና ሳይገሰስ በብልት አካባቢ የዘር ፈሳሹ በመፍሰሱ ብቻ እርግዝና የሚከሰትበት አጋጣሚ አለ፡፡ ስለዚህ በኮንዶም ውስጥ የፈሰሰ የዘር ፈሳሽ ወደማህጸን የሚገባበት አጋጣሚ ከተፈጠረ ማርገዝ ይቻላል፡፡ ነገር ግን ወደ ጠያቂዋ ሁኔታ ስንመለስ ወሲባዊ ግንኙነት የምትፈጽመው በኮንዶም ሲሆን ኮንዶም የተዘጋጀው ደግሞ ባብዛኛው እርግዝ ናን ለመከላከል ሲሆን በሚሰራበት ጊዜ በወንድና በሴት ዘር መካከል እንዳይገናኙ እንደግድግዳ ከመከላከል በተጨማሪ የሚጨመርበት የኬሜካል ውሁድ አለ፡፡ እነዚህ ኬሚካሎች የወንዱን የዘር ፍሬ መዋኘት እንዳይችል ወይንም እንዳይንቀሳቀስ በማድረግ አቅሙን የማዳከም ስራ ይሰራሉ፡፡

ስለዚህ በዚህ መልክ የተጠራቀመው የዘር ፈሳሽ ውጤታማ ላይሆን ይችላል፡፡ በእርግጥ ማርገዝ ከተቻለ በሚረገዘው ልጅ ጤና ላይ ምንም የሚያስከትለው ጉዳት ወይንም የጤና ችግር የለም፡፡ ኢሶግ፡ የወንድም ይሁን የሴት የዘር ፍሬ ከፈሰሰ በሁዋላ ምን ያህል የቆይታ እድሜ ይኖረዋል? ዶ/ር ኢያሱ፡ የወንድና የሴት የዘር ፍሬዎች ቆይታ ይለያያል፡፡ ከግንኙነት በሁዋላ የወንዱ የዘር ፈሳሽ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ በመዋኘት ከማህጸን በር አልፎ ከማህጸን ቱቦ ይደርሳል፡፡ ሁኔታዎች ለመቆየት ከተመቻቹለትም እስከ 72/ሰአት ድረስ ቆይታ ያደርጋል፡፡ የሴቷ የዘር ፍሬ ግን ሁኔታዎች በተሙዋሉበት ከ24-48 ሰአት ድረስ ብቻ መቆየት ይችላል፡፡ ኢሶግ፡ አንዲት ሴት በኮንዶም የተጠራቀመ የዘር ፈሳሽን ወደ ማህጸን በግልዋ ማስገባት ትችላለች? ዶ/ር ኢያሱ፡ የዘር ፈሳሽን ወደማህጸን ማስገባት የሚል አሰራር በግለሰብ ደረጃ የለም፡፡ ምናልባትም ሰዎች የተፈጥሮን አቀማመጥ ካለመረዳት የሚያስቡት ሊሆን ይችላል፡፡

በመጀመሪያ ብልት አለ፡፡ ከዚያም የማህጸን በር ይገኛል፡፡ ከዚያ በሁዋላ የማህጸን ቱቦ ጋ ደርሶ ፈሰሽን ማስገባት ሲቻል ነው እርግዝና ይኖራል የሚባለው፡፡ ብዙዎች የሚያስቡት ልክ ከብልት ቀጥሎ የሚያገኙትን አካል ማህጸንን እንደሚያገኙ አድርገው ከሆነ ስህተት ነው፡፡ ከማህጸን ቱቦ መድረስ የሚቻለው ክኒካል በሆነ የህክምና አሰራር እንጂ በግል አይደለም፡፡ በእርግጥ የወንድ የዘር ፈሳሽ በብልት እና በማህጸን በር አካባቢ በመፍሰሱ ብቻ የመቆየት እድሉን ካገኘ እራሱ ዋኝቶ እርግዝና እንዲከሰት የሚያደርግበት አጋጣሚ ስለሚስተዋል ይህንን እድል መጠቀም ይቻል ይሆናል፡፡ ነገር ግን ሊታወቅ የሚገባው የምንጠቀምባቸው ኮንዶሞች ፀረ ስፐርም ያልሆኑና የማያዳክሙ አይነት መሆናቸውን ማረጋገጥ ነው፡፡ ኢሶግ፡ ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩ ወይንም የተለያየ ውጤት ያላቸው ሰዎች ልጅ ለመውለድ ምን ማድረግ አለባቸው? ዶ/ር ኢያሱ፡ ይህንን ፍላጎት ለማሟላት ብዙ መፍትሔዎች አሉ፡፡ ወሲባዊ ግንኙነት ከኮንዶም ውጪ ከተደረገ ከአንዱ ሰው ወደሌላው እንዲሁም ወደሚረገዘው ልጅ ቫይረሱ መተላለፉ እርግጥ ነው፡፡

ነገር ግን ይህንን የመተላለፍ እድል ለመቀነስ መደረግ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች አሉ፡፡ የመጀመሪያው የቫይረሱ መጠን በሰውነትዋ ውስጥ አድጎ ከሆነ ወይንም የመከላከል አቅሙዋ ቀንሶ ከሆነ የፀረ ኤችአይቪ መድሀኒት በመውሰድ በደምዋ ውስጥ የሚገኘውን የቫይረስ መጠን እንዲቀንስ ማድረግ ነው፡፡ በዚህም አንዳቸው ለሌላኛው የሚያስተላልፉትን ቫይረስ ከመቀነስ ባሻገር ጤነኛ ልጅ ለመውለድ ያስችላቸዋል፡፡ በእርግጥም ቫይረሱ የመተላለፉን አደጋ ሙሉ በሙሉ ያስወግዳል ባይባልም እጅግ ይቀንሰዋል፡፡ ስለዚህ ወደሕክምናው በመሄድ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ ይጠቅማል፡፡ የፀረ ኤችአይቪ መድሀኒቱን ወስዶ በደም ውስጥ ያለውን ቫይረስ መቀነሱ ከታወቀ በሁ ዋላ የወር አበባ ቀንን በመቁጠር ማርገዝ በሚቻልባቸው ቀናት ብቻ ያለኮንዶም ግንኙነት ማድረግ እንደ አንድ አማራጭ ሊያዝ ይችላል፡፡ ይህ ግን ውስን ለሆነ ቀን እንደመጨረሻ አማራጭ የሚወሰድ መሆኑ ልብ ሊባል ይገባል፡፡

በእኛ አገር ባይኖርም ባደጉ አገሮች እንደ አማራጭ ከሚወሰዱ መንገዶች መካከል የወንድ የዘር ፍሬ ተወስዶ በማሽን የሚታጠብበት ነው፡፡ የወንዱ የዘር ፍሬ ከቫይረሱ ከጸዳ በሁዋላ በመርፌ ወደ ሴቷ ማህጸን እንዲገባ በማድረግ ልጅ መውለድ የሚቻልበት መንገድ አለ፡፡ በአጠቃላይ ግን ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩም ሆኑ ማንኛውም ሰው እርግዝናን ሲያስብ አስቀድሞ ሐኪምን ማማከር እንደሚገባ መዘንጋት የለበትም፡፡

Read 27100 times