ዱም ሚዲያና ፕሮሞሽን ወርሃዊ የሥነ ጽሑፍ ምሽቱን ትናንት አቀረበ፡፡ ከምሽቱ 11 ሰዓት “ብእር በዜማ” በሚል ርእስ በአምባሳደር መናፈሻ የቀረበው ወርሃዊ የሥነጽሑፍ ምሽት በከረምቤ ባሕላዊ የሙዚቃ ቡድን ጣእመዜማዎች የታጀበ ነው፡፡ በምሽቱ አልአዛር ሳሙኤል፣ ምልዕቲ ኪሮስ፣ ሰለሞን ሰሀለ፣ ሰናይት አበራ፣ ገነት አለባቸው፣ አንዱዓለም አሰፋ፣ እንድርያስ ተረፈ እና ሌሎች የሥነጽሑፍ ሥራዎቻቸውን አቅርበዋል፡፡